top of page


በምሥራቅ አርሲ ወረዳዎች በተፈጸመው ጥቃት የደረሰውን ጉዳት በተመለከተ
ግንቦት 28/2018 በምሥራቅ አርሲ ወረዳዎች በተፈጸመው ጥቃት የደረሰውን ጉዳት በተመለከተ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የተመራ ልዑክ ከሰላም ሚኒስቴርና ከኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር መወያየታቸው ተሰማ። በተፈጸመው ጥቃት ለደረሰው ጉዳት መንግሥት የችግሩን ምንጭ አጣርቶ ዘላቂ መፍትሔ እንዲፈልግና በአካባቢውም አስተማማኝ ሰላምን እንዲያሰፍን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ መጠየቃቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ዘግቧል፡፡ ቋሚ ሲኖዶሱ በጉዳዩ ዙሪያ ውይይት ካደረገ በኋላ በሊቀ ጳጳሳት የተመራ ከፍተኛ የቤተክርስቲያን የልዑካን ቡድን ከሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ
Jun 52 min read


የ"ቪቫ ሶፍት" ማሸጊያ ፕላስቲክ ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ አመሳስለው በመሥራት፣ ጥራቱን ያልጠበቀ ምርት ገበያ ላይ አስራጭተዋል ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰብ ላይ ተጨማሪ ምርመራ አንዲያደርግ ለፖሊስ 7 ቀን ተፈቀደለት፡፡
ግንቦት 28/2018 የ"ቪቫ ሶፍት" ማሸጊያ ፕላስቲክ ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ አመሳስለው በመሥራት፣ ጥራቱን ያልጠበቀ ምርት ገበያ ላይ አስራጭተዋል ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰብ ላይ ተጨማሪ ምርመራ አንዲያደርግ ለፖሊስ 7 ቀን ተፈቀደለት፡፡ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ፤ በ"ቪቫ ሶፍት" ላይ ተፈጽሟል በተባለ "የንግድ ምልክት መብት ጥሰት ወንጀል" ጠርጥሮ በቁጥጥር ስራ ያዋላቸው ግለሰብ አቶ ሰይድ መሐመድኑር የተባሉ ግለሰብ ናቸው፡፡ ፖሊስ ለፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት ባቀረበው ማመልከቻ መሠረት፣ "ፒዩር ውድ ፐልፕ ኤንድ ፔፐር ፓኬጂንግ" በኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ሕጋዊ የምዝገባ ሰርተፍኬት የተሰጠውንና የ (ቪቫ ሶፍት) የንግድ ምልክት ተጠርጣሪው ያለ ባለቤቱ ዕውቅና እና ፈቃድ ሲጠቀሙበ
Jun 51 min read


ኤልኒኖ ሊከሰት ይችላል ተብሏል ታድያ ምን ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ነው?
ግንቦት 28/2018 ክረምቱ ዋነኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑ አንዳንድ አካባቢዎች ድርቅ፣ በአንዳንድ አካባቢዎች ደግሞ ጎርፍ ሊከሰት እንደሚችል ትንበያ ተሰጥቷል፡፡ ኤልኒኖም ሊከሰት ይችላል ተብሏል፡፡ ይህ ደግሞ ወረርሽኝ እንዲፈጥር ምርትም እንዲወድም ያደርጋል ፡፡ ታድያ ምን ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ነው? ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ፍቅሩ አምባቸው
Jun 51 min read


ኮሜርሻል ኖሚኒስ ፊቱን ወደ የውጪ ሀገር የሰው ሀይል አቅርቦትም ፊቱን ማዞሩን ተናገረ፡፡
ግንቦት 28/2018 በሶስተኛ ወገን አገልግሎት ዘርፍ የጥበቃ፣ የፅዳት፣ የሀብትና ንብረት አስተዳደር ስራ 60 ዓመት የሞላው ኮሜርሻል ኖሚኒስ አሁን ደግሞ ፊቱን ወደ የውጪ ሀገር የሰው ሀይል አቅርቦትም ፊቱን ማዞሩን ተናገረ፡፡ በ1958 ዓ.ም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተቋቋመው ድርጅቱ ለመንግስታዊም ሆኑ ለግል ተቋማት የፅዳትና የጥበቃ አገልግሎት የሚሆኑ የሰው ሀይል ከማቅረብ በተጨማሪ ፣ ህንፃና ንብረት አስተዳደር ፣ ከካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ የፈንድ አስተዳደርን ጨምሮ 13 ዓይነት አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ ተናግሯል፡፡ በዚህም በመላ ሀገሪቱ በሚገኙት 32 ቅርንጫፎቹ ከ40 ሺህ በላይ ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩን የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ኮማንደር ጥላሁን ፀጋዬ ነግረውናል፡፡ ድርጅቱ እስካሁን ሲሰጣቸው የነበሩ አገልግሎቶቹን ማዘመንና ማስፋት ላይ እን
Jun 51 min read


የትምህርት ሚኒስቴር ከቅድመ አንደኛ እስከ መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተመጣጠነ የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም እንዲተገብር ግዴታ የሚጥል ረቂቅ አዋጅ ለቋሚ ኮሚቴ ተመራ፡፡
ግንቦት 28/2018 በሀገሪቱ "አሳሳቢ" ደረጃ ላይ ያለውን የመቀንጨር ችግር ለመፍታት የትምህርት ሚኒስቴር ከቅድመ አንደኛ እስከ መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለሚማሩ ተማሪዎች የተመጣጠነ የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም እንዲተገብር ግዴታ የሚጥል ረቂቅ አዋጅ ለቋሚ ኮሚቴ ተመራ፡፡ ረቂቅ አዋጁ በሀገሪቱ "አሳሳቢ" ደረጃ ላይ ያለውን የመቀንጨር ችግር ለመፍታት 13 ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ላይ ከፍተኛ ግዴታ የሚጥል ነው፡፡ ለረቂቅ አዋጁ መተግበር ማንኛውም ሰው የመተባበርን ግዴታ እንዳለበት በረቂቁ ተደንግጓል፡፡ የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ትናንት ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው ለጤና፣ ማህበራዊ ልማት ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመራው የምግብ ስርዓት እና የስርዓት ምግብ ረቂቅ አዋጅ ይሰኛል። ረቂቁ የቃላቱን ትርጉ
Jun 52 min read


የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ
ግንቦት 27/2018 ዛሬ በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት በቀረበው የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ በግብር ከፋዮችንና በግብር ሰብሳቢውን መስሪያ ቤቱ መካከል አለመስማማት በተፈጠረ ጊዜ የሚያስማማ የግልግል ዳኝነት እንዲኖር መደንገጉ ድርጅቶችን ከመዘጋት የሚያድን መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ተናገሩ፡፡ በገለልተኝነት የግልግል ዳኝነት እንዲሰጡ የሚመጠሩ ሰዎችን በተመለከተ ግን አመራረጡ ላይ ጥንቃቄ ይፈልጋል ብለዋል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ያሬድ እንዳሻው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp :..
Jun 41 min read


ማንኛውም ደረሰኝ ሳይቆርጥ የተገበያየ አካል በወንጀል እስከመጠየቅ የሚያደርሰው የተሻሻለው የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ እንደራሴዎች ም/ቤት ቀረበ፡፡
ግንቦት 27/2018 ማንኛውም ደረሰኝ ሳይቆርጥ የተገበያየ አካል በወንጀል እስከመጠየቅ የሚያደርሰው የተሻሻለው የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ቀረበ፡፡ ረቂቁ የታክስ ማጭበርበርን ለመከላከል ለ10 ዓመታት ወደኋላ በመሄድ ሂሳቡን በመመርመር ወይም ሂሳብ ኦዲት በማድረግ ተጨማሪ ግብር ማስከፈልን ለገቢ ሰብሳቢው የሚፈቅድ ነው፡፡ ዛሬ ለምክር ቤቱ የቀረበው ረቂቅ የግብር አስተዳደር አዋጅ በተለይ ደረሰኝ ባለመቁረጥ የሚደረግ ግብይት ላይ ከፍ ያለ ቅጣትን የሚያስከትሉ አንቀፆችን የያዘ ነው፡፡ ማንኛውም ሰው ህጋዊ ደረሰኝ ያልሰጠ እንደሆነ በእያንዳንዱ ባልሰጠው ደረሰኝ ልክ 100 ሺህ ብር አስተዳደራዊ ቅጣት በገንዘብ ይቀጣል ይላል የማሻሽያ አዋጁ ማብራሪያ፡፡ በተጨማሪ ይሄንኑ አስተዳደራዊ ቅጣት በዓመት ሁለት ጊዜ የተቀጣ እንደሆነ
Jun 42 min read


የአለማችን የሙቀት መጠን በእጅጉ እየጨመረ እንደሚመጣ የሳይንስ ሊቃውንት አስጠነቀቁ፡፡
ግንቦት 26/2018 - ዓለም አቀፍ ወሬዎች #ኤልኒኖ የአለማችን የሙቀት መጠን በእጅጉ እየጨመረ እንደሚመጣ የሳይንስ ሊቃውንት አስጠነቀቁ፡፡ ከፍተኛ የሙቀት መጠን በብዙ የአለማችን ክፍሎች እንደሚመዘገብ አለም አቀፉ የአየር ሁኔታ ተከታታይ መስሪያ ቤት ማስጠንቀቁን ቢቢሲ ፅፏል፡፡ ኤል ኒኖ የተሰኘው የአየር ለውጥ ክስተት የከፍተኛ ሙቀት ጭማሪው ምክንያት መሆኑ ታውቋል፡፡ ከወዲሁም የሙቀት መጠን ጭማሪው መከሰቱን መረጃው አስታውሷል፡፡ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ደግሞ የሙቀት መጠን ጭማሪው እየተጠናከረ ይመጣል ተብላል፡፡ የሙቀት መጠን ጭማሪው ደረጃ ሊቃውንቱን ከወዲሁ በእጅጉ እያሳሰበ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ የአየር ለውጡን ተፅዕኖ ለመገደብ ሲወተወት ቢቆይም ችግሩ ከእርምጃው እየገዘፈ መምጣቱ ይነገራል፡፡ #አሜሪካ የአሜሪካ ጦር በኢራን ኬሽም ደሴት ላይ ያነጣጠረ
Jun 32 min read


በተለያዩ ፈተናዎች ውስጥ ያለፈው የትምህርት ዘመን ምን መፍትሔ ተበጅተውለት ይሆን?
ግንቦት 26/2018 የተጀመረው የትምህርት ዘመን ሊጠናቀቅ የ1 ወር እድሜ ቀርቶታል፡፡ በመፅሐፍ ህትመት ችግር ምክንያት፤ አንድ መፅሐፍ ለአራት ሲጠቀሙ የቆዩ ተማሪዎች መኖራቸው ይታወቃል፡፡ የበጀት እጥረት እና የመምህራን ደመወዝ አለመከፈልን ጨምሮ በተለያዩ ፈተናዎች ውስጥ ያለፈው የትምህርት ዘመን ምን መፍትሔ ተበጅተውለት ይሆን? ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ፋሲካ ሙሉወርቅ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx X :- https://x.com/shegerfm?s
Jun 31 min read


በምርጫ ወቅት ከህግ ውጪ የሆነ ተግባር የፈፀሙ የምርጫ አስፈፃሚዎችን ከስራ ማሰናበቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተናገረ።
ግንቦት 25/2018 በምርጫ ወቅት ከህግ ውጪ የሆነ ተግባር የፈፀሙ የምርጫ አስፈፃሚዎችን ከስራ ማሰናበቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተናገረ። የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የምርጫውን እለትና የድምፅ ቆጠራ እየተካሄደበት ነው ያሉትን የዛሬውን እለት ክንውን በተመለከተ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው:። የተለያዩ ጥቆማዎችን መሰረት በማድረግ የቦርዱ የክትትል ቡድን ባደረገው አሰሳ ከህግ ውጪ የሆነ ተግባር ሲፈፅሙ የተገኙ ምርጫ አስፈፃሚዎች መገኘታቸውን ተናግረዋል። አድርገውታል የተባለው ህገ ወጥ ተግባር ባይፍታታም አዲስ አበባ ላይ ምርጫ ሲያስፈፅሙ የነበሩ ሁለት ሰራተኞች ናቸው ከስራ ተባርረዋል የተባለው። በተያያዘም ቡርጂ በተባለ የምርጫ ጣቢያ ትናንት የምርጫ አስፈፃሚዎች የምርጫ ወረቀቱን ራሳቸው ሲሞሉ ተገኝተዋል በመባሉ ጣቢያው መዘጋ
Jun 31 min read


የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የምሰጠው የአየር ትንበያ ትክክለኛነት እስከ 90 በመቶ እየደረሰ ነው አለ።
ግንቦት 21/2018 የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የምሰጠው የአየር ትንበያ ትክክለኛነት እስከ 90 በመቶ እየደረሰ ነው አለ። እንደ ውሃና ኢነርጂ እንዲሁም ግብርና ሚኒስቴር ያሉ ተቋማትም ከዚህ ቀደም ከነበረው በተሻለ መልኩ የትንበያ መረጃውን መሰረት አድርገው ስራዎችን እየሰሩ እንደሚገኙ ነግረናል። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት በተለያዩ ወቅቶች የሚኖረውን የአየር ሁኔታ አዝማሚያ በተመለከተ ትንበያዎችን እና ቅድመ ማስጠንቀቂያዎችን ይሰጣል። ኢንስቲትዩቱ እነዚህን ትንበያዎችን እና ማስጠንቀቂያዎች የሚሰጠው በተለያዩ አካባቢዎች ካሉት የአየር ሁኔታ መመዝገበያ ጣቢያዎች፤ከሚያሰባስበው መረጃ እንደሆነ የኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አሳምነው ተሾመ ተናግረዋል። መረጃዎቹን በመጠቀም የሚሰጠው ትንበያ ትክክለኛነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መ
May 291 min read


የት/ት ጉዳይ ግድ ብሎናል ያሉ 4 ድርጅቶች ተናባቢ የዲጂታል የትምህርት ስነ ምህዳር ይዘው መምጣታቸውን ተናገሩ፡፡
ግንቦት 21/2018 የትምህርት ጉዳይ ግድ ብሎናል ያሉ 4 ድርጅቶች "አሪፍ ስኩል" ሲሉ የጠሩትን ተናባቢ የዲጂታል የትምህርት ስነ ምህዳር ይዘው መምጣታቸውን ተናገሩ፡፡ አሪፍ ስኩል ይዘው የመጡት አሪፍ ፔይ ፣ AIT ቴክሎሎጂ፣ ገበያ እና ኢዱኬሽን ማተርስ የተባሉ አራት ድርጅቶች ናቸው፡፡ አሪፍ ስኩል የተቀናጀ የትምህርት አስተዳደር ሥርዓትን ፣ የክፍያ መንገድን ፣ በሰው ሰራሽ አስተውህሎት የታገዘ የትምህርት መሳሪያዎችን ያካተተ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ ስርዓቱ ለትምህርት ቤቶች አስተዳደር ፣ ለመምህራን፣ ለተማሪዎች እንዲሁም ለወላጆች እንደሚጠቅም ሲነገር ሰምተናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ....... ንጋቱ ሙሉ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shortur
May 291 min read


የእዳ ሽግሽግ ድርድሩ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ አለመጠናቀቁ ኢትዮጵያ ላይ የሚኖረው ተፅዕኖ ምን መሳይ ነው?
ግንቦት 21/2018 ለኢንዱስትሪ ፓርኮች ግንባታ የተወሰደው የአንድ ቢሊዮን ዶላር እዳ አከፋፈል በተመለከተ ኢትዮጵያ ከአበዳሪዎቿ ጋር አልተስማማችም፡፡ ከሰሞኑም ለቀናት የተደረገው ንግግር ውጤት እንዳላመጣ የገንዘብ ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡ የእዳ ሽግሽግ ድርድሩ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ አለመጠናቀቁ ኢትዮጵያ ላይ የሚኖረው ተፅዕኖ ምን መሳይ ነው? የዘርፉን ባለሙያ አነጋግረናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ....... ትዕግስት ዘሪሁን የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at
May 291 min read


ተቋማት በየዓመቱ ከሚያገኙት ትርፍ፤ ምን ያህሉን ለሰራተኞቻቸው ያከፋፍላሉ?
ግንቦት 20/2018 አንዳንድ ተቋማት ከሚያገኙት ዓመታዊ ትርፍ ከፊሉን ለሰራተኞቻቸው በጉርሻ ወይም በደመወዝ ጭማሪ መልክ ያከፋፍላሉ፡፡ ሌሎች ተቋሞች ደግሞ የተለየ መንገድን ይከተላሉ፡፡ ስራ እንዳይበደል በአሰሪና ሰራተኛ መሀከል ጤናማ ግንኙነት እንዲኖር ለማድረግ ተቋማት ምን ዓይነት መንገድን ቢከተሉ ይበጃል? የሌሎች ሀገሮች ልምድ እንዴት ያለ ነው? ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ....... ማርታ በቀለ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx X :-...
May 291 min read


የ12ኛ ክፍል ፈተናን በኦንላይን ሙሉ ለሙሉ ለመስጠት የግብዓት እጥረት እንደገጠማቸው ያነጋገርናቸው ክልሎች ተናገሩ፡፡
ግንቦት 20/2018 የ12ኛ ክፍል ፈተናን በኦንላይን ሙሉ ለሙሉ ለመስጠት የግብዓት እጥረት እንደገጠማቸው ያነጋገርናቸው ክልሎች ተናገሩ፡፡ ከሰኔ 24 ጀምሮ የሚሰጠው የ12ተኛ ክፍል ፈተና ሙሉ ለሙሉ በኦንላይን ለመስጠት ትምህርት ሚኒስቴር ዝግጅት ማጠናቀቁን በተለያዩ ጊዜያት መነገሩ ይታወሳል፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ፤ በክልሉ ከሚፈተኑ ተማሪዎች መካከል በኦንላይን መፈተን የሚችለው 76 በመቶ ብቻ መሆኑን አስረድቷል፡፡ በቀሪ ጊዜ ይህንን ቁጥር ወደ 80 በመቶ ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን ቢሮው የጠቀሰ ሲሆን ዘንድሮ 24 በመቶ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞችን በወረቀት ለመፈተን እየተዘጋጀ መሆኑን ነግሮናል፡፡ ለፈተናው የሚያስፈልጉ የኮምፒዩተር እጥረት፣ የኢንተርኔት አለመሟላት እና ሌሎች ግብአቶች እጥረት ማጋጠሙ ተሰምቷል፡፡ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክል
May 281 min read


ግንቦት 20/2018 - ዓለም አቀፍ ወሬዎች
#ፍልስጤም የፍልስጤማውያኑ ታጣቂ ቡድን (ሐማስ) የወታደራዊ ክንፉ የበላይ ሞሐመድ አውዳ በእስራኤል ጥቃት መገደሉ እውነት ነው አለ፡፡ ሞሐመድ አውዳ የተገደለው እስራኤል በጋዛ ከተማ በፈፀመችው የአየር ጥቃት እንደሆነ TRT ዎርልድ ጽፏል፡፡ ከሐማሱ የወታደራዊ ክንፍ አዛዥ ጋር በጥቃቱ ባለቤቱ እና ሁለት ልጆቹ መገደላቸው ታውቋል፡፡ አውዳ ከሐማስ መስራቾች አንዱ እንደነበር በቡድኑ መግለጫ ተጠቅሷል፡፡ ሞሐመድ አውዳ በሐማስ ወታደራዊ ክንፍ የበላይነት የተሰየመው በቅርቡ እንደነበር መረጃው አስታውሷል፡፡ እስራኤል የጋዛ የጦር ዘመቻዋን ከጀመረች ወዲህ በርካታ ስመ ጥር የሐማስ ወታደራዊ አዛዦችን መግደሏን መረጃው አስታውሷል፡፡ #ጋና ምዕራብ አፍሪካዊቱ ጋና ከደቡብ አፍሪካ ዜጎቿን ማስወጣት ጀመረች፡፡ በደቡብ አፍሪካ በውጭ ተወላጅ አፍሪካውያን ላይ ያነጣጠረው
May 282 min read


የምግብ ችግር እያለባትም፤ ካመረተችው ግማሽ የሚጠጋውን የምትደፋዋ ኢትዮጵያ!
ግንቦት 20/2018 በኢትዮጵያ በየዓመቱ ገበሬው ከሚያመርተው ምርት ከ40 በመቶ በላዩ ከገበታ ሳይደርስ ባክኖ ይቀራል። በየዓመቱ ከሚመረት እንደ ሽንኩርትና ቲማቲም ያለው ቶሎ የሚበላሽ የግብርና ምርት ግማሽ ያክሉ ተበላሽቶ የሚደፋ እንደሆነ ይነገራል። አፍሪካ በዚህ መንገድ ገበሬዎቿ ቢያመርቱም 4 ቢሊየን ዶላር የሚገመት ምርት ተበላሽቶ መልሳ ትደፋለች። ከዚህ ጀርባ ያለው ትልቁ ችግር የቀዝቃዛ ምርት ማጓጓዣና መስቀመጫ ሰንሰለት አለመኖር ነው ይባላል። ያደጉት ሀገሮች ከአጠቃላይ ምርታቸው የምርት ብክነትን ከ1 በመቶ በታች ማውረድ ችለዋል። ኢትዮጵያ ግን የምግብ ችግር ቢኖርባትም፤ ዛሬም ብዙ ስለማምረት ብትደክምም ካመረተችው ግማሽ ያክሉን እየደፋች ቀጥላለች። ታዲያ ምን ይበጃል? የቀዝቃዛ ምርት ሰንሰለትን ማስፋፋትስ ለምን ከባድ ሆነ? የዘርፉ ባለሙያዎች
May 281 min read


የቅድመ ምርጫ አውዱን እየገመገመ ያጋጠሙ ችግሮች እንዲፈቱ ከምርጫ ቦርድ እና ከሚመለከታቸው ጋር ለመነጋገር ዝግጅት ማድረጉን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ድርጀቶች ህብረት ተናገረ፡፡
ግንቦት 18/2018 የቅድመ ምርጫ አውዱን እየገመገመ ያጋጠሙ ችግሮች እንዲፈቱ ከምርጫ ቦርድ እና ከሚመለከታቸው ጋር ለመነጋገር ዝግጅት ማድረጉን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ድርጀቶች ህብረት ተናገረ፡፡ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ መንግስት ፣ ምርጫ ቦርድ ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ፣ ሚድያዎችና ሌሎችም የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ....... https://l1nq.com/z0jzlsy ትዕግስት ዘሪሁን
May 261 min read


“የድሬደዋ ነፃ የንግድ ቀጠና” በኢትዮጵያ ቀዳሚው ነፃ የንግድ ቀጠና ነው።
ግንቦት 18/2018 “የድሬደዋ ነፃ የንግድ ቀጠና” በኢትዮጵያ ቀዳሚው ነፃ የንግድ ቀጠና ነው። 2014 መጨረሻ ላይ ስራ የጀመረው ይህ ነፃ የንግድ ቀጠና ለጅቡቲ ወደብ በቅርብ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት የተቋቋመውና በኦሮሚያ ክልል ሞጆ ከተማ የሚገኘው ገዳ ነፃ የንግድ ቀጠና ደግሞ ሁለተኛው ነው፡፡ እነዚህ ነፃ የንግድ ቀጠናዎች በውስጣቸው መካሄድ በሚቻል ሰፋ ያሉ የኢኮኖሚ ተግባራት ከልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እንደሚለዩ ይጠቀሳል፡፡ በነጻ የንግድ ቀጠና ውስጥ ምርት ማምረት ፤ ንግድ ማካሄድ እና የሎጅስቲክስ አገልግሎት መስጠት እንደሚቻል፤በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ፤ የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ሃላፊ የሆኑት አቶ ጳውሎስ በለጠ ነግረውናል፡፡ የፋይናንስ እና ሆቴል አገልግሎቶችም ማቅረብ ይቻላል ብለዋል፡፡ ነጻየ
May 261 min read


አሁን በስራ ላይ ያሉ ሁሉም አሽከርካሪዎች ሰልጥነው የብቃት ምዘና አንዲወስዱ የሚያስገድድ ዘመናዊ የቁጥጥር ሥርዓት ሊዘረጋ ነው፡፡
ግንቦት 18/2018 አሁን በስራ ላይ ያሉ ሁሉም አሽከርካሪዎች ሰልጥነው የብቃት ምዘና አንዲወስዱ የሚያስገድድ ዘመናዊ የቁጥጥር ሥርዓት ሊዘረጋ ነው፡፡ ሁሉም አሽከርካሪዎች እንደገና እንዲሰለጥኑና እንዲመዘኑ በማድረግ ብቃታቸውን እንዲያረጋግጡ የሚያስችል አጠቃላይ የሰነድ ዝግጅት ተጠናቋል ያለው የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ነው፡፡ ይህ አዲስ አሰራር ከተለመደው አሰራር በተለየ መልኩ ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ፣ የምዘና ሂደቱ በዲጂታል ሲስተም እንዲመራ ተደርጎ ተቀርጿል ሲል ሚኒስቴር መ/ቤቱ መባህበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መገለጫ ላይ ጠቅሷል ። አሽከርካሪዎች ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ቅድሚያ ስልጠና ይወስዳሉ ተብሏል ። በዚሁ መሰረት ይህንን ሀገራዊ ፕሮጀክት በይፋ ወደ ትግበራ ለማስገባት በተለይም አጠቃላይ የአሽከርካሪዎች ምዝገባ እና ስ
May 261 min read


የአፍሪካ ቀን
ግንቦት 18/2018 አፍሪካ በምዕራባውያን ሚዲያ የግጭትና የረሃብ ቀጠና ተደርጋ በመሳሏ ምክንያት ለኢንቨስትመት አመቺ ካልሆኑ አህጉራት መካከል በመሆኗ በየዓመቱ 4.2ቢሊዮን ዶላር እንደምታጣ ጥናት አሳየ፡፡ በየዓመቱ ግንቦት 17 የአፍሪካ ቀን የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት) እ.ኤ.አ በ1963 በዚህ ቀን መመስረቱን ተከትሎ የአፍሪካ ቀን ተብሎ ይከበራል። የዘንድሮውን የአፍሪካ ቀን Africa no filter የተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት "አፍሪካ እየጠበቀች አይደለም"የሚል የሚዲያ ዘመቻ በማስጀመር 63ኛውን የአፍሪካ ቀን በትላንትናው እለት አክብሯል፡፡ አፍሪካ በምዕራባውያን ሚዲያ ለዘመናት የረሃብና የሰቆቃ ምልክት ተደርጋ ስትገለፅ ቆይታለች ያሉን የአፍሪካ ኖ ፊልተር ዋና ዳይሬክተር ሞኪ ማኩራ ናቸው፡፡ ድርጅታቸው
May 262 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

