top of page


''መስከረም ጀምሮ ከ77,000 በላይ ኢትዮጵያዊያን፤ ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል'' የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር
ሰኔ 1/2018 ዘንድሮ መስከረም ወር ጀምሮ ከ77,000 በላይ ኢትዮጵያዊያን፤ ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል ሲል የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ፡፡ በትናንትናው እለትም በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያሉ 1,722 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል ተብሏል። በሳምንቱ ውስጥ በተደረገ 10 ዙር በረራ የተመለሱት 1,666 ወንዶች እና 48 ሴቶች እንዲሁም 8 ህፃናት ሲሆኑ ከእነዚህ ውስጥ 27 ተመላሾች ደግሞ እድሜያቸው ከአስራ ስምንት ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ይገኙበታል። መስከረም 5/ 2018 በተጀመረው ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ስራ እስካሁን ከ77,000 በላይ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገር መመለስ ተችሏል። ሚኒስቴሩ ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ የማ
Jun 81 min read


የሜትር ታክሲ አገልግሎት አቅራቢው ''ያንጎ'' ከአዲስ አበባ ውጪ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀዋሳ ከተማ ሥራ በመጀመሩ ተሰማ።
ሰኔ 1/2018 የሜትር ታክሲ አገልግሎት አቅራቢው ''ያንጎ'' ከአዲስ አበባ ውጪ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀዋሳ ከተማ ሥራ በመጀመሩ ተሰማ። በሀዋሳ ባጃጅ፣ ባለ4 እግር ባጃጅ እና የሞተር ሳይክል አገልግሎቶች አሁን በያንጎ መተግበሪያ ላይ አሉ የተባለ ሲሆን፤ ተሳፋሪዎች በመጀመሪያዎቹ ሦስት ጉዞዎቻቸው 30 በመቶ በመቶ ቅናሽ ያገኛሉ ተብሏል። ያንጎ ሀዋሳ ከኤልና ትሬዲንግ እና ኮንትራስት ትሬዲንግ ጋር በመተባበር መቅረቡን ኩባንያው ከላከልን መግለጫ ላይ ተመልክናል። ያንጎ በሀዋሳ ሁለት አይነት ተሽከርካሪዎችን በሁለት የታሪፍ ክፍሎች ሥራውን ጀምሯል ተብሏል። አንደኛው“ባጃጅ ታሪፍ” የተባለ ሲሆን ይህም ሁለት ልዩ ባለ ሦስት ጎማ ተሽከርካሪዎችን ማለትም ባለ 3 እና 4 እግር ባጃጆችን ያካትታል ተብሏል። ሁለተኛው አማራጭ “ሞቶ ታሪፍ” የሚባል ሲሆን ይ
Jun 81 min read


በከባድ ሙስና የተከሰሱትን ወ/ሮ በረከት ወርቁን ጨምሮ 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ፡፡
ሰኔ 1/2018 በከባድ ሙስና የተከሰሱትን ወ/ሮ በረከት ወርቁን ጨምሮ 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ፡፡ በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው ወ/ሮ በረከት ወርቁን ጨምሮ አራት ተከሳሾን ፖሊስ በዛሬ ፍርድ ቤት እንዲያቀርብ ታዞ ነበር። ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ በጋዜጣ ጥሪ ተደርጎላቸው እንዲቀርቡ በማዘዝ ለሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት፤ "በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል" የተባሉ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርን እና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ በ13 ግለሰቦች ላይ የተመሰረተውን የከባድ ሙስና ወንጀል ክስ፣ የክ
Jun 81 min read


አነስተኛ ይዞታ ያላቸውን አርሶ አደሮች፣ አርብቶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮችን በተናጠል ከመስራት ተላቅቀው በንግድ መርህ የአግሪ-ቢዝነስ ኩባንያ እንዲያደራጁ የሚፈቅድ ረቂቅ አዋጅ ተሰናደ፡፡
ሰኔ 1/2018 አነስተኛ ይዞታ ያላቸውን አርሶ አደሮች፣ አርብቶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮችን በተናጠል ከመስራት ተላቅቀው በንግድ መርህ የአግሪ-ቢዝነስ ኩባንያ እንዲያደራጁ የሚፈቅድ ረቂቅ አዋጅ ተሰናደ፡፡ በአዋጁ መሰረት የሚቋቋመው ኩባንያ ከውጪ የሚያመጣቸውን ማንኛውም ማሽነሪዎች ግብዓቶች እና መለዋወጫዎች ከግብር ነጻ ይደረጋሉ ፤ አባላት በሚያገኙት የትርፍ ክፍፍል ላይ የገቢ ግብር አይከፍሉም፡፡ ረቂቁ አነስተኛ አምራቾች እንደ ህጋዊ የንግድ ተቋም ተቆጥረው ከባንክ ብድርና ፋይናንስ እንዲገኙ እና በከፍተኛ የንግድ ውሎች ውስጥ እንዲሳተፉ ያደርጋል ተብሏል፡፡ ባለፈው ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ፓርላማው ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ለግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመራው የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ አዋጅ አነስተኛ አርሶ አደሮች ቀድሚያ የውጭ ምንዛሬ እን
Jun 82 min read


“የሰኔ እዳው ሰኔና ሰኞ የገጠመ እለት ነው”
“የሰኔ እዳው ሰኔና ሰኞ የገጠመ እለት ነው” "ሰኔና ሰኞ" በኢትዮጵያ ባህላዊ ግጥሞች ውስጥ ፍጹም የማይገናኙ ወይም ሲገናኙ አደጋ የሚያመጡ ነገሮችን ለመግለጽ እንደ ዘይቤ ሲያገለግል ይስተዋላል። ይኽ ግጥምጥሞሽም በየተወሰነ ዓመታት (በ5፣ በ6 እና በ11 ዓመታት ልዩነት) በአንድ እለት የሚገጥም ሲሆን፣በብዙዎች ዘንድም እንደ መጥፎ እድል ተደርጎ ሲወሰድ ይስተዋላል። ⁉️ለመሆኑ የሰኔና ሰኞን መግጠም እንደ መጥፎ እድል (ሚልኪ) የማየት ልማድ ከየት ተጀመረ? በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ላይ የሸዋ ገዢ የነበሩ በመርዕድ አዝማች ወሰን ሰገድ መንዝና ይፋት (ተጉለት) ውስጥ በሚኖሩበት ወቅት ቤዛነ ወልድ የሚባል ተማሪን የማይስማማኝ ወር ንገረኝ ቢሉት ሰኔና ሰኞ የገጠመ እለት ለእርሶ አይስማማዎትም እንዳላቸው እና ከ4 አመት በኋላ ሰኔና ሰኞ በገጠመ እለት ንጉ
Jun 82 min read


ሰባተናው ሃገራዊ ምርጫ የሴቶች ተሳትፎ
ግንቦት 29/2018 በአንድ ሀገር የሚካሄድ ምርጫ ለዲሞክራሲ መበርታት ከሚኖረው ሚና አንፃር አንዱ መመዘኛ ምን ያህል ሴቶች ተሳትፈውበታል የሚለው ይገኝበታል፡፡ ከዚህአንፃር ባለፈው ሰኞ በተካሄደው ሰባተናው ሃገራዊ ምርጫ የሴቶች ተሳትፎ ካለፈው ምርጫም ያነሰ እንደሆነ የተለያዩ የሀገር ውስጥና የውጭ ታዛቢዎች ተናግረዋል፡፡ በዚህም የደህንነት ስጋት አንዱ ምክንያት ሆኖ ተጠቅሷል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ንጋት መኮንን የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at
Jun 61 min read


የሚመጣው የውጪ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ሁሉ ጠቃሚ ነው ወይ?
ግንቦት 29/2018 መንግስት በተለያየ ጊዜ የኢትዮጵያ የውጪ ኢንቨስትመንት እያደገ እንደመጣ ሲናገር ይደመጣል፡፡ በበጀት ዓመቱ 9 ወራት ብቻ ከውጪ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ 3.52 ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንደተገኘ ተነግሯል፡፡ የውጪ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ማደግ በተለይ ለአዳጊ ሀገሮች የበረከቱ ጥቅሞች እንዳሉት የሚነገር ሲሆን ዘርፉ ግን ከፍተኛ የሆነ ጥንቃቄም እንደሚሻም የዘርፉ ባለሞያዎች ያስረዳሉ፡፡ በተለይ አንድ የውጪ ኢንቨስተር ወደ ሀገር ቤት ለማልማት ብሎ ሲመጣ ከፍቃድ አስጣጥ ጀምሮ በጠቅላላ በልማት ሒደቱ የጠበቀ ቁጥጥር እና ክትትል ሊደረግበት ይገባልም ይላሉ፡፡ ይህ ካልሆነ ግን በኢንቨስትንት ስም ፈቃድ ወስደው የሀገሪቱ ህግ ከሚፈቅደው ውጪ ሀገሪቱን በሚጎዱ ተግባራት የመሰማራት እድል እንዳላቸው የሚያስጠነቅቁም ብዙዎች ናቸው፡፡ እነዚህ
Jun 62 min read


በምሥራቅ አርሲ ወረዳዎች በተፈጸመው ጥቃት የደረሰውን ጉዳት በተመለከተ
ግንቦት 28/2018 በምሥራቅ አርሲ ወረዳዎች በተፈጸመው ጥቃት የደረሰውን ጉዳት በተመለከተ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የተመራ ልዑክ ከሰላም ሚኒስቴርና ከኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር መወያየታቸው ተሰማ። በተፈጸመው ጥቃት ለደረሰው ጉዳት መንግሥት የችግሩን ምንጭ አጣርቶ ዘላቂ መፍትሔ እንዲፈልግና በአካባቢውም አስተማማኝ ሰላምን እንዲያሰፍን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ መጠየቃቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ዘግቧል፡፡ ቋሚ ሲኖዶሱ በጉዳዩ ዙሪያ ውይይት ካደረገ በኋላ በሊቀ ጳጳሳት የተመራ ከፍተኛ የቤተክርስቲያን የልዑካን ቡድን ከሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ
Jun 52 min read


የ"ቪቫ ሶፍት" ማሸጊያ ፕላስቲክ ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ አመሳስለው በመሥራት፣ ጥራቱን ያልጠበቀ ምርት ገበያ ላይ አስራጭተዋል ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰብ ላይ ተጨማሪ ምርመራ አንዲያደርግ ለፖሊስ 7 ቀን ተፈቀደለት፡፡
ግንቦት 28/2018 የ"ቪቫ ሶፍት" ማሸጊያ ፕላስቲክ ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ አመሳስለው በመሥራት፣ ጥራቱን ያልጠበቀ ምርት ገበያ ላይ አስራጭተዋል ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰብ ላይ ተጨማሪ ምርመራ አንዲያደርግ ለፖሊስ 7 ቀን ተፈቀደለት፡፡ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ፤ በ"ቪቫ ሶፍት" ላይ ተፈጽሟል በተባለ "የንግድ ምልክት መብት ጥሰት ወንጀል" ጠርጥሮ በቁጥጥር ስራ ያዋላቸው ግለሰብ አቶ ሰይድ መሐመድኑር የተባሉ ግለሰብ ናቸው፡፡ ፖሊስ ለፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት ባቀረበው ማመልከቻ መሠረት፣ "ፒዩር ውድ ፐልፕ ኤንድ ፔፐር ፓኬጂንግ" በኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ሕጋዊ የምዝገባ ሰርተፍኬት የተሰጠውንና የ (ቪቫ ሶፍት) የንግድ ምልክት ተጠርጣሪው ያለ ባለቤቱ ዕውቅና እና ፈቃድ ሲጠቀሙበ
Jun 51 min read


ኤልኒኖ ሊከሰት ይችላል ተብሏል ታድያ ምን ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ነው?
ግንቦት 28/2018 ክረምቱ ዋነኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑ አንዳንድ አካባቢዎች ድርቅ፣ በአንዳንድ አካባቢዎች ደግሞ ጎርፍ ሊከሰት እንደሚችል ትንበያ ተሰጥቷል፡፡ ኤልኒኖም ሊከሰት ይችላል ተብሏል፡፡ ይህ ደግሞ ወረርሽኝ እንዲፈጥር ምርትም እንዲወድም ያደርጋል ፡፡ ታድያ ምን ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ነው? ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ፍቅሩ አምባቸው
Jun 51 min read


ኮሜርሻል ኖሚኒስ ፊቱን ወደ የውጪ ሀገር የሰው ሀይል አቅርቦትም ፊቱን ማዞሩን ተናገረ፡፡
ግንቦት 28/2018 በሶስተኛ ወገን አገልግሎት ዘርፍ የጥበቃ፣ የፅዳት፣ የሀብትና ንብረት አስተዳደር ስራ 60 ዓመት የሞላው ኮሜርሻል ኖሚኒስ አሁን ደግሞ ፊቱን ወደ የውጪ ሀገር የሰው ሀይል አቅርቦትም ፊቱን ማዞሩን ተናገረ፡፡ በ1958 ዓ.ም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተቋቋመው ድርጅቱ ለመንግስታዊም ሆኑ ለግል ተቋማት የፅዳትና የጥበቃ አገልግሎት የሚሆኑ የሰው ሀይል ከማቅረብ በተጨማሪ ፣ ህንፃና ንብረት አስተዳደር ፣ ከካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ የፈንድ አስተዳደርን ጨምሮ 13 ዓይነት አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ ተናግሯል፡፡ በዚህም በመላ ሀገሪቱ በሚገኙት 32 ቅርንጫፎቹ ከ40 ሺህ በላይ ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩን የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ኮማንደር ጥላሁን ፀጋዬ ነግረውናል፡፡ ድርጅቱ እስካሁን ሲሰጣቸው የነበሩ አገልግሎቶቹን ማዘመንና ማስፋት ላይ እን
Jun 51 min read


የትምህርት ሚኒስቴር ከቅድመ አንደኛ እስከ መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተመጣጠነ የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም እንዲተገብር ግዴታ የሚጥል ረቂቅ አዋጅ ለቋሚ ኮሚቴ ተመራ፡፡
ግንቦት 28/2018 በሀገሪቱ "አሳሳቢ" ደረጃ ላይ ያለውን የመቀንጨር ችግር ለመፍታት የትምህርት ሚኒስቴር ከቅድመ አንደኛ እስከ መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለሚማሩ ተማሪዎች የተመጣጠነ የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም እንዲተገብር ግዴታ የሚጥል ረቂቅ አዋጅ ለቋሚ ኮሚቴ ተመራ፡፡ ረቂቅ አዋጁ በሀገሪቱ "አሳሳቢ" ደረጃ ላይ ያለውን የመቀንጨር ችግር ለመፍታት 13 ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ላይ ከፍተኛ ግዴታ የሚጥል ነው፡፡ ለረቂቅ አዋጁ መተግበር ማንኛውም ሰው የመተባበርን ግዴታ እንዳለበት በረቂቁ ተደንግጓል፡፡ የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ትናንት ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው ለጤና፣ ማህበራዊ ልማት ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመራው የምግብ ስርዓት እና የስርዓት ምግብ ረቂቅ አዋጅ ይሰኛል። ረቂቁ የቃላቱን ትርጉ
Jun 52 min read


የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ
ግንቦት 27/2018 ዛሬ በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት በቀረበው የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ በግብር ከፋዮችንና በግብር ሰብሳቢውን መስሪያ ቤቱ መካከል አለመስማማት በተፈጠረ ጊዜ የሚያስማማ የግልግል ዳኝነት እንዲኖር መደንገጉ ድርጅቶችን ከመዘጋት የሚያድን መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ተናገሩ፡፡ በገለልተኝነት የግልግል ዳኝነት እንዲሰጡ የሚመጠሩ ሰዎችን በተመለከተ ግን አመራረጡ ላይ ጥንቃቄ ይፈልጋል ብለዋል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ያሬድ እንዳሻው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp :..
Jun 41 min read


ማንኛውም ደረሰኝ ሳይቆርጥ የተገበያየ አካል በወንጀል እስከመጠየቅ የሚያደርሰው የተሻሻለው የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ እንደራሴዎች ም/ቤት ቀረበ፡፡
ግንቦት 27/2018 ማንኛውም ደረሰኝ ሳይቆርጥ የተገበያየ አካል በወንጀል እስከመጠየቅ የሚያደርሰው የተሻሻለው የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ቀረበ፡፡ ረቂቁ የታክስ ማጭበርበርን ለመከላከል ለ10 ዓመታት ወደኋላ በመሄድ ሂሳቡን በመመርመር ወይም ሂሳብ ኦዲት በማድረግ ተጨማሪ ግብር ማስከፈልን ለገቢ ሰብሳቢው የሚፈቅድ ነው፡፡ ዛሬ ለምክር ቤቱ የቀረበው ረቂቅ የግብር አስተዳደር አዋጅ በተለይ ደረሰኝ ባለመቁረጥ የሚደረግ ግብይት ላይ ከፍ ያለ ቅጣትን የሚያስከትሉ አንቀፆችን የያዘ ነው፡፡ ማንኛውም ሰው ህጋዊ ደረሰኝ ያልሰጠ እንደሆነ በእያንዳንዱ ባልሰጠው ደረሰኝ ልክ 100 ሺህ ብር አስተዳደራዊ ቅጣት በገንዘብ ይቀጣል ይላል የማሻሽያ አዋጁ ማብራሪያ፡፡ በተጨማሪ ይሄንኑ አስተዳደራዊ ቅጣት በዓመት ሁለት ጊዜ የተቀጣ እንደሆነ
Jun 42 min read


የአለማችን የሙቀት መጠን በእጅጉ እየጨመረ እንደሚመጣ የሳይንስ ሊቃውንት አስጠነቀቁ፡፡
ግንቦት 26/2018 - ዓለም አቀፍ ወሬዎች #ኤልኒኖ የአለማችን የሙቀት መጠን በእጅጉ እየጨመረ እንደሚመጣ የሳይንስ ሊቃውንት አስጠነቀቁ፡፡ ከፍተኛ የሙቀት መጠን በብዙ የአለማችን ክፍሎች እንደሚመዘገብ አለም አቀፉ የአየር ሁኔታ ተከታታይ መስሪያ ቤት ማስጠንቀቁን ቢቢሲ ፅፏል፡፡ ኤል ኒኖ የተሰኘው የአየር ለውጥ ክስተት የከፍተኛ ሙቀት ጭማሪው ምክንያት መሆኑ ታውቋል፡፡ ከወዲሁም የሙቀት መጠን ጭማሪው መከሰቱን መረጃው አስታውሷል፡፡ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ደግሞ የሙቀት መጠን ጭማሪው እየተጠናከረ ይመጣል ተብላል፡፡ የሙቀት መጠን ጭማሪው ደረጃ ሊቃውንቱን ከወዲሁ በእጅጉ እያሳሰበ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ የአየር ለውጡን ተፅዕኖ ለመገደብ ሲወተወት ቢቆይም ችግሩ ከእርምጃው እየገዘፈ መምጣቱ ይነገራል፡፡ #አሜሪካ የአሜሪካ ጦር በኢራን ኬሽም ደሴት ላይ ያነጣጠረ
Jun 32 min read


በተለያዩ ፈተናዎች ውስጥ ያለፈው የትምህርት ዘመን ምን መፍትሔ ተበጅተውለት ይሆን?
ግንቦት 26/2018 የተጀመረው የትምህርት ዘመን ሊጠናቀቅ የ1 ወር እድሜ ቀርቶታል፡፡ በመፅሐፍ ህትመት ችግር ምክንያት፤ አንድ መፅሐፍ ለአራት ሲጠቀሙ የቆዩ ተማሪዎች መኖራቸው ይታወቃል፡፡ የበጀት እጥረት እና የመምህራን ደመወዝ አለመከፈልን ጨምሮ በተለያዩ ፈተናዎች ውስጥ ያለፈው የትምህርት ዘመን ምን መፍትሔ ተበጅተውለት ይሆን? ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ፋሲካ ሙሉወርቅ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx X :- https://x.com/shegerfm?s
Jun 31 min read


በምርጫ ወቅት ከህግ ውጪ የሆነ ተግባር የፈፀሙ የምርጫ አስፈፃሚዎችን ከስራ ማሰናበቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተናገረ።
ግንቦት 25/2018 በምርጫ ወቅት ከህግ ውጪ የሆነ ተግባር የፈፀሙ የምርጫ አስፈፃሚዎችን ከስራ ማሰናበቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተናገረ። የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የምርጫውን እለትና የድምፅ ቆጠራ እየተካሄደበት ነው ያሉትን የዛሬውን እለት ክንውን በተመለከተ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው:። የተለያዩ ጥቆማዎችን መሰረት በማድረግ የቦርዱ የክትትል ቡድን ባደረገው አሰሳ ከህግ ውጪ የሆነ ተግባር ሲፈፅሙ የተገኙ ምርጫ አስፈፃሚዎች መገኘታቸውን ተናግረዋል። አድርገውታል የተባለው ህገ ወጥ ተግባር ባይፍታታም አዲስ አበባ ላይ ምርጫ ሲያስፈፅሙ የነበሩ ሁለት ሰራተኞች ናቸው ከስራ ተባርረዋል የተባለው። በተያያዘም ቡርጂ በተባለ የምርጫ ጣቢያ ትናንት የምርጫ አስፈፃሚዎች የምርጫ ወረቀቱን ራሳቸው ሲሞሉ ተገኝተዋል በመባሉ ጣቢያው መዘጋ
Jun 31 min read


የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የምሰጠው የአየር ትንበያ ትክክለኛነት እስከ 90 በመቶ እየደረሰ ነው አለ።
ግንቦት 21/2018 የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የምሰጠው የአየር ትንበያ ትክክለኛነት እስከ 90 በመቶ እየደረሰ ነው አለ። እንደ ውሃና ኢነርጂ እንዲሁም ግብርና ሚኒስቴር ያሉ ተቋማትም ከዚህ ቀደም ከነበረው በተሻለ መልኩ የትንበያ መረጃውን መሰረት አድርገው ስራዎችን እየሰሩ እንደሚገኙ ነግረናል። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት በተለያዩ ወቅቶች የሚኖረውን የአየር ሁኔታ አዝማሚያ በተመለከተ ትንበያዎችን እና ቅድመ ማስጠንቀቂያዎችን ይሰጣል። ኢንስቲትዩቱ እነዚህን ትንበያዎችን እና ማስጠንቀቂያዎች የሚሰጠው በተለያዩ አካባቢዎች ካሉት የአየር ሁኔታ መመዝገበያ ጣቢያዎች፤ከሚያሰባስበው መረጃ እንደሆነ የኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አሳምነው ተሾመ ተናግረዋል። መረጃዎቹን በመጠቀም የሚሰጠው ትንበያ ትክክለኛነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መ
May 291 min read


የት/ት ጉዳይ ግድ ብሎናል ያሉ 4 ድርጅቶች ተናባቢ የዲጂታል የትምህርት ስነ ምህዳር ይዘው መምጣታቸውን ተናገሩ፡፡
ግንቦት 21/2018 የትምህርት ጉዳይ ግድ ብሎናል ያሉ 4 ድርጅቶች "አሪፍ ስኩል" ሲሉ የጠሩትን ተናባቢ የዲጂታል የትምህርት ስነ ምህዳር ይዘው መምጣታቸውን ተናገሩ፡፡ አሪፍ ስኩል ይዘው የመጡት አሪፍ ፔይ ፣ AIT ቴክሎሎጂ፣ ገበያ እና ኢዱኬሽን ማተርስ የተባሉ አራት ድርጅቶች ናቸው፡፡ አሪፍ ስኩል የተቀናጀ የትምህርት አስተዳደር ሥርዓትን ፣ የክፍያ መንገድን ፣ በሰው ሰራሽ አስተውህሎት የታገዘ የትምህርት መሳሪያዎችን ያካተተ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ ስርዓቱ ለትምህርት ቤቶች አስተዳደር ፣ ለመምህራን፣ ለተማሪዎች እንዲሁም ለወላጆች እንደሚጠቅም ሲነገር ሰምተናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ....... ንጋቱ ሙሉ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shortur
May 291 min read


የእዳ ሽግሽግ ድርድሩ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ አለመጠናቀቁ ኢትዮጵያ ላይ የሚኖረው ተፅዕኖ ምን መሳይ ነው?
ግንቦት 21/2018 ለኢንዱስትሪ ፓርኮች ግንባታ የተወሰደው የአንድ ቢሊዮን ዶላር እዳ አከፋፈል በተመለከተ ኢትዮጵያ ከአበዳሪዎቿ ጋር አልተስማማችም፡፡ ከሰሞኑም ለቀናት የተደረገው ንግግር ውጤት እንዳላመጣ የገንዘብ ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡ የእዳ ሽግሽግ ድርድሩ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ አለመጠናቀቁ ኢትዮጵያ ላይ የሚኖረው ተፅዕኖ ምን መሳይ ነው? የዘርፉን ባለሙያ አነጋግረናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ....... ትዕግስት ዘሪሁን የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at
May 291 min read


ተቋማት በየዓመቱ ከሚያገኙት ትርፍ፤ ምን ያህሉን ለሰራተኞቻቸው ያከፋፍላሉ?
ግንቦት 20/2018 አንዳንድ ተቋማት ከሚያገኙት ዓመታዊ ትርፍ ከፊሉን ለሰራተኞቻቸው በጉርሻ ወይም በደመወዝ ጭማሪ መልክ ያከፋፍላሉ፡፡ ሌሎች ተቋሞች ደግሞ የተለየ መንገድን ይከተላሉ፡፡ ስራ እንዳይበደል በአሰሪና ሰራተኛ መሀከል ጤናማ ግንኙነት እንዲኖር ለማድረግ ተቋማት ምን ዓይነት መንገድን ቢከተሉ ይበጃል? የሌሎች ሀገሮች ልምድ እንዴት ያለ ነው? ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ....... ማርታ በቀለ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx X :-...
May 291 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

