top of page


ከህግ ውጪ ታስረው የነበሩ ከ1300 በላይ እስረኞችን ማስለቀቁን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ተናገረ፡፡
የካቲት 17/2018 ከህግ ውጪ ታስረው የነበሩ ከ1300 በላይ እስረኞችን ማስለቀቁን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ተናገረ፡፡ ኮሚሽኑ ይህንን ያለው ጋዜጠኞችን ጠርቶ አሳሳቢ የሰብዓዊ መብት አያያዞችንና ጠቅለል ያሉ ስራዎችን በተመለከተ ማብራሪያ በሰጠበት ወቅት ነው፡፡ በኢትዮጵያ ከህግ ውጪ በዘፈቀደ የሚደረግ እስር መኖሩንና ይህም የሰዎችን ህገ መንግስታዊ መብት የሚፃረር በመሆኑ ተደጋጋሚ ውትወታዎችን ሲያደርግ መቆየቱን ኮሚሽኑ ጠቁሟል፡፡ በዚህም በተያዘው ዓመት ከህግ ውጪ የሆነ እስር የመቀነስ አዝማሚያ አሳይቷል ያሉት የሰብኣዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ፤ባደረግነው ውትወታ 130 በላይ በዘፈቀደ ታስረው የነበሩ ሰዎችን አስለቅቀናል ብለዋል፡፡ ከኦሮሚያ ክልል 915 ሰዎች ተለቅቀዋል፤በአማራ ክልል 186፣በሶማሌ ክልል 123፣ በጋምቤላ
Feb 241 min read


በመገኛኛ ብዙሃን ሴቶችና ህፃናት የሚወከሉበት መንገድ መብቶቻቸውን ጥያቄ ውስጥ የሚከት መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ተናገረ፡፡
የካቲት 17/2018 በመገኛኛ ብዙሃን ሴቶችና ህፃናት የሚወከሉበት መንገድ መብቶቻቸውን ጥያቄ ውስጥ የሚከት መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ተናገረ፡፡ ኮሚሽኑ ከዚህ ቀደም ባደረኩት ክትትል ትኩረት የሚያስፈልጋቸውና አብዛኛውን የማህበረሰብ ክፍል የሚይዙት የሴቶችና ህፃናት መብት አጠባበቅ ላይ መሻሻሎች ቢኖሩም በተለይ በመገናኛ ብዙሃን ሲቀርቡ በሚገባቸውን ልክ ይወከላሉ ወይ? የሚለው ጉዳይ ላይ ብዙ ክፍተቶችን ተመልክተናል ብሎናል፡፡ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት በእለት ተእለት ስራቸው መብቶቻቸውን ላለመጣስ የሴቶችና ህፃናት መብቶችን ለመጠበቅ የወጡ አዋጆችንና ድንጋጌዎችን እየፈተሹ መስራት ላይ ችግሮች አሉ ያሉን በኮሚሽኑ የሴቶችና ህፃናት የስራ ክፍል ዳይሬክተር የሆኑን ወ/ሮ ሰላማዊት ግርማይ ናቸው፡፡ በተለያዩ ዘገባዎች ስለ ሴቷ
Feb 242 min read


በጋምቤላ ክልል ናፍጣ በሊትር እስከ 280 ብር እየተሸጠ ነው ሲሉ በክልሉ የተሰማሩ ባለሀብቶች ቅሬታቸውን አቀረቡ፡፡
የካቲት 17/2018 በጋምቤላ ክልል ናፍጣ ከገበያው ዋጋ በላይ በሊትር እስከ 280 ብር እየተሸጠ ነው ሲሉ በክልሉ የተሰማሩ ባለሀብቶች ቅሬታቸውን አቀረቡ፡፡ የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ከአልሚዎቹ እየተነሳ ስላለው ቅሬታ አላውቅም ብሏል፡፡ ይህ የናፍጣ የሽያጭ በህገወጥ መንገድ ሳይሆን በግላጭ በማደያዎች እየተፈፀመ እንደሆነም ሰምተናል። በነዳጅ መጨመር ምክንያትም ከ75% በላይ የሚሆን የእርሻ መሬት ፆም አዳሪ ሆኖ እንደሚከርምም አልሚዎቹ ስጋታቸውን ነግረውናል። ስራ ያቆሙ እንዳሉም ሰምተናል። በዚህ ዘርፍ ለተሰማሩ አልሚዎች በታሪፉ የሚቀርበውን ነዳጅ የክልሉ ንግድ ቢሮ ከደላሎች ጋር ተመሳጥሮ እየተጠቀሙበት ነውም ብለውናል። የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ በበኩሉ አንድ ነዳጅ በ134 ብር ከ 79 ሳንቲም እንደሚሸጥ እንጂ እስከ
Feb 241 min read


በኢትዮጵያ የኮንትሮባንድ ንግድ ከመፈታት ይልቅ ይበልጥ ውስብስብ እየሆነ መምጣቱ ተነገረ።
የካቲት 17/2018 በኢትዮጵያ የኮንትሮባንድ ንግድ ከመፈታት ይልቅ ይበልጥ ውስብስብ እየሆነ መምጣቱ ተነገረ። በ5 ዓመታት ውስጥ ብቻ በኮንትሮባንድ ከኢትዮጵያ የሚወጡ ሸቀጦች ዋጋ ግምት ከ 1.3 ቢሊየን ብር ወደ 8.9 ቢሊየን ብር ማደጉ ተጠቅሷል። በ2011 ዓ.ም 340 ሚሊየን ብር የነበረው በኮንትሮባንድ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ሸቀጦች ዋጋ ግምት በ2015 ዓ.ም ወደ 2.74 ቢሊየን ብር ከፍ ማለቱ ተነግሯል። የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ያዘጋጀው አራተኛው አገር አቀፍ የፀረ ህገ ወጥ ንግድ ኮንፈረንስ በስካይ ላይት ሆቴል እየተካሄደ ነው። የቁም እንስሳት ፣ መድሃኒቶች ፣ እና ቡና የኮንትሮባንድ ንግድ በስፋት ከሚካሄድባቸው ምርቶች መካከል እንደሆነ በኮንፈረንሱ ላይ ሲነገር ሠምተናል። ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ፣ ጁ
Feb 241 min read


የአሜሪካ ግዛቶችን የመታው ማዕበል የቀላቀለ ከፍተኛ የበረዶ ክምር ከ5 ሺህ በላይ በረራዎች እንዲሰረዙ ማድረጉ ተነገረ።
የካቲት 17/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #አሜሪካ ኒውዮርክን ጨምሮ የአሜሪካ ግዛቶችን የመታው ማዕበል የቀላቀለ ከፍተኛ የበረዶ ክምር ከ5 ሺህ በላይ በረራዎች እንዲሰረዙ ማድረጉ ተነገረ። ሄርናንዶ በተሰኘው ማዕበል እንደ ኒውዮርክ፣ኒውጀርሲ እና ማሳቹሴትስ ያሉት ግዛቶች በከፍተኛ ደረጃ መጠቃታቸው ተነግሯል። በአንዳንድ አካባቢዎች የበረዶ ክምሩ ከ55ሴንቲ ሜትር በላይ ከፍታ ያለው መሆኑም ተነግሯል። በከባድ ነፋስ በታጀበው የበረዶ ክምር ከ40 ሚሊየን በላይ ህዝብ በቤት ውስጥ ተገድቦ ውሎ ለማደር መገደዱም ተሰምቷል። በከፍተኛው የበረዶ ክምርና ነፋስ ምክንያት በውሃ ዳርቻ አካባቢ ባሉ ከተሞች የጎርፍ ስጋት እንዳይኖርም አስግቷል ተብሏል። የሚበዙት ግዛቶችም በአስቸካይ ጊዜ አዋጅ ውስጥ ለመቆየት ተገደዋል ሲል ፒ.ቢ.ኤስ የወሬ ምንጭ ዘግቧል። ከባድ የ
Feb 242 min read


የገልፍ ሃገራትን ዘንግቶ የቆየው የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ መንገድ (ክፍል 4)
የካቲት 16/2018 #ጉዳያችን - የገልፍ ሃገራትን ዘንግቶ የቆየው የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ መንገድ (ክፍል 4) ኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ያሉ የገልፍ ሃገራት ቱሪስቶችን ለመሳብ ምን መስራት አለባት? እስካሁንስ የዘነጋችው ስራ ምንድን ነው? በጉዳዩ ላይ የታሪክ ተመራማሪው አደም ካሚል(ፕ/ር) የሰጡንን ማብራሪያ ያድምጡ…. ቴዎድሮስ ወርቁ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx X :- https://x.c
Feb 231 min read


በሀገሪቱ ከትምህርት ውጪ የሆኑት፤ ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ጉዳይ!
የካቲት 16/2018 በኢትዮጵያ በተለይም ግጭት በሚደጋገምባቸው አካባቢዎች ተማሪዎች ለዓመታት ከትምህርት ውጪ ሆነው ቆይተዋል፡፡ በዚህ ወቅትም እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ውጪ እንደሆኑ የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል፡፡ የፀጥታ ሁኔታ መረጋጋት በታየባቸው ቦታዎችም ቢሆን፤ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ለመመለስ የበዙ ፈተናዎች እንደሚያጋጥሙ ይነገራል፡፡ ከእነዚህም መካከል ተማሪዎቹ 2 እና 3 ዓመታት ከትምህርት ርቀው ሲመለሱ ለድባቴ፣ እድሜዬ ከፍ ብሎ እንዴት ዝቅ ብዬ እማራለሁ በማለት ለስደት፣ ላለዕድሜ ጋብቻ እና ለመሳሰሉት ችግሮች እንደሚዳረጉ ይጠቀሳል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ጦርነት እና ግጭት የተደጋገመባቸው የአማራ እና የትግራይ ክልሎች እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቀናል፡፡ ሙሉ ዘገ
Feb 231 min read


የኢትዮጵያ ግብርና ለባለመዋዕለ ነዋዮች ሳቢ ያልሆነው ለምንድነው?
የካቲት 16/2018 ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ቢሆንም ሀብት እውቀታቸው ይዘው ወደዘረፋ የሚቀላቀሉ ባለመዋዕለ ነዋዮች ግን እንደሚፈለገው አይደለም፡፡ ባለሀብቶች ፣ ትራክተር እና ኮምፓልነር ይዘው ግብርና ከመስራት ይልቅ በሪል ስቴት ፣ በሆቴል በመሳሰሉትና በከተማ በሚሰሩ ዘርፎች በስፋት ሲሰማሩ ይታያል፡፡ የኢትዮጵያ ግብርና ለባለመዋዕለ ነዋዮች ሳቢ ያልሆነው ለምንድነው? በሰብል እና ጥጥ የግብርና ዘርፍ ላይ ትሰማርተው የሚሰሩ ባለመዋዕለ ነዋዮች የፋይናንስ ፣ የመሰረተ ልማት አለመሟላት፣ የብድር አቅርቦት አለመመቻቸት ፣ የፀጥታ ችግር እና መሰል ችግሮች በእርሻው ልማት ላይ እየፈተናቸው መሆኑን ያስረዳሉ። የግብርና ሚኒስቴር አልሚዎቹ ያነሷቸው ችግሮች መኖራቸውን ያምናል። የግብርና ሚኒስቴርና ኢንቨስትመንትና ምርት ግብይት ዴስክ ሃላፊ
Feb 231 min read


በባንኮችና በሌሎችም ዘርፎች እንደተደረገው ለውጭ አየር መንገዶች ዘርፉን የመክፈት ፍላጎት መንግስት ለጊዜው የለውም ተባለ፡፡
የካቲት 16/2018 በባንኮችና በሌሎችም ዘርፎች እንደተደረገው ለውጭ አየር መንገዶች ዘርፉን የመክፈት ፍላጎት መንግስት ለጊዜው የለውም ተባለ፡፡ በኢትዮጵያ የሚሰሩ የግል አየር መንገዶች ብዛት 12 ቢደርስም እነደ ኬኒያ እና ኡጋንዳ ካሉት የጎረቤት ሀገራት ጋር ሲነፃፀር ግን በአቅምም በቁጥርም ዝቅተኛ ነው ይባላል። እነዚህ የግል አየር መንገዶች(General Aviation) ዘርፉ ጠንክሮና እራሱን ችሎ መቆም እስከሚችል ድረስም መንግስት የውጭ ሀገር አየር መንገዶችን የመጋበዝ ፍላጎት የለውም ተብሏል። የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሃንስ አበራ እንደነገሩን በሂደት ግን በሩ ለውጭ ባለሃብቶች ክፍት መሆኑ አይቀርም። በኢትዮጵያ በግል አየር መንገድ የተሰማሩ ኩባንያዎች ከህግ እስከ አሰራር የሚያነሷቸው ብዙ ችግሮች እንዳሉ ይነ
Feb 231 min read


በ12 ባለሃብቶች ከንጋት ሃይቅ 3.8 ሚሊዮን ኪሎ ግራም አሳ መመረቱ ተነገረ፡፡
የካቲት 16/2018 በ12 ባለሃብቶች ከንጋት ሃይቅ 3.8 ሚሊዮን ኪሎ ግራም አሳ መመረቱ ተነገረ፡፡ በሃይቁ ካለው ከፍተኛ የአሳ ምርት አንፃር አሁንም ቢሆን በበቂ መጠን እየተመረተ አይደለም ተብሏል። ተጨማሪ ባለሃብቶች ወደ ስራው እንዲገቡም ጥሪ ቀርቧል፡፡ የታላቁ ህዳሴ ግድብ በፈጠረውና ንጋት በሚል ስያሜ በሚጠራው ሰው ሰራሽ ሃይቅ የሚድሮክ ኤትዮጵያ አካል የሆነው ኤልፎራ አግሮ ኢንዱስትሪን ጨምሮ 12 ባለሃብቶች ከጉባ አካባቢ ወጣቶች ጋር በመሆን በዚህ ዓመት 3ሺህ 895 ቶን ወይም 3.8 ሚሊዮን ኪሎ ግራም አሳ አምርተው ለገበያ ማቅረባቸውን ሰምተናል፡፡ ባለሃብቶቹ ለአሳ ምርት አስፈላጊ የሆኑ የማስገሪያ ማሽነሪዎችንና ምርቱን ለማጓጓዝ የሚሆኑ ማቀዝቀዣ የተገጠመላቸው ተሽከርካሪዎችን በማቅረብ ወደ ስራው መግባታቸውን ግድቡ የሚገኝበት የ
Feb 232 min read


አሜሪካ የመርከብ ላይ ሆስፒታሏን ወደ ግሪንላንድ ደሴት ለመላክ መወጠኗን ዴንማርክ ውድቅ አደረገችው፡፡
የካቲት 16/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #አሜሪካ አሜሪካ የመርከብ ላይ ሆስፒታሏን ወደ ግሪንላንድ ደሴት ለመላክ መወጠኗን ዴንማርክ ውድቅ አደረገችው፡፡ ቀደም ሲል የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ የመርከብ ላይ ሆስፒታሉን ወደ ግሪንላንድ ለመላክ መወጠናቸውን በትሩዝ ማህበራዊ ትስስር ገፃቸው እወቁልኝ ማለታቸውን AFP አስታውሷል፡፡ የዴንማርኩ የመከላከያ ሚኒስትር ግሪንላንድ ይሄ ዓይነቱ የአሜሪካ የጤና ድጋፍ አያሻትም ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ የአርክቲክ ክበቧ የአለማችን ታላቋ ደሴት ግሪንላንድ የአውሮፓዊቱ ዴንማርክ የራስ ገዝ ግዛት ነች፡፡ ትራምፕ ለአሜሪካ ደህንነት በእጅጉ አስፈላጊ በመሆኗ ከአሜሪካ ጋር መዋሐድ ይኖርበታል ሲሉ ቆይተዋል፡፡ የትራምፕ ውጥን ከዴንማርክም ሆነ ከግሪንላንዳውያ በኩል ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል፡፡ የአሜሪካው ፕሬዘዳ
Feb 232 min read


በኢትዮጵያ ህገ መንግስት የሚነሱበት አከራካሪ ጉዳዮች
የካቲት 14/2018 ህገ መንግስት ይሻሻል ወይስ ባለበት ይሁን፣ በፓርላመንታዊ ስርዓት እንቀጥል ወይስ ፕሬዝዳንታዊውን እንከተል፣ የባንድራ ጉዳይ የምርጫ ሁኔታና ሌሎችም መሰል ሃሳቦች ብዙ ጊዜ የፖለቲካ ሰዎች የሚከራከሩባቸው ጉዳዮች ናቸው። ህገ መንግስት ሙሉ ለሙሉ መለወጥ አለበት እና ፈጽሞ መነካት የለበትም የሚሉ የተራራቁ ሃሳቦች እንዳሉ በተለያየ ጊዜ ሰምተናል። ነገር ግን መለወጥ አለበት የሚሉ ወገኖችም ቢሆኑ የትኞቹ በሚለው ላይ ሰፋ ያለ ልዩነት እንዳላቸው ይጠቀሳል። አቶ ፍሬህይወት ሳሙኤል የቀድሞ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ምርጫ 1997 ተከትሎ በተነሳ ሁከት፣የሁከቱ አጣሪ ኮምሽን ሰብሳቢ ነበሩ። አቶ ፍሬህይወት በእነዚህ አከራካሪ የህገ መንግስት ጉዳዮች ላይ መፅሐፍ የፃፉ ሲሆን
Feb 212 min read


ዘንድሮ ይደረጋል ተብሎ ለሚጠበቀው ሀገራዊ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል እጩዎች ምዝገባ
የካቲት 14/2018 ዘንድሮ ይደረጋል ተብሎ ለሚጠበቀው ሀገራዊ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል እጩዎች ምዝገባ ጊዜ እስከ ፊታችን ሰኞ ድረስ መራዘሙ ይታወቃል፡፡ እጩ ምዝገባ ጊዜው እንዲራዘምላቸው ከጠየቁት መካከል አምስት ፓርቲዎች ያሉበት ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት አንደኛው ነው፡፡ ትብብሩ የእጩ ምዝገባ ጊዜው በመራዘሙ በሚፈልገው ልክ እጩዎቹን አስመዝግቦ እንዲሆን ጠይቀነዋል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. የኔነህ ሲሳይ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm
Feb 211 min read


የፔሩ ፓርላማ ጆሴ ማሪያ ባልካዛርን የሀገሪቱ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት አድርጎ ሰየመ።
የካቲት 13/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #ፔሩ የፔሩ ፓርላማ ጆሴ ማሪያ ባልካዛርን የሀገሪቱ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት አድርጎ ሰየመ። ፓርላማው ቀደም ብሎ ለአራት ወራት በተጠባባቂ ፕሬዝዳነትነት ያገለገሉትን ጆሴ ጄሪ በሙስና ምክንያት ከስልጣን ማንሳቱ ይታወሳል። አሁን የተመረጡት ፕሬዝዳንት ጆሴ ማሪያ ባልካዛር የፓርላማው አባል እንደሆኑ ተነግሯል በአስር ዓመት ውስጥ በፔሩ ስምንት ፕሬዝዳንቶች መፈራረቃቸውን ሮይተርስ ጽፏል። ሀገሪቱ ሚያዝያ ወር ላይ ፕሬዝደንቷን እና የፓርላማ አባላትን ምርጫ ለማካሄድ ቀጠሮ ይዛለች። #ብሪታንያ የብሪታንያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር በዲኤጎ ጋርሺያ የአየር ሃይል ሰፈር ዙሪያ የደረሱት ስምምነት ትልቅ ስህተት ያለበት ነው ሲሉ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ተቹ። ዲኤጎ ጋርሺያ
Feb 203 min read


የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከዚህ በኋላ ኢንዱስትሪዎች የሚገነባባቸው አካባቢዎች መሰረተ ልማት ለሟሟላት አመቺ ካልሆነ አይገነባም አለ፡፡
የካቲት 13/2018 የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከዚህ በኋላ ኢንዱስትሪዎች የሚገነባባቸው አካባቢዎች መሰረተ ልማት ለሟሟላት አመቺ ካልሆነ አይገነባም አለ፡፡ አሁን ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋት በማሰብ መሬት በአንዳንድ ክልሎች ለማዘጋጀት እየተሰራ ነው ብሏል፡፡ በተለያዩ ምክንያቶች ከዚህ ቀደም ከተዘጉ ኢንዱስትሪዎች መካከል አብዛኛዎቹ ወደ ስራ ለመመለስ ተችሏል ብሏል የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፡፡ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል የፋይናንስ አቅርቦት እጥረት የውጪ ምንዛሪ በተፈለገው ልክ አለማግኘትና ሌሎችም ችግሮች በተለያዩ ጊዜያት በአምራቾች ዘንድ ሲነሳ የነበረ ችግር ነው ብለዋል፡፡ መንግስት እነዚህ ችግሮችን ለመፍታት ባለፉት 4 ዓመታት እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ባለፉት 3 አማታት የተካሄደው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከመጀመሩ በፊ
Feb 201 min read


አካል ጉዳተኞችን በሚመለከት በማህበረሰቡ በኩል የሚሰጡ የተሳሳተ ግምቶች በተለይ ሴት አካል ጉዳተኞች ወደ ሃላፊነት እንዳይመጡ አድርጓል ተባለ።
የካቲት 13/2018 አካል ጉዳተኞችን በሚመለከት በማህበረሰቡ በኩል የሚሰጡ የተሳሳተ ግምቶች በተለይ ሴት አካል ጉዳተኞች ወደ ሃላፊነት እንዳይመጡ አድርጓል ተባለ። ይህን ያሉት የፖለቲካ ፓርቲዎች ናቸው። ያነጋገርናቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች አካል ጉዳተኞችን ወደ አመራርነት ቦታ እንዲመጡ፣ ውሳኔ ሰጪም እንዲሆኑ፣ በመጪው ምርጫ እራሳቸውንም እንዲወክሉ እያደረግን ነው ብለዋል። ሆኖም በማህበረሰቡ በኩል በተለይ ሴት አካል ጉዳተኞች አይችሉም የሚል የተሳሳተ ግምት ስለሚሰጥ እነሱም አቅሙ ቢኖራቸውም ደፍረው ለመሳተፍ ፍቃደኛ እንዳይሆኑ አድርጓቸዋል ተብሏል። የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት(መኢአድ) የድርጅት ጉዳይ እና የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ እና የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ዋና ፅሀፊ አቶ ሙሉጌታ አበበ እንደ መኢአድ አካል
Feb 201 min read


ነዳጅ ለዝርፊያ እንዳይጋለጥ አዲስ የስርጭት ሥርዓት መዘርጋቱን ነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ተናግሯል፡፡
የካቲት 13/2018 ከፍተኛ የውጪ ምንዛሪ የሚመደብለት ነዳጅ ለዝርፊያ እንዳይጋለጥ ሌብነትም ለማስቀረት አዲስ የስርጭት ሥርዓት መዘርጋቱን የኢትዮጵያ ነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ተናግሯል፡፡ ለመሆኑ ይህ ሥርዓት በተለይ በስፋት ኢንቨስት ያደረጉትን ግለሰቦች እንዳይጎዳስ ምን ያህል የተጠና ነው? ባለስልጣኑስ ከዚህ መአዘን ያለው ልምድ እና ከለውጡ ጋር ተያይዞ ሊፈጠር የሚችል ነዳጅ እጥረት እንዳይኖር ምን ያህል የቤት ስራውን አጠናቋል፡፡ በተለይ በየማደያው ፤ በየግዜው እና በየደረጃው ሰፋ ያለ ኢንቨስትመንት ያደረጉ ድርጅቶች የስርጭት መጠኑ ምን ያህል ተጠንቶላቸዋል? በዚህ ጉዳይ፤ የነዳጅ እና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶር ደስታው መኮንን ጠይቀናል። ተህቦ ንጉሴ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና
Feb 201 min read


በኢትዮጵያ 5,600 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተመዝግበው በስራ ላይ መሆናቸው ተነገረ፡፡
የካቲት 13/2018 በኢትዮጵያ 5,600 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተመዝግበው በስራ ላይ መሆናቸው ተነገረ፡፡ ከዛሬ 40 አመት በፊት የ1977ቱን ድርቅ ተከትሎ ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረግ ወደ ኢትዮጵያ የመጣው ኬር ኢትዮጵያ ከነዚህ ድርጅቶች ውስጥ አንደኛው ሲሆን ኢትዮጵያ ውስጥ ስራ ከጀመርኩ 40 አመት ሆኖኛል ብሏል፡፡ ትናንት በሸራተን ሆቴል በተሰናዳ ዝግጅትም ይህንኑ የ40 ዓመት የስራ ጉዞውን አስቧል፡፡ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ፤ኬር ኢትዮጵያ ከዛሬ 40 አመት በፊት ኢትዮጵያ የከፋ የሰብአዊ ቀውስ ውስጥ በነበረችበት ጊዜ የመጣ ድርጅት መሆኑን ተናግረዋል። ኬር በአለም ዙሪያ በ121 ሀገሮች እንደሚራ የተነገረ ሲሆን በኢትዮጵያ ያለው ፕሮጀክትም ከሁሉም በመጠኑ ትልቁ እንደሆነ
Feb 201 min read
አዋሽ ኢንሹራንስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጓዦችን የጉዞ የጤና ኢንሹራንስ ሽፋን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ስምምነት አደረገ።
የካቲት 12/2018 አዋሽ ኢንሹራንስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጓዦችን የጉዞ የጤና ኢንሹራንስ ሽፋን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ስምምነት አደረገ። ስምምነቱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቺፍ ኮሜርሺያል ኦፊሰር አቶ ለማ ያዴቻ እና የአዋሽ ኢንሹራንስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጅባት አለምነህ በዛሬው እለት ተፈራርመውታል። በስምምነቱ መሰረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጓዦች የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የሞባይል መተግበርያ ላይ የጉዞ ኢንሹራንስ ሽፋን አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላቸዋል ተብሏል። የመድን አገልግሎቱ ተጓዦች ለተለያዩ ጉዳዮች ወደተለያዩ የዓለም ክፍሎች ሲጓዙ ለሚያገጥማቸው የተለያዩ የጤና እክሎች እንደሚውል ተጠቅሷል። የዋሽ ኢንሹራንስ ዋና ስራ አሰፈፃሚ አቶ ጅባት አለምነህ "ከኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከአለ
Feb 191 min read


የሰላም እጦት ኢትዮጵያን በቆዳው ዘርፍ ማግኘት የሚገባትን ያህል ገቢ እንዳታገኝ አድርጓታል ሲል የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ተናገረ።
የካቲት 12/2018 የሰላም እጦት ኢትዮጵያን በቆዳው ዘርፍ ማግኘት የሚገባትን ያህል ገቢ እንዳታገኝ አድርጓታል ሲል የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ተናገረ። ማህበሩ ይህን ያለው ለ15 ኛ ጊዜ የሚያካሄደውን የመላው አፍሪካ የቆዳ ንግድ ትርኢት “ሜሴ ፍራንክፈርት” ከተሰኘ አለም አቀፍ የንግድ ትርኢት አዘጋጅ ጋር በጋራ ለማከናወን ትናንት በስካይ ላይት ሆቴል ባደረጉት ስምምነት ወቅት ነው። በመድረኩ ላይም በፀጥታ ችግር ምክንያት ከፍተኛ ቆዳ የሚገኝባቸው አካባቢዎች ላይ ቆዳዎችን ለመሰብሰብ ባለመቻሉ በርካታ ቆዳዎች በስብሰው እንደቀሩም ተነግሯል። በዚህ ምክንያት ኢንደስትሪዎች ማምረት የሚገባቸውን ያህል የቆዳ ውጤቶች እንዳያመርቱ ፥ ሀገርም በዘርፉ ማግኘት የሚገባትን ያህል እንዳታገኝ አድርጎታል ተብሏል። በዘርፉ የተሰማሩ ኢንደስትሪዎች እየተቸገሩ
Feb 192 min read


የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ ኢራንን ለመምታት መዘጋጀቱን ተሰማ፡፡
የካቲት 12/2018 የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ ኢራንን ለመምታት መዘጋጀቱን ተሰማ፡፡ ዋሽንግተንን ቴህራንን በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት ለመምታት ዝግጅት ማድረጓን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ሰዎች ነግረውናል ብሎ የዘገበው ሲ ኤን ኤን ነው፡፡ ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግን የመጨረሻውን ውሳኔ አለመስጠታቸው በመረጃ ተጠቅሷል፡፡ የአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ከፍተኛ ባለስልጣናት በትላንትናው እለት በዋይት ሐውስ ተገኝተው በኢራን ጉዳይ ላይ ውይይት ማድረጋቸውም ተነግሯል፡፡ ትራምፕም ከኢራን ጋር ስለተደረገው ድርድር ሁኔታ ከልዩ መልዕክተኛው ስቲቭ ዊትኮፍ እና ከአማቻቸው ጃሬድ ኩሽነር ማብራሪያ እንደተሰጣቸው በመረጃው ተነስቷል፡፡ አሜሪካና ኢራን ያደረጉት ትራምፕ ቀይ መስመር በሚላቸው ጉዳዮች ላይ አሁንም ከስምምነት አለመድረሱ ተዘግቧል፡፡
Feb 191 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

