top of page


ኢትዮዽያ በአለም የሎጅስቲክስ ሜዳ
የካቲት 27/2018 የሎጅስቲክስ ስራ ፍፁም የሰላም መስመር እና እውቀት ይፈልጋል፡፡ ሎጅስቲክስ በኢትዮጵያ እንዲዘምን፣ እንዲቀላጠፍ አሁንም ብርቱ ስራ ይጠይቃል። እቃዎችን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ለማንቀሳቀስ፣ መያዝ፣ ማከማቸት እና ማስተናገድ ፤ በየትኛውም የአለም መሮጫ ኮሪደር እና ባህር ማገላበጥ ፤ በአየር በየብስ ምድር ለመላወስ ጥንቅቅ ያለ የሎጅስቲክስ ስራ ይፈልጋል። ለዚህ ደግሞ በየጊዜው በአለም በሚደረጉ ጉባኤዎች እና የሎጅስቲክስ ማህበራት ላይ በኃላፊነት ቦታ መገኘት እንደሚያስፈልግ ይታመናል። በተለይ ከአፍሪካ ብቸኛው የአለም ፍሬይት ፎርዋርደርስ ማህበር ፊያታ የቦርድ አባል እና በ ኢትዮጵያም የማህበሩ ፕሬዝዳንት አቶ ዳዊት ውብሸት በዚህ ጉዳይ ስጋት እንዳላቸው ነግረውናል። ኢትዮዽያ በአለም የሎጅስቲክስ ሜዳ ፤ በጭነት መርከቦች እና አጠቃላ
Mar 61 min read


የኤ ኤፍ ጂ ኤርክራፍት ፋይናንስ ጀርመን (AFG) እህት ኩባንያ የሆነው ኤ ኤፍ ጂ አቪየሺን አየርላንድ ኩባንያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው አፍሪካ ሀገራት መግባቱን ተናገረ።
የካቲት 24/2018 በአውሮፕላን ንግድና ሀብት አስተዳደር የሚታወቀው ኤ ኤፍ ጂ ኤርክራፍት ፋይናንስ ጀርመን (AFG) እህት ኩባንያ የሆነው ኤ ኤፍ ጂ አቪየሺን አየርላንድ ኩባንያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው አፍሪካ ሀገራት መግባቱን ተናገረ። ኩባንያው ለአፍሪካ ስራው ሲልም ሁለት ከፍተኛ ባለሞያዎቹን በአፍሪካ ተገኝተው እንዲሰሩ እንደመደባቸው ባወጣው መግለጫ ተናግሯል። AFG አቪዬሽን አየርላንድ የናይጄሪያው ካሊ ኤር ሁለት CRJ1000 አውሮፕላኖች ባለቤት እንዲሆን ማስቻሉን ተናግሯል። በዚህም የተነሳ የአፍሪካ ሀገራት አየር መንገዶች፣ አፕሬተሮች፣ የመንግሥት እና የአቪዬሽን ዘርፍ ሀላፊዎች ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለቸው ተረድቻለሁ ብሏል። ይህ ፍላጎት የአፍሪካ የአቪዬሽን ዘርፍ በአለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እየተቀየረ መምጣቱን ያሳል ሲልም ኩ
Mar 42 min read


አቢሲንያ ባንክ ‹‹ይጀምሩ፣ ያድሱ እና ይደጉ›› በሚል መሪ ቃል ለሁለት ወራት ያህል ባካሄደው ፕሮግራም ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ ተቀማጭ ገንዘብ መሰብሰብ መቻሉን ተናገረ።
የካቲት 19/2018 አቢሲንያ ባንክ ‹‹ይጀምሩ፣ ያድሱ እና ይደጉ›› በሚል መሪ ቃል ለሁለት ወራት ያህል ባካሄደው ፕሮግራም ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ ተቀማጭ ገንዘብ መሰብሰብ መቻሉን ተናገረ። ከዚህ በተጨማሪም 140 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ ማግኘቱን አስረድቷል። ባንኩ ፕሮግራሙን ሲያካሂድ የነበረው አዳዲስ ደንበኞችን ለመመልመል፣ ነባር ደንበኞችን ከባንኩ ጋር ያላቸውን ደንበኝነት ለማደስ እንዲሁም ተቀማጭና የውጭ ምንዛሬ ግኝቶችን ለማሳደግ አስቦ እንደነበር ተጠቅሷል። ይህ ፕሮግራም ከህዳር 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ጥር 29 / 2018 ዓ.ም. ድረስ ሲካሄድ ቆይቷል ተብሏል። አቢሲኒያ ባንክ በዚህ መርሃግብር ደንበኞቹ ለማበረታታት ሽልማት አዘጋጅቷል። በዚህ መርሀ ግብር ለሽልማቱ ተሳታፊ የሆኑት ከብር 1000 ሺሕ ብር ጀምሮ ተ
Feb 261 min read


ኢትዮጵያን ከሌሎች ሀገሮች ልዩ ከሚያደርጓት ስርዓቶች አንዱ የቡና አፈላል ስርዓቷ ነው፡፡
የካቲት 17/2018 ኢትዮጵያን ከሌሎች ሀገሮች ልዩ ከሚያደርጓት ስርዓቶች አንዱ የቡና አፈላል ስርዓቷ ነው፡፡ ቡና በኢትዮጵያ ከተሞችም ሆነ ገጠራማ አካባቢዎች ላይ የተለየ የአቀራረብ ስርዓት አለው፡፡ ይህ የቡና አፈላል ሥርዓትና ሂደት ኢትዮጵያ አለማቀፍ ቅርስ አድርጋ ለማስመዝገብ ስራ መጀመሯም እየተነገረ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የቡና አፈላል ሥርዓት (የቡና ሥነ-ሥርዓት) በዓለም አቀፉ የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (UNESCO) በማይዳሰሱ የባህል ቅርሶች መዝገብ ላይ እንዲሰፍር ለማድረግ ስራ ከጀመረች ሰንብታለች፡፡ ኢትዮጵያ የቡና (Arabica Coffee) መገኛ ምድር ብቻ ሳትሆን፣ ቡናን ከመጠጥነት ባለፈ የማኅበራዊ መስተጋብር፣ የሰላም፣ እና የባህል መገለጫዋ እንደሆነ ይነገራል፡፡ በተጨማሪም የቡና አፈላል ሥነ-ሥርዓት በኢትዮጵያውያን ዘንድ የ
Feb 241 min read


የሰላም እጦት ኢትዮጵያን በቆዳው ዘርፍ ማግኘት የሚገባትን ያህል ገቢ እንዳታገኝ አድርጓታል ሲል የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ተናገረ።
የካቲት 12/2018 የሰላም እጦት ኢትዮጵያን በቆዳው ዘርፍ ማግኘት የሚገባትን ያህል ገቢ እንዳታገኝ አድርጓታል ሲል የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ተናገረ። ማህበሩ ይህን ያለው ለ15 ኛ ጊዜ የሚያካሄደውን የመላው አፍሪካ የቆዳ ንግድ ትርኢት “ሜሴ ፍራንክፈርት” ከተሰኘ አለም አቀፍ የንግድ ትርኢት አዘጋጅ ጋር በጋራ ለማከናወን ትናንት በስካይ ላይት ሆቴል ባደረጉት ስምምነት ወቅት ነው። በመድረኩ ላይም በፀጥታ ችግር ምክንያት ከፍተኛ ቆዳ የሚገኝባቸው አካባቢዎች ላይ ቆዳዎችን ለመሰብሰብ ባለመቻሉ በርካታ ቆዳዎች በስብሰው እንደቀሩም ተነግሯል። በዚህ ምክንያት ኢንደስትሪዎች ማምረት የሚገባቸውን ያህል የቆዳ ውጤቶች እንዳያመርቱ ፥ ሀገርም በዘርፉ ማግኘት የሚገባትን ያህል እንዳታገኝ አድርጎታል ተብሏል። በዘርፉ የተሰማሩ ኢንደስትሪዎች እየተቸገሩ
Feb 192 min read


የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች መዋዕለ ነዋያቸውን ፈሰስ ለሚያደርጉ ባለሀብቶች እምነት እንዲያደርጉ ቢያስችላቸውም በየጊዜው የሚለዋወጡ ህጎች ግን አሁንም ችግር ሆኖ ቀጥሏል ተባለ፡፡
የካቲት 12/2018 ኢትዮጵያ እያደረገቻቸው ያሉ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በሀገሪቱ መዋዕለ ነዋያቸውን ፈሰስ ለሚያደርጉ ባለሀብቶች እምነት እንዲያደርጉ ቢያስችላቸውም በየጊዜው የሚለዋወጡ ህጎች ግን አሁን ኢንቨስት ለሚያደርጉ ችግር ሆኖ ቀጥሏል ተባለ፡፡ ከውጭ የሚመጣ ሀብት በተወሰኑ ዘርፎች ላይ ብቻ ማዋሉም ሌሎች ዘርፎች በቂ ፋይናንስ እንዳያገኙ ከልክሏል ተብሏል፡፡ እንደ ትምህርት ፣ ጤና ፣ አነስተኛ እና ጥቃቅን ስራ ፈጠራ በመሳሰሉ ማህበራዊ ዘርፎች የሚሳተፉና ተዕኖ የሚያሳድሩ፣ ትርፍም የሚያገኙ ተቋማት የኢንቨስትመንት ሁኔታ ምን ይመስላል በሚል የተደረገ የምክክር መድረክ ላይ ነው ወሬው የሰማነው፡፡ ዝግጅቱን ያሰናዳው ACE investment እና Impact Advisors የተባለ የኢትዮጵያ ተቋም ከአለም አቀፉ አቀፍ GSG ተቋም ጋ
Feb 191 min read


''ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ዘርፍ ብድር የምትፈልጉ ኑ ወደ እኔ በቂ የብድር ገንዘብ ተዘጋጅቶላችኋል'' የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
የካቲት 11/2018 ''ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ዘርፍ ብድር የምትፈልጉ ኑ ወደ እኔ በቂ የብድር ገንዘብ ተዘጋጅቶላችኋል'' ሲል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጥሪ አቀረበ። ባንኩ በዚህ ዘርፍ በአሁኑ ሰዓት ብዙ የብር ጥያቄዎች የሉብኝም ብሏል። ባንኩ ይህን ያለው በረመዳን ወር የእልምና እምነት ተከታይ ደንበኞቹ ዘካ ለመስጠት የሲቢኢ ኑር የዘካ ቁጠባ ሂሳብን እንዲገለገሉ ጥሪ ባቀረበበት ፕሮግራም ላይ ነው፡፡ ባንኩ ‘አብሮነትና በጎነት በረመዳን' ሲል የጠራውን ፕሮግራም በዛሬው እለት አስጀምሯል። የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል የዘካ ቁጠባ ሂሳብ አንዱ መሆኑን አስታውሰው በተለይ በረመዳን የእምነቱ ተከታዮች እንዲገለገሉበት ጥሪ አቅርበዋል፡፡ አገልግሎቱ የዘካ ሰጪና ተቀባዮችን ጊዜ፣ ወጪ፣ ልፋትና
Feb 181 min read


በተያዘው በጀት ዓመት 6 ወራት በስነ ምግባርና እና ብልሹ አሰራር ምክንያት 651 የሚሆኑ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሰራተኞች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተነገረ።
ጥር 28/2018 በተያዘው በጀት ዓመት 6 ወራት በስነ ምግባርና እና ብልሹ አሰራር ምክንያት 651 የሚሆኑ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሰራተኞች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተነገረ። አስተዳደራዊ እርምጃዎች ከተወሰደባቸው 651 ሰራተኞች የተሰናበቱ 13፣ የደመወዝ ቅጣት 481 እና 157 ደግሞ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ተነግሯል። ይህ የተነገረው አገልግሎቱ የ2018 በጀት ዓመት 6 ወራት አፈፃፀሙን በተመለከተ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው። በሌላ በኩል ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት በዲጅታል የሙስና መጠቆሚያ 251፣ በሌሎች አማራጮች (በአካል፣ በኢሜል፣ በስልክ) ደግሞ 60 በድምሩ 311 ጥቆማዎች እና አቤቱታዎች የቀረቡ መሆኑን ያነሳው አገልግሎቱ 270ቹ ተጣርተዋል ብሏል። በቀረቡ ጥቆማዎች መሰረትም ተጣርቶ ጥፋተኛ መሆናቸው ከተለዩ 118
Feb 51 min read


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባለፉት 6 ወራት ባካሄደው 13 የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ከ1.3 ትሪሊዮን በላይ ብር ከገበያው መሰብሰቡን ተናገረ።
ጥር 25/2018 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባለፉት 6 ወራት ባካሄደው 13 የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ከ1.3 ትሪሊዮን በላይ ብር ከገበያው መሰብሰቡን ተናገረ። ላኪዎች፣ በዶላር ቤት የሚያከራዩ፣ በህጋዊ መንገድ ዶላር የሚያገኙ ሁሉ ያለ ገደብ ዶላራቸውን በባንክ ማስቀመጥና በፈለጉ ጊዜ መጠቀም እንዲችሉ ይደረጋል ተብሏል። ባንኩ ይህን የተናገረው የራሱን እና የተጠሪ ተቋማትን የ6 ወራት የስራ ክንውን ሪፖርት ዛሬ በፓርላማው ቀርቦ ለፕላን ፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሲያቀርብ ነው። ብሔራዊ ባንክ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ከሚሰራቸው ስራዎች ውስጥ አንዱ ዶላርን ለባንኮች በጨረታ እያቀረበ ብርን ከገበያው መሰብሰብ እንደሆነ ተናግሯል፡፡ በፓርላማ ተገኝተው ሪፖርቱን በንባብ ያቀረቡት የብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር
Feb 21 min read


ኢትዮጵያ ከዩሮ ቦንድ አበዳሪዎች ጋር በመርህ ደረጃ ስምምነት ላይ ደርሳበት የነበረው የብድር ሽግሽግ ሳይሳካ ቀረ፡፡
ጥር 22/2018 ኢትዮጵያ ከዩሮ ቦንድ አበዳሪዎች ጋር በመርህ ደረጃ ስምምነት ላይ ደርሳበት የነበረው የብድር ሽግሽግ ሳይሳካ ቀረ፡፡ የብድር ሽግሽጉን በተመለከተ ኢትዮጵያ አለም አቀፍ ጠበቃ ቀጥራ ከዩሮ ቦንድ አበዳሪዎች ጋር ንግግር ስታደርግ መቆየቷ ይታወሳል፡፡ ከሳምንታት በፊትም በመርህ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንም አሳውቀው ነበር፡፡ ይሁንና ስምምነታቸው ስራ ላይ ይውል ዘንድ የአለም አቀፉን የገንዘብ ድርጅት IMF እና የቡድን 20 ሃገራት የአበዳሪዎች ኮሚቴ ይሁንታ ሲጠበቅ ቆይቷል፡፡ ታዲያ የቡድን 20 ሃገራት የአበዳሪዎች ኮሚቴ እንዳለው ኢትዮጵያ ከወጭ ንግድ የምታገኘው ገቢ IMF ከተነበየው በላይ ከሆነ ከምታገኘው ገቢ 2 ነጥብ 75 በመቶ ለዩሮ ቦንድ አበዳሪዎች በተጨማሪነት እንድትከፍል የሚጠይቀው የስምምነት አካል ኢትዮጵያ ብትስማማበትም
Jan 301 min read


ኢቲኬር የስፓይሩሊና ምግብ አጋዥ እና የውበት መጠበቂያ ምርቶችን እንዲያመርት ፍቃድ ተሰጠው።
ጥር 22/2018 ኢቲኬር የስፓይሩሊና ምግብ አጋዥ እና የውበት መጠበቂያ ምርቶችን እንዲያመርት ፍቃድ ተሰጠው። ስፓይሩሊና በያዘው ከፍተኛ ፕሮቲን እንደ አጋዥ ምግብ ወይንም ሰፕልመንት የሚመርጥ እንዲሁም ለውበት መጠበቂያነት የሚያገለግለውና በውሃ አካላት ላይ የሚገኘውን አልጌ ነው። ኢቲ ኬራ ስፓይሩሊና አልጌን ለአጋዥ ምግብነትም ፣ ለውበት መጠበቂያም አድርጎ እንዲያመርት የመጠቀሚያ ፈቃድ የሰጠው የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ነው፡፡ ይህን ስምምነትም በዛሬው እለት በኢቲኬር ፕሮዳክት መስራችና ባለቤት አቶ ማቲዮስ መባ እና የብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዮት ብርሃኑ (ዶ/ር) መካከል ተፈርሟል። ስፓይሮሊና አልጌን የመሳሰሉ የብዝሃ ሕይወቶችን ለመጠቀም ፣ ለማምረት ፍቃድ ያስፈልጋል፡፡ የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲት
Jan 301 min read
የኤሌክትሪክ ሀይል አጠራቅሞ በመያዝ የሀይል ማቋረጥ በሚያጋጥም ጊዜ የኤሌክትሪክ አገልግሎት መስጠት የሚችል አሰራር ሊጀመር ነው፡፡
ጥር 19/2018 የኤሌክትሪክ ሀይል አጠራቅሞ በመያዝ የሀይል ማቋረጥ በሚያጋጥም ጊዜ የኤሌክትሪክ አገልግሎት መስጠት የሚችል አሰራር ሊጀመር ነው፡፡ በአንድ የሃገር በቀል ተቋም እና በቻይና ኩባንያ መካከል በፈረመው ስምምነት መሰረት በታዳሽ ሀይል በሚሰራ ባትሪ ስራው ይከናወናል ተብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ምንታምር ፀጋው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx X :- https://x.c
Jan 271 min read


ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚካሄደው የግብርና ስራ በየዓመቱ የሚያስፈልገው አጠቃላይ ብድር 2.5 ትሪሊዮን ነው፡፡
ጥር 18/2018 ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚካሄደው የግብርና ስራ በየዓመቱ የሚያስፈልገው አጠቃላይ ብድር 2.5 ትሪሊዮን ነው፡፡ አሁን ላይ በዓመት እየቀረበ ያለው 52 ቢሊዮን ብር ነው፡፡ ለማዳበርያ ከንግድ ባንክ እየቀረበ ያለውን ብድር ሳይካተት፡፡ ይህም ማለት ግብርናው ከሚፈልገው ብድር አኳያ እየቀረበ ያለው እዚህ ግባ የሚባል አለመሆኑ ነው፡፡ መንግስት በቅርቡ ይፋ ያደረገው ሀገር አቀፍ የግብርና ፍኖተ ካርታ ከ4 ዓመት በኋላ ለግብርናው ዘርፍ በየአመቱ መቅረብ የሚገባው ብድር መጠን 880 ቢሊዮን ብር ለማድረስ አቅዷል፡፡ በግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የዲጂታል ፋይናሻል ሰርቪስ ፕሮግራም ቡድን መሪው አቶ አወት ተኬኤ የፋይናንስ ዘርፉ ለግብርናው በቂ ብድር የማያቀርበው ዘርፉን በቅጡ ባለመረዳት ነው፡፡ በተለይም የግል ፋይናስ ተ
Jan 261 min read


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከፍተኛ የተባለ የግማሽ ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ልዩ ጨረታ ሊያካሂድ ነው፡፡
ጥር 18/2018 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከፍተኛ የተባለ የግማሽ ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ልዩ ጨረታ ሊያካሂድ ነው፡፡ ነገ አካሂደዋለሁ ብሎ ባወጣው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ 500 ሚሊዮን ዶላር ለባንኮች አቀርባለሁ ብሏል፡፡ የዛሬ ሳምንት ባካሄደው የ70 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ 15 ባንኮች አንድን ዶላር በአማካይ 154.9 ብር በሆነ ዋጋ ገዝተዋል፡፡ በዚህ ጨረታ የባንኮች ፍላጎት 94.7 ሚሊዮን ዶላር ማግኘት የነበረ ሲሆን በጊዜው ብሔራዊ ባንክ ካቀረበው 70 ሚሊዮን ዶላር ጋር ሲነፃፀር ከ24 ሚሊዮን ዶላር በላይ ክፍተት እንዳለው ያሳያል፡፡ ይህም በባንኮች ዘንድ ከፍ ያለ የውጭ ምንዛሬ ፍላጎት መኖሩን ያሳያል፡፡ በጥቁር ገበያው እና በመደበኛው የምንዛሬ ገበያ መካከል ያለው ልዩነትም እንደታሰበው መጥበብ አልቻለም፡፡ የተጠቀሱትን ክፍተቶች ከግምት በማስገባ
Jan 261 min read


ዳሸን ባንክ ከአንድ ዓመት በፊት ባስጀመረው የሴቶች የአቅም ግንባታ መርሀ ግብር ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት አካሄደ።
ጥር 14/2018 ዳሸን ባንክ ከአንድ ዓመት በፊት ባስጀመረው የሴቶች የአቅም ግንባታ መርሀ ግብር ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት አካሄደ። በተለያዩ የስራ ዘርፎች የተሰማሩ ሴት ሰራተኞቹን አቅም ለማጎልበትና ወደከፍተኛ የአመራር ሃላፊነቶች ለማሳደግ ያለመውና ለአንድ ዓመት ያህል ሲተገበር በቆየው አጠቃላይ የሴቶችን አቅም የማጎልበት መርሃ-ግብር (Comprehensive Women Empowerment Program) ላይ ያተኮረ ውይይት አካሂዷል። ባንኩ ከአንድ አመት በፊት የሴቶች አቅም ግንባታ መርሃ ግብርን ማስጀመሩ ይታወሳል። በአንድ አመት ጊዜም ከ140 በላይ የሚሆኑ ሴት የባንኩ ባልደረቦች በዚህ መርሃግብር የመሳተፍና በተለያዩ መንገዶች አቅማቸውን የማጎልበት እድል አግኝተዋል ብሏል። በዚህ መርሃ-ግብር በአንድ ዓመት ሶስት የትስስርና ውይ
Jan 221 min read


በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ከሳምንት በኋላ በሚከበረው የጥምቀት በዓልም የተሻለ የቱሪስት ፍሰት እንደሚኖር ዝግጅት ተደርጓል፡፡
ጥር 5/2018 ከፍ ያለ የውጭ ቱሪስት ከሚገኝባቸውና የሀገር ውስጥ ቱሪዝም እንቅስቃሴም ሞቅ ከሚልባቸው ሃይማኖታዊ በዓላት መካከል የጥምቀት በዓል አንዱ ነው፡፡ በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ከሳምንት በኋላ በሚከበረው የጥምቀት በዓልም የተሻለ የቱሪስት ፍሰት እንደሚኖር ዝግጅት ተደርጓል፡፡ በቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎች ለቱሪስቶች የተሻለ የትራንስፖርት አማራጭ እንዲኖርና ለብዙዎችም ጊዜያዊ የስራ እድል እንዲፈጠር እየተሰራ ነው ተብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. በረከት አካሉ YouTube : https://url-shortener.me/2DTR Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 Facebook፡ https://url-shortener.me/2DTY WhatsApp : https://url-shortener.me/2D
Jan 131 min read


10 ቢሊዮን ዶላር ወጪ የሚጠይቀው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ተጀመረ።
ጥር 2/2018 10 ቢሊዮን ዶላር ወጪ የሚጠይቀው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ተጀመረ። ግንባታውን ያስጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ናቸው፡፡ የቢሾፍቱ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ፕሮጀክት ይሆናል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስረድተዋል። ይኽም ከኢትዮጵያ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ሪፎርም፣ የኢንደስትሪ ማስፋፊያ አጀንዳ እና የረጅም ዘመን የአቪየሽን ስትራቴጂ ጋር የተናበበ ነውም ሲሉም አክለዋል። ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድን አለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያጠናክራል። በAfCFTA ማህቀፍ የአፍሪካን የማገናኘት አቅም ይጨምራል ተብሏል። ከአዲስ አበባ ደቡብ ምስራቅ 40 ኪሎሜትር አካባቢ የምትገኘውና 1910 ሜትር ከፍታ ያላት ቢሾፍቱ ለአውሮፕላኖች ሥራ የተመቸ ከባቢ ያላት ሲሆን
Jan 101 min read


የታህሳስ ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 9.7 በመቶ ሆኗል ሲል የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ተናገረ።
ጥር 1/2018 የታህሳስ ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 9.7 በመቶ ሆኗል ሲል የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ተናገረ። የታህሳስ 2018 ዓ.ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት መጠን 9.7 በመቶ ደርሷል፤ ይህም በታህሳስ 2017 ዓ.ም ከተመዘገበው 17.0 በመቶ ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ ቅናሽ አሳይቷል ሲል ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል። የወር ከወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት በታህሳስ 2018 ዓ.ም በ0.3 በመቶ የቀነሰ ሲሆን፤ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ጋር ሲነጻጸር የ0.8 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች የዋጋ ግሽበት 9.8 በመቶ የደረሰው በዋናነት የአትክልት፣ የሥጋ፣ የስኳር እና የጣፋጭ ምግቦች፣ የወተት ተዋጽኦዎች፣ የፍራፍሬ፣ የዘይትና የቅባት እንዲሁም የሌሎች የምግብ ሸቀጦች ዋጋ በመጨመሩ ነው። በሌላ በኩል የዳቦ እና የጥራጥ
Jan 91 min read
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ኢንተርፕራይዝ እንዲያቋቁሙ መፈቀዱ እራሳቸውን በገንዘብ እንዲችሉ ያግዛል ተባለ፡፡
ጥር 1/2018 የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ኢንተርፕራይዝ እንዲያቋቁሙ መፈቀዱ እራሳቸውን በገንዘብ እንዲችሉ ያግዛል ተባለ፡፡ ይህም የሚሰጡት ስልጠና ጥራት እንዲኖረው ይረዳል ሲሉ ያነጋገርናቸው የዘርፉ ባለሙያ ጠቅሰዋል፡፡ ባለፈው አመት የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ ወጥቶ ወደ ስራ ገብቷል፡፡ ፖሊሲው ውስጥ ከተካተቱ ጉዳዮች አንዱ ቴክኒክና ሙያ ተቋማት እራሳቸውን በፋይናንስ እንዲችሉ ማድረግ ነው፡፡ ለዚህም የተለያዩ አማራጮችን ያስቀመጠ ሲሆን ኢንተርፕራይዝ አቋቁመው በሚያሰለጥኑበት ዘርፍ የንግድ አገልግሎት እንዲሰጡ ይፈቅዳል፡፡ በሚዛን የግብርና ኮሌጅ የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ተጠሪ አቶ ካሳሁን አይከን ይሄ ለተቋማቱ ምን ይዞላቸው ይመጣል? ስንል ጠይቀናቸዋል። አቶ ካሳሁን የስልጠና ጥራት እንዲኖር ፣ በፋይናንስ እራሱን የቻለ
Jan 91 min read
በኢትዮጵያ አብዛኛው የፋይናንስ ተቋም አሰራሩ አንድ ዓይነት ነው።
ታህሳስ 27/2018 በኢትዮጵያ አብዛኛው የፋይናንስ ተቋም አሰራሩ አንድ ዓይነት ነው። በተለይ በዓል በመጣ ግዜ ፤ በዓሉን ታሳቢ በማድረግ የብድር አገልግሎት የሚሰጡ የፋይናንስ ተቋም ቁጥራቸው ቢጨምር ፤ አንዛኛውን ሰው በፋይናንስ ለማካተት አንደኛው መንገድ ይሆናል ይባላል። በበዓል ወቅት እና የማህበራዊ አገልግሎት ጊዜ ለአንድ ቀንም ቢሆን አስቸኳይ የፋይናንስ አቅርቦት ለማግኘት አብዛኛው የፋይናንስ ተቋም ብድር ሲሰጥ አይታይም፡፡ ይሁንና የማህበራዊ እና የበዓል ሰሞን ወጭዎችን ለመሸፈን የሚያስፈልግ የፋይናንስ አስቸኳይ ብድር አገልግሎት ስራ መጀመሩን ሰምተናል፡፡ ይህ የፋይናንሰ አቀባይ ምንዳ የገንዘብ ቁጠባና ህብረት ስራ ማህበር ይባላል። ደንበኞች ይህን አገልግሎት በአጭሩ እንዴት ያገኙታል? ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ተህቦ ንጉ
Jan 51 min read


የይዞታ ማረጋገጫ ሳይኖር፤ የንብረት ታክስ እንዲከፈል የሚያስገድደው ረቂቅ አዋጅ
ታህሳስ 27/2018 መንግስት የባለቤትነት መብት የሌላቸው ሰዎች የይዞታ ማረጋገጫ ባይኖራቸውም የንብረት ታክስ እንዲከፍሉ የሚያስገድድ ረቂቅ አዋጅ እያሰናዳ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ ለመሆኑ የባለቤትነት መብት በሌለበት ሁኔታ ለይዞታ የንብረት ታክስ እንዲከፈል ማድረግ ምን ያክል ትክክለኛ አካሄድ ይሆናል? የንብረት ታክስ የሚከፍለው ግለሰብስ በሂደት መብት እንዲፈጠርለት አያደርግም ወይ? የሚል ጥያቄም ይነሳል፡፡ የህግ ባለሞያ አነጋግረናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ንጋቱ ረጋሣ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw Telegram : https://t.me/S
Jan 51 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

