top of page


የሜትር ታክሲ አገልግሎት አቅራቢው ''ያንጎ'' ከአዲስ አበባ ውጪ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀዋሳ ከተማ ሥራ በመጀመሩ ተሰማ።
ሰኔ 1/2018 የሜትር ታክሲ አገልግሎት አቅራቢው ''ያንጎ'' ከአዲስ አበባ ውጪ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀዋሳ ከተማ ሥራ በመጀመሩ ተሰማ። በሀዋሳ ባጃጅ፣ ባለ4 እግር ባጃጅ እና የሞተር ሳይክል አገልግሎቶች አሁን በያንጎ መተግበሪያ ላይ አሉ የተባለ ሲሆን፤ ተሳፋሪዎች በመጀመሪያዎቹ ሦስት ጉዞዎቻቸው 30 በመቶ በመቶ ቅናሽ ያገኛሉ ተብሏል። ያንጎ ሀዋሳ ከኤልና ትሬዲንግ እና ኮንትራስት ትሬዲንግ ጋር በመተባበር መቅረቡን ኩባንያው ከላከልን መግለጫ ላይ ተመልክናል። ያንጎ በሀዋሳ ሁለት አይነት ተሽከርካሪዎችን በሁለት የታሪፍ ክፍሎች ሥራውን ጀምሯል ተብሏል። አንደኛው“ባጃጅ ታሪፍ” የተባለ ሲሆን ይህም ሁለት ልዩ ባለ ሦስት ጎማ ተሽከርካሪዎችን ማለትም ባለ 3 እና 4 እግር ባጃጆችን ያካትታል ተብሏል። ሁለተኛው አማራጭ “ሞቶ ታሪፍ” የሚባል ሲሆን ይ
Jun 81 min read


የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ
ግንቦት 27/2018 ዛሬ በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት በቀረበው የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ በግብር ከፋዮችንና በግብር ሰብሳቢውን መስሪያ ቤቱ መካከል አለመስማማት በተፈጠረ ጊዜ የሚያስማማ የግልግል ዳኝነት እንዲኖር መደንገጉ ድርጅቶችን ከመዘጋት የሚያድን መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ተናገሩ፡፡ በገለልተኝነት የግልግል ዳኝነት እንዲሰጡ የሚመጠሩ ሰዎችን በተመለከተ ግን አመራረጡ ላይ ጥንቃቄ ይፈልጋል ብለዋል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ያሬድ እንዳሻው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp :..
Jun 41 min read
የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን የገንዘብ ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል፡፡
ግንቦት 17/2018 የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን የገንዘብ ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል፡፡ ከመካከሉ ከ33 ቢሊዮን ዶላር በላዩ የውጭ እዳ ሲሆን 18.3 ቢሊዮን ዶላሩ ደግሞ ከሃገር ውስጥ የተወሰደ ብድር ነው፡፡ ለመሆኑ የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር ከሌሎች አገራት አንፃር ሲታይ ከፍተኛ ፣ መካከለኛ ወይስ ዝቅተኛ ? ሀገሪቱ አሁን ያለችበት የኢኮኖሚ አቅምስ ያለባትን እዳ ለመክፈል የሚያስችላት ይሆን? የምጣኔ ሃብት በለሞያ የሆኑት አቶ ክቡር ገና የኢትዮጵያ እዳ ከሌሎች አገራት ጋር ሲተያይ ከፍተኛ የሚባል እንዳልሆነ ጠቅሰው የመክፈል አቅሟ ግን "በጣም ደካማ ስለሆነ ጫናው በጣም ከፍ ብሎ ይታያል፣ ለመክፈልም አስቸጋሪ ነው ይላሉ፡፡ የአገር ውስጥ እዳው በኢትዮጵያ ብር ሲመለስ ወደ 3 ትሪሊዮን እንደሚሆን እንዲሁም የውጭ ብድሩ ደግሞ
May 251 min read
አቢሲንያ ባንክ ˝እችላለሁ˝ 5ኛ ዙር የ2025 BYD Seagull ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪና የሎተሪ እድለኛን ለመለየት የእጣ ማውጠት ስነ ስርዓት አከናወነ፡፡
ሚያዝያ 22/2018 አቢሲንያ ባንክ ˝እችላለሁ˝ 5ኛ ዙር የ2025 BYD Seagull ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪና የሎተሪ እድለኛን ለመለየት የእጣ ማውጠት ስነ ስርዓት አከናወነ፡፡ ዛሬ በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት መድረክ ከ2.3 ሚሊዮን በላይ የኩፖን ቁጥሮችን መሠረት በማድረግ የ2025 BYD Seagull ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪና ዕድለኛን ለመለየት የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል፡፡ አቢሲኒያ ባንክ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን (March 8) በማስመልከት፣ “እችላለሁ ” በሚል መሪ ቃል ለ5ኛ ጊዜ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ አቅም የሚያጎለብት መርሐ-ግብር ማካሄዱ ይታወሳል፡፡ ባንኩ ባሰናዳው መርሀ ግብር ላይም በደም እጥረት ምክንያት የሚከሰተውን የእናቶች ሞት ለመቀነስ፣ ሀገር አቀፍ የደም ልገሳ ዘመቻ ያከናወነ ሲሆን በዚህም 3,012 ዩኒት ደም መሰብሰብ
Apr 301 min read
በኢትዮጵያ በፋይናንስ ተቋሞች የተከፈተ የቁጠባ ሂሳብ ቁጥር ከ176 ሚሊየን በላይ ደርሷል።
ሚያዝያ 20/2018 በኢትዮጵያ በፋይናንስ ተቋሞች የተከፈተ የቁጠባ ሂሳብ ቁጥር ከ176 ሚሊየን በላይ ደርሷል። ከዚህ የባንክ ሂሳብ 97 በመቶው ግን ከ100 ሺህ ብር በታች ገንዘብ የተቀመጠበት መሆኑ ተነግሯል። በኢትዮጵያ የፋይናንስ ተቋሞች በኪሳራ ምክንያት ቢዘጉ ገንዘቡን የቆጠበው ሰው ያስቀመጠውን እንዳያጣ ለመካስ በሚል የተቋቋመው የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ስራ ከጀመረ ሶስት ዓመት ሆኖታል። ፈንዱ በዚህ ጊዜ ከባንኮችና ሌሎች የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት የሰበሰበው የአረቦን ገንዘብ ከ20 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱ ተነግሯል። ከጠቅላላ አረቦኑ አብዛኛው ወይም 10.41 ቢሊዮን ብሩ ከግል ባንኮች የተሰበሰበ እንደሆነ ፈንዱ ከላከልን መረጃ ላይ ተመልክተናል። 9.96 ቢሊዮን ብሩ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፤ ቀሪው 0
Apr 281 min read


ኢትዮጵያ እና ቻይና ባለፈው ዓመት 8.5 ቢሊዮን ዶላር የንግድ ልውውጥ አድርገዋል፡፡
ሚያዝያ 20/2018 ኢትዮጵያ እና ቻይና ባለፈው ዓመት 8.5 ቢሊዮን ዶላር የንግድ ልውውጥ አድርገዋል፡፡ ከዚህ ውስጥ 8 ቢሊዮን ዶላሩ ቻይና ወደ ኢትዮጵያ ሸቀጦቿን ልካ ያገኘቺው ገቢ ሲሆን ቀሪው 5 መቶ ሚሊዮን ዶላሩ የኢትዮጵያ ምርቶች በቻይና ገበያ ያወጡት ዋጋ ነው፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የንግድ ሚዛን ልዩነቱ እጅግ ሰፊ ነው፡፡ የሁለቱ ሀገራት የንግድ ትስስር የበለጠ እንዲጠብቅ ካደረጉ ማህበራት መካከል የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክርቤት ቀዳሚው እንደሆነ ይነገራል፡፡ የምክር ቤቱ ምክትል ዋና ፀሀፊ አቶ ካሳሁን ማሞ የሁለቱ ሀገራት የንግድ ትስስር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን ይናገራሉ፡፡ የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ቻይና ከሚገኙ የተለያዩ የንግድ ማህበራት ጋር የጋራ ስምምነት እየተዋዋለ መሆኑን የ
Apr 281 min read


የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ግሪን ሞሽን አብረው ለመስራት ተስማሙ።
ሚያዝያ 14/2018 የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በኢትዮጵያ ገበያም የገባው የእንግሊዙ ግሪንሞሽን የመኪና ኪራይ አገልግሎት ሰጪ ኩባንያ ግሪን ሞሽን አብረው ለመስራት ተስማሙ። በስምምነቱ መሰረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሼባ ማይልስ ደንበኞች በአለም ዙሪያ የሚገኙ የግሪን ሞሽን መኪና ኪራይ ሲጠቀሙ ተጨማሪ ማይልስ ያገኛሉ። በዚህም የግሪን ሞሽን የመኪና ኪራይ ተጠቃሚ አንድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሼባ ማይልስ ደንበኛ ለሚያወጣው አንድ ዶላር አንድ ማይል ያገኛል ተብሏል። ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….. ንጋቱ ሙሉ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shortur
Apr 221 min read


በቁም እንስሳት ሃብቷ ከአፍሪካ ቀዳሚ መሆኗ በሚነገርላት ኢትዮጵያ፤ የስጋ ምርት ለምን እንዲህ ተወደደ?
ሚያዝያ 8/2018 በቁም እንሰሳት ሃብቷ ከአፍሪካ ቀዳሚ መሆኗ የሚነገርላት ኢትዮጵያ የስጋ ምርት እንደልብ የማይገኝባት፣ ቢገኝም እንኳን የዋጋው ነገር ለብዙዎች የማይቀመስ በመሆኑ ’’ስጋ’’ የመግዛት አቅም ያላቸው ብቻ የሚያገኙት መሆኑ ተደጋግሞ ይነሳል፡፡ በተለይ ልኳንዳ ነጋዴዎች የስጋ ምርት ላይ በሚጣለው አግባብ ያልሆነና ተደራራቢ ግብር ምክንያት ስጋ እንዲወደድ፣ ነጋዴውም ጫና ውስጥ እንዲገባ ሆኗል ይላሉ፡፡ የአዲስ አበባ ልኳንዳ ነጋዴዎች ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ አየለ ሳህሌ የስጋን ግብር በተመለከተ ከዛሬ 10 ዓመት ጀምሮ ቅሬታችንን ስናቀርብ ቆይተናል ይሁንና እስካሁን ይህ ነው የሚባል ምላሽ አልተሰጠንም ብለውናል፡፡ የገቢ ሰብሳቢው መስሪያ ቤት የልኳንዳ ቤቶችን ግብር የሚያሰላው በሬው የሚመዝነውን ኪሎ በመውሰድ 1 ኪሎ ስጋ ከሚሸጥበት ዋጋ ጋር
Apr 162 min read


የሩሲያው የኢ-ኮሜርስ ንግድ ስርዓት መድረክ ዋይልድቤሪስ (Wildberries) ለኢትዮጵያ ገበያም በሩን ክፍት ሊያደርገ ነው፡፡
ሚያዝያ 7/2018 የሩሲያው የኢ-ኮሜርስ ንግድ ስርዓት መድረክ ዋይልድቤሪስ (Wildberries) ለኢትዮጵያ ገበያም በሩን ክፍት ሊያደርገ ነው፡፡ ይህም በአፍሪካ ኢትዮጵያን የመጀመሪያው መዳረሻው ስትሆን በአለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ 11ኛዋ ያደርጋታል ተብሏል፡፡ የዋይልድቤሪስ በኢትዮጵያ መስራት መጀመር ሸማቾች ከአትዮጵያ በቀጥታ እንደ ቡና፣ ጨርቃጨርቅ፣ የቆዳ ውጤቶች፣ መገልገያዎች ፣ የቤት እቃዎች እና የተፈጥሮ መዋቢያዎች ያሉ ምርቶችን በቀጥታ እንዲሸምቱ ያስችላቸዋል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ በመጀመሪያው ምዕራፍ ኢትዮጵያዊያን ነጋዴዎች ምርቶቻቸውን ለሩሲያ ደንበኞች እንዲያቅርቡ ይስችላቸዋል ተብሎሏል፡፡ ወደፊት ደግሞ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያላቸው ምርቶችን ለኢትዮጵያ ሸማቾች በማምጣት የንግድን ዘርፉን የማሳደግ እቅድ አለ ተብሎ ተነግሯል። ለነጋዴዎች የ
Apr 152 min read


በቀን እስከ 50 ሺህ ስኩዌር ሜትር ወይም ከ40 እስከ 45 ኮንቴነር ሴራሚክ ማምረት የሚችል ፋብሪካ ከ3 ሳምንት በኋላ ምርት ይጀምራል ተባለ።
መጋቢት 28/2018 በቀን እስከ 50 ሺህ ስኩዌር ሜትር ወይም ከ40 እስከ 45 ኮንቴነር ሴራሚክ ማምረት የሚችል ፋብሪካ ከ3 ሳምንት በኋላ ምርት ይጀምራል ተባለ። በ50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ኢንቨስትመንት ከአዲስ አበባ 65 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው በቱለፋ ከተማ የተገነባው ይህን ፋብሪካ የገነባው ባይጂያ ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ የተባለ ድርጅት ነው። በ30 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ የሴራሚክ እና የፖርስሊን ምርቶች ፋብሪካ ምርት ሲጀምር ብቻውን አሁን ካለው የሴራሚክ ፍላጎት እስከ 70 በመቶ ድረስ የማቅረብ አቅም አለው ተብሎለታል። በባይጂያ ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ የሚመረቱን ምርቶች ለገበያ የሚያቀርበው ማንሰን ኢንቨስትመንትስ ነው። የማንሰን ኢንቨስትመንትስ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳዊት እርገቱ እና የባይጂያ ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ ዋና
Apr 61 min read


ዳሸን ባንክ ልዩ የሱፐር አፕ ማስተዋወቅ ውድድር ሽልማትን ጨምሮ አራት አዳዲስ አገልግሎቶችን ዛሬ አስጀመረ።
መጋቢት 24/2018 ዳሸን ባንክ ልዩ የሱፐር አፕ ማስተዋወቅ ውድድር ሽልማትን ጨምሮ አራት አዳዲስ አገልግሎቶችን ዛሬ አስጀመረ። ባንኩ የሱፐር አፕ ተጠቃሚዎችን ለማበረታት እንዲሁም የአገልግሎቱን ተደራሽነት ለማስፋት የቲክቶክ ይዘት ፈጠራ ውድድር ማዘጋጀቱን ይፋ አድርጓል። በዚህ ውድድር ለሚያሸንፉ የይዘት ፈጣሪዎች በድምሩ ስድስት ሚሊዮን ብር የገንዘብ ሽልማት እንዳዘጋጀ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የንግድ ሥራ ትምህርት ቤት (ኮሜርስ) በተዘጋጀ ስነ ስርአት ላይ ተነግሯል። በዳሸን ሱፐር አፕ ቲክቶክ ቻሌንጅ አሸናፊ ለመሆን ይዘት ፈጣሪዎች ስለ ዳሸን ባንክ ሱፐር አገልግሎቶች የሚገልፅ የቲክቶክ ቪዲዮ በመስራት ማጋራት ይጠበቅባቸዋል ተብሏል። የሰሩት ቪዲዮ በቲክቶክ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዕይታ ሲያገኝ፣ በዳሸን ሱፐር አፕ ውስጥ በሚገኘው የዳሸን ክሬቲቭ አ
Apr 21 min read


ቪዛ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለ ቪዛ ካርድ ደንበኞች የ2026 የዓለም ዋንጫን በአካል ተገኝተው የሚመለከቱበትን ዕድል ይዘው መቅረባቸውን ተናገሩ።
መጋቢት 24/2018 ቪዛ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለ ቪዛ ካርድ ደንበኞች የ2026 የዓለም ዋንጫን በአካል ተገኝተው የሚመለከቱበትን ዕድል ይዘው መቅረባቸውን ተናገሩ። ዕድሉ የምድብ ጨዋታዎችን በአካል ለመመልከት የሚያስችል መሆኑ ተነግሯል። ይህ ከመጋቢት 5 እስከ ሚያዝያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ንቅናቄ፣ በመላው ኢትዮጵያ ለሚገኙ የባንኩ የዴቢትም ሆነ የቅድመ ክፍያ ቪዛ ካርድ ተጠቃሚዎች በሙሉ ክፍት ነው ተብሏል። ደንበኞቹ በቪዛ ካርዳቸው የሚፈጽሙት እያንዳንዱ ግብይት እንደ አንድ ዕጣ ይቆጠራል የተባለ ሲሆን ለዚህ ምዝገባ አይጠየቅም ተብሏል። በቪዛ የምሥራቅ አፍሪካ ክላስተር ሓላፊ የሆኑት ያሬድ እንዳለ፣ የካርድ ተጠቃሚዎችን በየቀኑ እየፈጸሟቸው ለሚገኙ ግብይቶች ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ተባብረን በመሸለማችን ደስተኞች ነን'' ብለዋል።
Apr 21 min read


የእሳት እራት ተብሎ የሚጠራው ነፍሳት በኢትዮጵያ በአፅዋት ላይ ምንም ጉዳት የማያስከትል ቢሆንም አውሮፓ ከገባ ግን ከ100 በላይ የእፅዋት ዓይነቶችን ቀርጥፎ የሚበላ ሌላ ባህሪ ያለው ተባይ ይሆናል፡፡
መጋቢት 24/2018 የእሳት እራት ተብሎ የሚጠራው ነፍሳት በኢትዮጵያ በአፅዋት ላይ ምንም ጉዳት የማያስከትል ቢሆንም አውሮፓ ከገባ ግን ከ100 በላይ የእፅዋት ዓይነቶችን ቀርጥፎ የሚበላ ሌላ ባህሪ ያለው ተባይ ይሆናል፡፡ በዚህም ምክንያት ከአመታት በፊት በኢትዮጵያ የአበባ እርሻዎች ውስጥ መገኘቱን ተከትሎ የአውሮፓ ህብረት ተባዩ ከምርቱ ጋር ወደኛ እንዳይመጣብን የሚል ማሳሰቢያ ሰትቶ ነበር፡፡ የአበባ ምርት ወደ ህብረቱ እንዳይገባ ከመታገዱ በፊት ምን እርምጃ ተወሰደ፡፡ በእንግሊዝኛው ምህጻረ ቃል F C M የሚሰኘው ተባይ የቢራቢሮ ዝርያ ሲሆን በእኛ አገር የእሳት እራት በመባል ይታወቃል ። በሀገራችንአብዛኞቹ ዕፅዋት የዚህ ተባይ መኖሪያ ሆነው እንደሚያገለግሉ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ወንዳለ ሃብታሙ ነግረውናል፡፡
Apr 21 min read
በአይነቱ ልዩ የሆነ የሪል ስቴት ኤክስፖ በለንደን እንግሊዝ ከግንቦት 15 እስከ 17/2018 እንደሚካሄድ ተነገረ።
መጋቢት 22/2018 በአይነቱ ልዩ የሆነ የሪል ስቴት ኤክስፖ በለንደን እንግሊዝ ከግንቦት 15 እስከ 17/2018 እንደሚካሄድ ተነገረ። በእንግሊዝና አካባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው የመኖሪያ ቤት ማፍራት የሚችሉበትን ዕድል ለመፍጠር የተዘጋጀ ኤክስፖ ነው ተብሏል። በሪል ስቴት አልሚዎችና በተጠቃሚዎች መካከል ያለውን መተማመን ለማሳደግና አስተማማኝ በሆነ መንገድ ግብይቶች እንዲፈፅሙ የተዘጋጁ ስርዓቶችን ለማስተዋወቅ ያለመ መሆኑም ተጠቅሷል። በኤክስፖው ላይ ከሚመለከታቸው አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጋር በሚደረግ የመረጃ ልውውጥና የፓናል ውይይት በዘርፉ ስላሉ ችግሮች ይነሳል ተብሎ እንደሚጠበቅም ኤክስፖውን አስመልክቶ ከተዘጋጀ መግለጫ ላይ ተመልክተናል። ባንኮች በውጪ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የቢዝነስ ድ
Mar 311 min read


የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎች አሁን ላይ ከ45 በመቶ በላይ የሚሆነውን የሀገር ውስጥ ምርት ፍላጎት እየሸፈኑ ነው ተባለ።
መጋቢት 19/2018 የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎች አሁን ላይ ከ45 በመቶ በላይ የሚሆነውን የሀገር ውስጥ ምርት ፍላጎት እየሸፈኑ ነው ተባለ። እንደ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎች ከውጪ ይገቡ የነበሩትን ምርቶች እዚሁ በማምረት በከፊልም ቢሆን ፍላጎቱን እየሸፈኑ ነው። በዚህም ፋብሪካዎቹ ምርቶችን ወደ ተለያዩ ሀገራት በመላክ የውጭ ምንዛሪ ከማስገኘት ባሻገር የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ማሟላት ላይም ጥሩ ስራ እየሰሩ እንደሚገኙ መረዳት ይቻላል ሲሉ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ድኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ ተናግረዋል። ከአገልግሎት አሰጣጥ ፣ ከመሠረተ ልማት እና ብድር አቅርቦት ጋር የተገናኙ የፋብሪካዎቹ ችግሮች እንዲፈቱ የተደረገው ጥረት ውጤቶቹ እንዲገኙ አግዘዋል ብለዋል። የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ጋር በመተባበር በአዲስ አበ
Mar 281 min read


የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ለማሳደግ የተሰራው ስራ ውጤት እያመጣ ነው ሲል የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተናገረ።
መጋቢት 18/2018 የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ለማሳደግ የተሰራው ስራ ውጤት እያመጣ ነው ሲል የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተናገረ። ሚኒስቴሩ እንዳለው የፋብሪካዎቹ አማካይ የማምረት አቅም አሁን ላይ 66.3 በመቶ ደርሷል። ከ8ዓመት በፊት አማካይ የማምረት አቅማቸው 46 በመቶ እንደነበር የሚኒስቴሩ የመንግስት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ አበባ ታመነ ተናግረዋል። ከመሠረተ ልማት እና ጥሬ ዕቃ አቅርቦት እንዲሁም ከመንግስታዊ አገልግሎቶች ጋር የተያያዙ ችግሮች እንዲፈቱላቸው የተደረገው ጥረት የፋብሪካዎቹ የማምረት አቅም እንዲሻሻል ረድቷል ብለዋል። የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ጋር በመተባበር የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎችን የስራ ሃደት ከትናንት ጀምሮ የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ባለሞያዎች ተዘዋውረው እንዲመለከቱ
Mar 271 min read


የፕላስቲክ ቆሻሻን መልሰው ጥቅም ላይ ለሚያውሉ የገንዘብ እርዳታ ሊደረግላቸው ነው፡፡
መጋቢት 9/2018 የፕላስቲክ ቆሻሻን መልሰው ጥቅም ላይ ለሚያውሉ የገንዘብ እርዳታ ሊደረግላቸው ነው፡፡ ቆሻሻን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋሉ ዘርፍ ሴቶች እንዲሰማሩ ይበረታታሉ ብሏል፡፡ አለም አቀፍ የመልሶ ጥቅም ላይ የማዋል ቀንን ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ እያከበረች ነው። በየዓመቱ መጋቢት 9 ቀን ወይም እንደ እ.ኤ.አ ማርች 18 ቀን በአለም አቀፍ ደረጃ የሚከበረውን የመልሶ ጥቅም ላይ የማዋል ቀን ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ እየተከበረ መሆኑን ሰምተናል። "ቆሻሻ መልሶ ጥቅም ላይ መዋል የሚችል ሀብት ነው" በሚል መሪ ቃል እየተከበረ የሚገኘውን አለም አቀፍ ኩነትን መሰረት በማድረግ "ቆሻሻን ወደ ዕድል እንቀይር ሴቶችንና ወጣቶችን በኢኮኖሚ እናብቃ" በሚል ሀሳብም በአዲስ አበባ እየተከበረ ይገኛል። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ፔትኮ ኢትዮጵያ ከተባለ
Mar 181 min read


በሚቀጥሉት 4 ዓመታት ውስጥ 300 ሚሊዮን ዶላር ብድር ለአነስተኛ ማሳ ላላቸው ገበሬዎች ሊቀርብ መሆኑን ተነገረ፡፡
መጋቢት 9/2018 በሚቀጥሉት 4 ዓመታት ውስጥ 300 ሚሊዮን ዶላር ብድር ለአነስተኛ ማሳ ላላቸው ገበሬዎች ሊቀርብ መሆኑን ተነገረ፡፡ ይህ የሰማነው የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን እና ለእርሻ ድርጅት ባደረጉት አብሮ የመስራት ስምምነት ላይ ነው፡፡ ለእርሻ ደርጅት በሚቀጥሉት 4 ዓመታት አነስተኛ ማሳ ላላቸው ገበሬዎች ብድር ለማመቻቸት አቅዶ እየሰራ መሆኑን የተናገረ ሲሆን ከዚህ በፊት በሙከራ ደረጃ በሰራው ስራ ገበሬዎች ውጤታማ መሆናቸውን ተጠቅሷል፡፡ የለእርሻ ድርጅት ስራ አስፈፃሚ አቶ አብርሃም እንድርያስ በዚህ ዓመት ብቻ ለ65 ሺህ ገበሬዎች ብድር ለማቅረብ እቅድ መያዛቸውን የሚናገሩ ሲሆን ለስራውም ከተለያዩ ባንኮች ጋር እንደሚሰሩም አስረድተዋል፡፡ በሙከራ የስራ ወቅት ገበሬው በትክክል የሚፈልገው ብድር ከተሰጠው ያለምንም ችግር ብድሩን መክፈ
Mar 181 min read


በኢትዮጵያ የፋይናንስ ተቋማት የሚገላበጠው አብዛኛው ገንዘብ ወይም ከ73 በመቶ በላዩ የሚዟዟረው በዲጂታል መንገድ ነው፡፡
መጋቢት 8/2018 በኢትዮጵያ የፋይናንስ ተቋማት የሚገላበጠው አብዛኛው ገንዘብ ወይም ከ73 በመቶ በላዩ የሚዟዟረው በዲጂታል መንገድ ነው፡፡ በተያዘው የበጀት ዓመት በ6ት ወራት ውስጥ ብቻ 14.56 ትሪሊዮን ብር በዲጂታል መንገድ ተገላብጧል፡፡ ይህ በዲጂታል ገንዘብ ማስተላለፍ ጊዜን የሚቆጥብ፣ ምቹ መሆኑ ቢጠቀስም የአገልግሎት ክፍያውና ሌሎች ተቆራጮች መኖርና ለአጭበርባሪዎች የተጋለጠ ነው በሚልም ይወቀሳል፡ መንግስታዊ ተቋማት ለሚሰጡት አገልግሎት ክፍያቸውን ወደ ድርጅት ባንኪንግ ማዞራቸውን ተከትሎ ከማህበረሰቡ ለአገልግሎት እየተባለ የሚቆረጠው ገንዘብ እየበዛ መጥቷል፡፡ ደመወዝተኛውም ይሁን በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ለተለያዩ የክፍያ ስርዓቶች የሚያደርጉት የገንዘብ ልውውጥ ተደራራቢ ታክስ እንዲከፍሉ አያደርግም? በጉዳዩ ላይ
Mar 171 min read


ኢትዮዽያ በአለም የሎጅስቲክስ ሜዳ
የካቲት 27/2018 የሎጅስቲክስ ስራ ፍፁም የሰላም መስመር እና እውቀት ይፈልጋል፡፡ ሎጅስቲክስ በኢትዮጵያ እንዲዘምን፣ እንዲቀላጠፍ አሁንም ብርቱ ስራ ይጠይቃል። እቃዎችን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ለማንቀሳቀስ፣ መያዝ፣ ማከማቸት እና ማስተናገድ ፤ በየትኛውም የአለም መሮጫ ኮሪደር እና ባህር ማገላበጥ ፤ በአየር በየብስ ምድር ለመላወስ ጥንቅቅ ያለ የሎጅስቲክስ ስራ ይፈልጋል። ለዚህ ደግሞ በየጊዜው በአለም በሚደረጉ ጉባኤዎች እና የሎጅስቲክስ ማህበራት ላይ በኃላፊነት ቦታ መገኘት እንደሚያስፈልግ ይታመናል። በተለይ ከአፍሪካ ብቸኛው የአለም ፍሬይት ፎርዋርደርስ ማህበር ፊያታ የቦርድ አባል እና በ ኢትዮጵያም የማህበሩ ፕሬዝዳንት አቶ ዳዊት ውብሸት በዚህ ጉዳይ ስጋት እንዳላቸው ነግረውናል። ኢትዮዽያ በአለም የሎጅስቲክስ ሜዳ ፤ በጭነት መርከቦች እና አጠቃላ
Mar 61 min read


የኤ ኤፍ ጂ ኤርክራፍት ፋይናንስ ጀርመን (AFG) እህት ኩባንያ የሆነው ኤ ኤፍ ጂ አቪየሺን አየርላንድ ኩባንያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው አፍሪካ ሀገራት መግባቱን ተናገረ።
የካቲት 24/2018 በአውሮፕላን ንግድና ሀብት አስተዳደር የሚታወቀው ኤ ኤፍ ጂ ኤርክራፍት ፋይናንስ ጀርመን (AFG) እህት ኩባንያ የሆነው ኤ ኤፍ ጂ አቪየሺን አየርላንድ ኩባንያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው አፍሪካ ሀገራት መግባቱን ተናገረ። ኩባንያው ለአፍሪካ ስራው ሲልም ሁለት ከፍተኛ ባለሞያዎቹን በአፍሪካ ተገኝተው እንዲሰሩ እንደመደባቸው ባወጣው መግለጫ ተናግሯል። AFG አቪዬሽን አየርላንድ የናይጄሪያው ካሊ ኤር ሁለት CRJ1000 አውሮፕላኖች ባለቤት እንዲሆን ማስቻሉን ተናግሯል። በዚህም የተነሳ የአፍሪካ ሀገራት አየር መንገዶች፣ አፕሬተሮች፣ የመንግሥት እና የአቪዬሽን ዘርፍ ሀላፊዎች ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለቸው ተረድቻለሁ ብሏል። ይህ ፍላጎት የአፍሪካ የአቪዬሽን ዘርፍ በአለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እየተቀየረ መምጣቱን ያሳል ሲልም ኩ
Mar 42 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

