top of page


''በትግራይ ክልል ይደረጋል ተብሎ የታሰበው የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ልየታ ለምን ዘገየ?'' የህዝብ እንደራሴዎች
የካቲት 12/2018 የህዝብ እንደራሴዎች በትግራይ ክልል ይደረጋል ተብሎ የታሰበው የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ልየታ ለምን ዘገየ? በእስር ላይ የሚገኙ የአማራ ሊሂቃን ከእስር ተፈተው በምክክሩ እንዲሳተፉ ያደረጋችሁን ጥረት ውጤት ለምን ለህዝብ አላሳወቃችሁም? ሲሉ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን ጠየቁ፡፡ ኮሚሽኑ በበኩሉ በትግራይ ክልል 20 ጊዜ ተሳትፎ መደረጉን ከዚህ በኋላ ፈቃደኞችን ይዞ የአጀንዳ ልየታውን እንደሚያደርግ ተናግሯል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ምህረት ስዩም የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://s
Feb 191 min read


የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች መዋዕለ ነዋያቸውን ፈሰስ ለሚያደርጉ ባለሀብቶች እምነት እንዲያደርጉ ቢያስችላቸውም በየጊዜው የሚለዋወጡ ህጎች ግን አሁንም ችግር ሆኖ ቀጥሏል ተባለ፡፡
የካቲት 12/2018 ኢትዮጵያ እያደረገቻቸው ያሉ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በሀገሪቱ መዋዕለ ነዋያቸውን ፈሰስ ለሚያደርጉ ባለሀብቶች እምነት እንዲያደርጉ ቢያስችላቸውም በየጊዜው የሚለዋወጡ ህጎች ግን አሁን ኢንቨስት ለሚያደርጉ ችግር ሆኖ ቀጥሏል ተባለ፡፡ ከውጭ የሚመጣ ሀብት በተወሰኑ ዘርፎች ላይ ብቻ ማዋሉም ሌሎች ዘርፎች በቂ ፋይናንስ እንዳያገኙ ከልክሏል ተብሏል፡፡ እንደ ትምህርት ፣ ጤና ፣ አነስተኛ እና ጥቃቅን ስራ ፈጠራ በመሳሰሉ ማህበራዊ ዘርፎች የሚሳተፉና ተዕኖ የሚያሳድሩ፣ ትርፍም የሚያገኙ ተቋማት የኢንቨስትመንት ሁኔታ ምን ይመስላል በሚል የተደረገ የምክክር መድረክ ላይ ነው ወሬው የሰማነው፡፡ ዝግጅቱን ያሰናዳው ACE investment እና Impact Advisors የተባለ የኢትዮጵያ ተቋም ከአለም አቀፉ አቀፍ GSG ተቋም ጋ
Feb 191 min read


በኢትዮጵያ በየዓመቱ በኤችአይቪ ከሚያዙ ሰዎች መካከል የአፍላ ወጣት ሴቶች ቁጥር ከፍተኛ ሆኗል ተባለ፡፡
የካቲት 12/2018 በኢትዮጵያ በየዓመቱ በኤችአይቪ ከሚያዙ ሰዎች መካከል የአፍላ ወጣት ሴቶች ቁጥር ከፍተኛ ሆኗል ተባለ፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ምህረት ስዩም የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx X :- https://x.com/shegerfm?s=2 LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv Instagram: https://shorturl.at/9X4
Feb 191 min read


የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም ለኢትዮጵያ የፅልመት ቀን ነበር፡፡
ታሪክን የኋሊት የካቲት 12 / 2018 ዓ.ም የካቲት 12 ቀን 1929 ለኢትዮጵያ የፅልመት ቀን ነበር፡፡ የስቃይና የመከራ ውርጅብኝ በኢትዮጵያዊነታቸው ብቻ የተቀበሉበት ቀን ነበር፡፡ የካቲት 12 የዋለው አርብ ነበር፡፡ የኢጣሊያው ልዑል ልጅ በመውለዱ ለድሆች ምፅዋት ይሰጣል ተብሎ ተነገረ፡፡ በዛሬው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በዚያን ጊዜ ገነት ልዑል ቤተመንግስት፣ ድሆችና ታዋቂ የከተማ ነዋሪዎች ተጠሩ፡፡ ለዝንተዓለም በባዕድ ተገዝታ የማታውቀው ኢትዮጵያ ክብሩዋ ተገሶ፣ ወሰኗ ተደፍሮ፣ በፋሰሽት ኢጣሊያ መወረሩዋ እንደ እግር እሳት የሚያንጋበግባቸው ሁለቱ ወጣቶች አበርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም በዚያው ቤተመንግስት ተገኝተዋል፡፡ ሁለቱ ጓደኛሞች ከአጣሊያኖች ጋር የሚሰሩ እንደመሆናቸው በቤተመንግስቱ መገኘታቸው የተለመደ ነው፡፡ ያልተለመደው ያንለት እዚያ የ
Feb 192 min read


የቡና ዓይነቶች ጣዕም፣ የቀለም እና የዋጋ ልዩነታቸው ታዲያ ከየት መጣ?
የካቲት 11/2018 ኢትዮጵያ የከፋ፣ የጅማ፣ የሀረር እና ይርጋ ጨፌ የቡና ዝርያዎች መገኛ ሀገር ናት፡፡ እነዚህ የቡና ዓይነቶች መነሻቸው አንድ ፤ ዝርያቸውም ተመሳሳይ፣ መሆኑን የዘርፉ ባለሞያዎች ይናገራሉ፡፡ የጣዕም፣ የቀለም እና የዋጋ ልዩነታቸው ታዲያ ከየት መጣ? ተመራማሪዎች በማስረጃ፣ የታሪክ ምሁራን በቅርስ፣ አርኪ ኦሎጂስቶችም በመሬት ውስጥ ምስክርነት ሌላውም ሌላውም አለኝ ያለውን ማስረጃ በማቅረብ ኢትዮጵያ ቡናን ለአለም ያስተዋወቀች ምድር ስለመሆኗ ይሞግታሉ። የቡና ርስት ኢትዮጵያ ስለመሆኗ ሳይንስም፣ ታሪክም፣ ቢያረጋግጥም፣ መጠሪያው 'ኮፊ አረቢካ' መሰኘቱን ብዙዎች በቁጭት ይናገሩታል፡፡ “ኮፊ አረቢካ” የሚለዉን ስያሜ ያገኘው የቀደምት የአረብ ነጋዴዎች ከኢትዮጵያ ወስደው በራሳቸው ስም ሰጥተው መጠሪያው እንዳደረጉ
Feb 182 min read


ተቋማት ተፈላጊ እንዲሆኑ ለማስቻል ተቋማትን የሚመዝንበትን ሞዴል እየከለሰ መሆኑን የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ተናገረ፡፡
የካቲት 11/2018 ተቋማት በአለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እና ተፈላጊ እንዲሆኑ ለማስቻል ተቋማትን የሚመዝንበትን ሞዴል እየከለሰ መሆኑን የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ተናገረ፡፡ የሽልማት ድርጅቱ በሀገር ውስጥ ያሉ አምራች እና አገልግሎት ሰጭ ተቋማት በአለም አቀፍ የገበያ መድረክ ላይ ብቁ እና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ አለም አቀፉ ገበያ የሚፈልጋቸው አዳዲስ መመዘኛ ሞዴሎችን አካትቻለሁ ብሏል፡፡ ከዚህ ቀደም ተቋማት ሲመዘኑ በመስፈርትነት ያልተካተቱ ፤ የአሰራር ሥርዓቶች እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በተመለከተ አዲስ በተከለሰው ሞዴል እንዲካተቱ መደረጉንም ሰምተናል፡፡ ለአብነት ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመረዳት እና መጠቀምን እንደ አንድ መመዘኛ እንዲሆን መደረጉም ተነግሯል፡፡ ይህን የነገሩን የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ዋና ስራ አስፈ
Feb 181 min read


የአፈርን ለምነትና ጤናማነት በመጨመር የተሻለ ምርት እንዲገኝ የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎች ስራ ላይ እየዋሉ ነው ተባለ ፡፡
የካቲት 11/2018 የአፈርን ለምነትና ጤናማነት በመጨመር የተሻለ ምርት እንዲገኝ የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎች ስራ ላይ እየዋሉ ነው ተባለ ፡፡ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ግብርናና እንስሳት ህክምና ኮሌጅ እየተተገበረ ያለው ይህ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ እየተራቆተ እና ምርት እየራቀው የመጣውን ለግብርና የሚውል መሬት ለምነት ለመመለስ ያግዛል ተብሏል፡፡ ይህ ባዮቻር የተባለው ቴክኖሎጂ እየተራቆተ የመጣውን የእርሻ መሬት ለማከም እንደሚረዳ የነገሩን በጅማ ዩንቨርስቲ ግብርናና የእንስሳት ህክምና ኮሌጅ ውስጥ መምህርና ተመራማሪ እንዲሁም የአፈር ለምነት ለማስጠበቅ የተለያዩ ጥናቶችን ያደረጉት ዶ/ር ሚልክያስ አህመድ ናቸው፡፡ የእርሻ መሬት ከጊዜ ወደ ጊዜ የተፈጥሮ ማዳበሪያን በመጠቀም እንኳን የሚፈልገውን ያክል ምርት መስጠት እየቻለ አይደለም የሚሉት ዶ/ር ሚልክያስ
Feb 181 min read


ሰራተኛ ቀጥረው የሚያስጠብቁ የግል ኤጅንሲዎች
የካቲት 11/2018 በአዲስ አበባ ባንኮችን፣ የግል ተቋማትን፣ የመንግስት መስሪያ ቤቶችን ሌላም ሌላም እንዲጠብቁ ሀላፊነት ወስደው፣ ህጋዊ ፍቃድ ተቀብለው፣ ሰራተኛ ቀጥረው የሚያስጠብቁ የግል ኤጅንሲዎች ቁጥር 250 ደርሷል ተብሏል። በእነዚህ ኤጀንሲዎች ስር ተቀጥረው ዩኒፎርም ለብሰው፣ ዱላ ታጥቀው የሚጠብቁት የመስሪ ቤቱ ንብረት እንዳይዘረፍ፣ ተቋሙ ጥቃት እንዳይደርስበት በር ላይ ቁመው የሚቆጣጠሩ፣ ሰራተኛው ሲገባ ፍትሸው የሚያስገቡ፣ ሲወጣ አይተው የሚሸኙ ካላቸው ሀላፊነት ከተሰጣቸው የስራ ድርሻ አንጻር የሚከፈላቸው ደመወዝ ለእለት ጉርስ የሚበቃ እንዳልሆነ ይጠቀሳል። ብዙዎቹ በየቀኑ በሚሊዮን ሚቆጠር ብር ሲገባ ሲወጣ የሚውልበትን ባንክ እየጠበቅን የምንቀበለው ክፍያ ለቤት ኪራይ የመክፈል አቅም ያለው አይደለም፡፡ ደግሞም ኤጅንሲዎች ከተቋሙ የሚቀበሉ
Feb 181 min read


ኢራን የሆርሙዝ ሰርጥን በጊዜያዊነት መዝጋቷ ተሰማ ።
የካቲት 11/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #ኢራን ኢራን የሆርሙዝ ሰርጥን በጊዜያዊነት መዝጋቷ ተሰማ ። ሰርጡ የተዘጋው *የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ* በአካባቢው የባህር ሃይል ልምምድ ስለሚያደርግ ነው ተብሏል። ልምምዱ አሜሪካ በአረብ ባህር አካባቢ ወታደራዊ አቅሟን እያደረጀች መምጣቷን ተከትሎ የሚካሄድ እንደሆነ ዘ ቴሌግራፍ ጽፏል። ዋሽንግተን አውሮፕላን ተሸኳሚ የጦር መርከብን ጨምሮ ወታደሮችን ከዘመን አፈራሽ የውጊያ መሳሪያዎች ጋር ወደ አካባቢው መላኳ ተነግሯል። የኢራን እርምጃ ሁለቱ ሀገራት አለመግባባታቸውን ለመፍታት በጄኔቫ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ላይ እያሉ የተሰማም ነው። ኢራን የሆርሙዝ መተላለፊያን ስትዘጋ እንደ ጎርጎርሳውያኑ አቆጣጠር ከ1980ዎቹ ወዲህ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ተብሏል። #ሩሲያ ሩሲያ በባልቲክ ሀገራት ላይ ወረራ ከፈ
Feb 181 min read


''ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ዘርፍ ብድር የምትፈልጉ ኑ ወደ እኔ በቂ የብድር ገንዘብ ተዘጋጅቶላችኋል'' የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
የካቲት 11/2018 ''ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ዘርፍ ብድር የምትፈልጉ ኑ ወደ እኔ በቂ የብድር ገንዘብ ተዘጋጅቶላችኋል'' ሲል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጥሪ አቀረበ። ባንኩ በዚህ ዘርፍ በአሁኑ ሰዓት ብዙ የብር ጥያቄዎች የሉብኝም ብሏል። ባንኩ ይህን ያለው በረመዳን ወር የእልምና እምነት ተከታይ ደንበኞቹ ዘካ ለመስጠት የሲቢኢ ኑር የዘካ ቁጠባ ሂሳብን እንዲገለገሉ ጥሪ ባቀረበበት ፕሮግራም ላይ ነው፡፡ ባንኩ ‘አብሮነትና በጎነት በረመዳን' ሲል የጠራውን ፕሮግራም በዛሬው እለት አስጀምሯል። የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል የዘካ ቁጠባ ሂሳብ አንዱ መሆኑን አስታውሰው በተለይ በረመዳን የእምነቱ ተከታዮች እንዲገለገሉበት ጥሪ አቅርበዋል፡፡ አገልግሎቱ የዘካ ሰጪና ተቀባዮችን ጊዜ፣ ወጪ፣ ልፋትና
Feb 181 min read


ኢትዮጵያ የባህር በር በሰላማዊ መንገድ እንድታገኝ ቱርክዬ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ጫና እንድታደርግ ከቱርክዬ ፕሬዚዳንት ጋር ጠንከር ያለ ውይይት ማድረጋቸውን ጠ/ሚ ዐቢይ ተናገሩ።
የካቲት 11/2018 ኢትዮጵያ የባህር በር በሰላማዊ መንገድ እንድታገኝ ቱርክዬ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ጫና እንድታደርግ ከቱርኩ ፕሬዚዳንት ጋር ጠንከር ያለ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ከቱርኩ ፕሬዚዳንት ሪሲፕ ታይፕ ኤርዶዋን ጋር ሆነው በቤተመንግስት መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው ኢትዮጵያ የባህር በር በሰላማዊ መንገድ ማግኘት የምትችልበት ሁኔታ ለይ ቱርክዬ በዲፕሎማሲያዊ መስኩ ጫና በመፍጠር እንዲያግዙ ከፕሬዝዳንት ኤርዶዋን ጋር ተወያይተናል ብለዋል። ፕሬዚዳንት ኤርዶዋን ከዚህ አንፃር የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ጠንከር ያለ ውይይት አደርገናል፣ ለዚህም ምስጋና አቀርባለሁ ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ከዚህ በተጨማሪም በኢትዮጵያ እና በቱርክዬ መካከል ያለው ዓመታ
Feb 181 min read


የተከለከለው ትልቅ ትንሽ፤ ወፍራም ስስ ተብሎ ሳይሆን ሁሉም አይነት የፕላስቲክ ከረጢት መሆኑን የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ተናገረ፡፡
የካቲት 10/2018 የተከለከለው ትልቅ ትንሽ፤ ወፍራም ስስ ተብሎ ሳይሆን ሁሉም አይነት የፕላስቲክ ከረጢት መሆኑን የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ተናገረ፡፡ ባለስልጣኑ ሁሉንም አይነት የከረጢት ፕላስቲክ ይዞ የተገኘ በአዋጅ 1383/2017 መሰረት ከ2000 ብር በማያንስ እና ከ5000 ብር የማይበልጥ ገንዘብ እንደሚቀጣ አሰረድቷል፡፡ የአካባቢ ጥበቃ በለስልጣን "ህግን እናውቃለን" በማለት የተከለከለው ስስ ፌስታል ብቻ ነው ከሚሉ አሳሳች አካላት ህብረተሰቡ እራሱን እንዲጠብቅ አሳስቧል፡፡ ባለስልጣኑ ይህን ያሳሰበው ዛሬ የፕላስቲክ ከረጢትን የሚተካ ከፕላስቲክ ውጭ ከረጢቶችን ከሚያመርቱ አካላት ጋር ባካሄደው ውይይት ላይ ነው፡፡ በውይይቱ ላይ ፕላስቲክ በአገር ኢኮኖሚ፣ጤና እና ማህበራዊ ጉዳይ ላይ እያደረሰ ያለውን ቀውስ አስመልክተው የውይይት መ
Feb 172 min read


አንዳንድ የጸጥታ ችግር ባሉባቸው አካባቢዎችና የጤና አገልግሎት መስጫ ባልተስፋፋቸው ቦታዎች የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት በሚፈለገው ልክ እየተተገበረ አይደለም ተባለ፡፡
የካቲት 10/2018 አንዳንድ የጸጥታ ችግር ባሉባቸው አካባቢዎችና የጤና አገልግሎት መስጫ ባልተስፋፋቸው ቦታዎች የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት በሚፈለገው ልክ እየተተገበረ አይደለም ተባለ፡፡ ከጸጥታ ስጋቱ በተጨማሪ ስለአገልግሎቱ የሚሰጡ የተሳሳቱ አስተያየቶችም ችግር መሆኑ ተነግሯል፡፡ የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት መጠቀም ቢፈልጉም በተለያየ ምክንያት ዕክል የገጠማቸው አፍላ ወጣቶች ላይ በማተኮር አገልግሎቱ እንዲስፋፋ እያደረገ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡ በቅርቡ በተከወነ ጥናት በሀገሪቱ የውልደት ምጣኔው መቀነሱ የተነገረ ቢሆንም አሁንም ግን የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎቱን ማስፋፋት ላይ የሚቀሩ ስራዎች አሉ የሚሉት በጤና ሚኒስቴር የስነ ተዋልዶ ጤና የቤተሰብ ዕቅድና የወጣቶች ፕሮግራም ሀላፊ የሆኑት ዶክተር አለማየሁ ሁንዱማ ናቸው፡፡ በተጨ
Feb 171 min read


የትምህርት ስርዓት በቴክኖሎጂ የሚያግዙ (EdTech) ስራ ፈጣሪዎች ያመጧቸው መፍትሔዎች ውጤት እያመጡ መሆኑ ተሰማ።
የካቲት 10/2018 የትምህርት ስርዓት በቴክኖሎጂ የሚያግዙ (EdTech) ስራ ፈጣሪዎች ያመጧቸው መፍትሔዎች ውጤት እያመጡ መሆኑ ተሰማ። በተለይ ትምህርት በቅጡ በማይሰጥባቸው ተፈናቃይና ስደተኛ መጠለያ ጣቢያዎች ላሉ ተማሪዎች፣በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም ሂሳብና ቋንቋ ትምህርት ዘርፎች በቴክኖሎጂ የታገዙ የትምሀርት አሰጣጦች ውጤት እያስገኙ መሆኑ ተጠቅሷል። ከሰሞኑ ሪች ፎር ቼንጅ ነዋ? በተባለ ግብረሰናይ ድርጅ ስለጠናም የገንዘብ ድጋፍም የሚደረግላቸው ትምህርትን በቴክኖሎጂ የሚያቀብሉ ፈጣሪዎች ሀሳባቸውን ለፖሊሲ አውጪዎች ለትምህርት ዘርፍ ተዋኒያን ያስተዋወቁበት መድረክ ተካሂዷል። ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube :
Feb 171 min read


በአማራ ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች በቀጠለ የሰላም እጦት ምክንያት የትምህርት ሥርዓቱ ጫና ውስጥ ወድቋል፡፡
የካቲት 9/2018 በሰሜኑ ጦርነት እና አሁንም በአማራ ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች በቀጠለ የሰላም እጦት ምክንያት የትምህርት ሥርዓቱ ጫና ውስጥ ወድቋል፡፡ ባለፉት አራት እና አምስት አመታት በክልሉ በነበሩ፣ አሁንም ድረስ በቀጠሉ ሰላም እጦቶች እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉ ችግሮች ምክንያት ዘርፉ በብዙ ውጣ ውረድ እያለፈ ነው ያለው የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ለዚህም ድጋፍ እሻለሁ ብሏል፡፡ በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ከ4 ሺህ ትምህርት ቤቶች በላይ ጉዳት የደረሰበት የክልሉ ትምህርት ቢሮ ከነበረበት ችግር ሳያገግም አሁንም ድረስ በቀጠለው የሰላም እጦት ምክንያት ትምህርት ቤቶች ጉዳት እየደረሰባቸው እንደሆነ ነግሮናል፡፡ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ጉዳት የደረሰባቸው ትምህርት ቤቶች እንዳሉ ያነሱት የትምህርት ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ጌ
Feb 161 min read


የፎርዋርድ የውጭ ምንዛሪ ግብይት ያለ ብሔራዊ ባንክ ማረጋገጫ ማካሄድ እንዲችሉ መፍቀዱ ነው፡፡
የካቲት 9/2018 በቅርቡ ብሔራዊ ባንክ በውጭ ምንዛሪ መመሪያ ላይ በ19 ጉዳዮች ላይ ማሻሻያዎች ካደረገባቸው ጉዳዮች መካከል የፎርዋርድ የውጭ ምንዛሪ ግብይት ያለ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማረጋገጫ ማካሄድ እንዲችሉ መፍቀዱ ነው፡፡ ይህ ማለት አንድ ነጋዴ አንድ ሺህ ዶላር የሚያወጣ ሰሊጥ ወደ አረብ ሀገር ቢልክ ከባንኮች ጋር የላከው ሰሊጥ ገበያ ላይ ተሽጦ የሚመጣው የውጪ ምንዛሪ ከወዲሁ ባንኩ የሚገዛበትን ዋጋ መዋዋል ይችላል፡፡ ይህ ሲያደርግ ውል የተስማሙበት ጊዜ እና ሰሊጡ የተሸጠበት ወቅት ያለው የውጪ ምንዛሪ ዋጋ ከፍና ዝቅ ማለት የሚፈጥረውን ስጋት ከወዲሁ ለማስቀረት ይረዳል ተብሏል፡፡ አቶ ጥላሁን ግርማ የፋይናንስ ኢኮኖሚ እና የኢንቨስትመንት አማካሪ ናቸው፡፡ የፎርዋርድ የውጪ ምንዛሪ ግብይት በፅሁፍ የተፈቀደ ነገር እስካሁን አልተመለ
Feb 162 min read


ወባ ስርጭትን ከአፍሪካ በፈረንጆቹ 2030 ለማጥፋት በአፍሪካ ህብረት የተያዘውን ግብ ለማሳካተት የሚያስችል ስራ አባል አገራት እየሰሩ እንዳልሆነ ተነገረ።
የካቲት 9/2018 ወባ ስርጭትን ከአፍሪካ በፈረንጆቹ 2030 ለማጥፋት በአፍሪካ ህብረት የተያዘውን ግብ ለማሳካተት የሚያስችል ስራ አባል አገራት እየሰሩ እንዳልሆነ ተነገረ። በፈረንጆቹ 2030 የወባን ስርጭት ከአህጉሪቱ ወደ ዞሮ ለማውረድ ግብ ተቀምጦ የነበረ ቢሆንም የበሽታው ስርጭት መጠን እና በህመሙ በሚሞተው ሰው መጠን አፍሪካ አሁንም ከአለም ቀደማሚውን ስፍራ ትይዛለች። በአለም ጤና ድርጅት ሪፖርት መሰረት በ 2024 በአለም አቀፍ ደረጃ ካለው የወባ ስርጭት ወይንም የተጠቂ መጠን 96 በመቶ ወይንም ከ270 ሚሊዮን በላይ በአፍሪካ ሲሆን ፤በበሽታው ሕይወቱን ከሚጣው የአለማችን ህዝብ ደግሞ 97 በመቶ በአፍሪካ ህብረት አባል አገራት የሚመዘገብ መሆኑን ይዘረዝራል። የ2025 የአፍሪካ የወባ ህመም ክትትል ሪፖርት እንደሚያሳየው 270 ሚሊየን በላይ የ
Feb 161 min read


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ምክር ቤት እና የአደጋ ጊዜ ፈንድ ማቋቋሚያ ደንብ
የካቲት 9/2018 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ምክር ቤት እና የአደጋ ጊዜ ፈንድ ማቋቋሚያ ደንብ የመንግስት ሰራተኛው እና ተሿሚዎች ከወር ደመወዛቸው 0.5 በመቶ እንዲቆረጥባቸው ያስገድዳል፡፡ የሚሰበሰበው ገንዘብ በከተማዋ ለሚያጋጥሙ የሰው ሰራሽ እና የተፈጥሮ አደጋዎች በራስ አቅም ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚውል መሆኑ ተነግሯል፡፡ ደንቡ ከሃይማኖት ተቋማት በየዓመቱ ከእያንዳንዱ አጥቢያ 12 ሺህ ብር ፣የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ፍቃድ ሲያወጡ እና ሲያድሱ በዓመት 5 ሺህ ብር፣ የከተማዋ ነዋሪ ከውሃ ክፍያ ጋር የሚታሰብ በወር 5 ብር ተደምሮ እንዲከፍል ያዛል፡፡ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች የመጠባበቂያ ዕቅድ መነሻ በድህረ አደጋ ወቅት ከአደጋ ጉዳት ለማገገም፣ የአስቸኳይ ጊዜ ሰብዓዊ ዕርዳታ ለማቅረብ ፣ ለመልሶ ግንባታና
Feb 162 min read


የካቲት 9/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
የካቲት 9/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #እስራኤል የእስራኤል መንግስት የሀገሪቱ ዜጎች በቀላሉ በዌስት ባንክ መሬት እንዲገዙ የሚያስችል ህግ አፀደቀ። ህጉ እስራኤላውያን ግለሰቦች በዌስት ባንክ መሬት እንዲገዙ የሚፈቅድ ሲሆን ከገዙት መሬትም የተወሰነውን ለሀገሪቱ የመንግስት አስተዳደር ማስተላለፍ እንደሚችሉ ይደነግጋል። ህጉ እስራኤል በዌስት ባንክ የምታካሂደውን የአይሁዶች የሰፈራ ፕሮግራም ለማጠናከር ታስቦ የተዘጋጀ ነው በሚል ከተለያዩ ወገኖች ትችት እየቀረበበት ይገኛል። የአውሮፓ ህብረት አባላት እና የአረብ ሀገራት ትችቱን ከሰነዘሩት መካከል እንደሆኑ DPA international ዘግቧል። የእስራኤል መንግስት ግን ህጉ የዜጎችን ሃብት የማፍራት መብት ታሳቢ አድርጎ ብቻ የተዘጋጀ ነው ብሏል። #ሱዳን የሡዳን ጦር በምዕራብ ኮርዶፋን የነበረን የፈ
Feb 161 min read


ከ940 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ወጥቶባቸው የተገነቡ ከፀሀይ የኤሌክትሪክ ሀይል የሚያመነጩ 4 ፕሮጀክቶች ወደ ስራ መግባቸው ተነገረ፡፡
የካቲት 9/2018 ከ940 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ወጥቶባቸው የተገነቡ ከፀሀይ የኤሌክትሪክ ሀይል የሚያመነጩ 4 ፕሮጀክቶች ወደ ስራ መግባቸው ተነገረ፡፡ በሶማሌ ክልል የዲግ፣ የኑስደሪቅ፣ የጋሻሞ እና የምርቃን ከጸሐይ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በላከልን መግለጫ ጠቅሷል፡፡ አራቱ ፕሮጀክቶች በድምሩ 1.8 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ያላቸው ሲሆን፤ ለፕሮጀክቶቹ ግንባታ 20.42 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር ዝርጋታ፣ 78 .46 ኪ.ሜ ዝቅተኛ መስመር ዝርጋታ እንዲሁም 21 የተለያዩ አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች ተተክለዋል ብሏል፡፡ ፕሮጀክቶቹ የጤና እና የትምህርት ተቋማትን ጨምሮ ከ9500 በላይ ደንበኞችን የ24 ሰዓት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ የሚያደርጉ ናቸው
Feb 162 min read


የገልፍ ሃገራትን ዘንግቶ የቆየው የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ መንገድ (ክፍል 3)
የካቲት 9/2018 #ጉዳያችን - የገልፍ ሃገራትን ዘንግቶ የቆየው የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ መንገድ (ክፍል 3) ኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ያሉ የገልፍ ሃገራት ቱሪስቶችን ለመሳብ ምን መስራት አለባት? እስካሁንስ የዘነጋችው ስራ ምንድን ነው? በጉዳዩ ላይ የታሪክ ተመራማሪው አደም ካሚል(ፕ/ር) የሰጡንን ማብራሪያ ያድምጡ…. ቴዎድሮስ ወርቁ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx X :- https://x.com/
Feb 161 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

