top of page
በአለም አቀፍ ደረጃ የለጋሾች ድጋፍ በመቀነሱ ኢትዮጵያን ጨምሮ በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ዘላቂ ለውጥን ለማምጣት የሚያስችል የበጎ አድራጎት ተቋም መገንባት እንዳለባቸው ተመከረ፡፡
ሰኔ 10/2018 በአለም አቀፍ ደረጃ የለጋሾች ድጋፍ በመቀነሱ ኢትዮጵያን ጨምሮ በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ዘላቂ ለውጥን ለማምጣት የሚያስችል የበጎ አድራጎት ተቋም መገንባት እንዳለባቸው ተመከረ፡፡ ለዚህም በመንግስትና በግሉ ዘርፍ መካከል ትብብር መፍጠር ሀገር በቀል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን ማጠናከር እና ማስፋፋት እንደሚያስፈልግ ተነግሯል። ይህ የተነገረው ዛሬ በአዲስ አበባ በተጀመረው የምስራቅ አፍሪካ የበጎ አድራጎት ኮንፈረንስ ላይ ነው። በመድረኩ የበጎ አድራጎት ዘርፍ ላይ የድጋፍ መቀነስ በተለይ ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ ሀገራት የሚገጥሟቸውን ችግሮች ፣ እየተፈጠሩ ያሉ አዳዲስ ለውጦችና በቀጣናው ዘላቂ ልማት ማምጣት ላይ ያተኮሩ ውይይቶች የሚካሄዱበት እንደሆነ ተነግሯል። ኢትዮጵያ እንደ ዩኤስኤአይዲ(USAID) ያሉ የእርዳታ ተቋማት የሚደረግ
6 days ago1 min read


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአንድ ጊዜ 24 መኪኖችን ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያን ወደ ስራ አስገባ።
ሰኔ 10/2018 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአንድ ጊዜ 24 መኪኖችን ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያን ወደ ስራ አስገባ። አገልግሎቱ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን (IPDC) ጋር በመተባበር በአንድ ጊዜ 24 የኤሌክትሪክ መኪኖችን አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ፈጣን ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያ ገንብቶ ወደ ስራ አስገብቷል። ተቋሙ ግዙፍ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎችን በራሱ እና ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ እና በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ለመገንባት በስፋት እየሰራ መሆኑን የአገልግሎቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው ተናግረዋል። በመጋቢት ወር ስራ ከጀመሩት የኮተቤ እና የፒያሳ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች በተጨማሪ አሁን ደግሞ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር በመተባበር ወደ ስራ ያስገባቸው ጣቢያዎች መኖራቸውን ያነሱት ዋና
6 days ago1 min read


በአዲስ አበባ 21 የቅጥር ኤጀንሲዎች መታገዳቸው ተሰምቷል
ሰኔ 10/2018 በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተያዘው በጀት ዓመት ህጋዊ ፈቃድ ካላቸው የቅጥር ኤጀንሲዎች መካከል 21ዱ መታገዳቸው እና ፤ የ3ቱ ደግሞ ፍቃዳቸው መሰረዙ ተሰምቷል፡፡ 100 የሚሆኑ ኤጀንሲዎች ደግሞ ስራቸውን በአግባቡ አልከወኑም ህጋዊነትንም አልተከተሉም ተብለው ጉዳቸው በቢሮው የማኔጅመንት እየታየ ይገኛል ተብሏል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውስጥ በህጋዊ መንገድ ተመዝግበውና ፈቃድ አውጥተው የሚንቀሳቀሱ ወደ 384 የሚጠጉ የሰራተኛና አሰሪ አገናኝ ኤጀንሲዎች ይገኛሉ። የእነዚህ ኤጀንሲዎች ኃላፊነት ከተሰጣቸው ኃላፊነት ውጭ የሚሰሩ፣ ለሰራተኞች ተገቢውን ደመወዝ የማይከፍሉ፣ እንዲሁም ሰራተኞች ዓመታዊና የወሊድ ፈቃድ በሚወስዱበት ወቅት ደመወዝ የሚቀንሱ ኤጀንሲዎች ላይ ከዕገዳ እስከ ፈቃድ ስረዛ የሚደርስ ጥብቅ እርምጃ እየተወሰደ ነ
6 days ago1 min read


1.5 ቢሊዮን ብር ከግብር ለመሰብሰብ መታቀዱስ ምን ያህል ያስኬዳል ?
ሰኔ 9/2018 የኢትዮጵያ የመጪው ዓመት በጀት የመካከለኛው ምስራቅ ያሳደረውን ጫና ከግምት ያስገባ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡ ከዚህባልተናነሰ በሀገር ቤት በተለያዩ አካባቢዎች አሁንም የቀጠለው ወታደራዊ ግጭት ምርትና ምርታማነት ላይ ጫና የሚያሳድር በመሆኑ በጀቱን በአግባቡ ስራ ላይ አውሎ ኢኮኖሚው ላይ ለውጥ ለማምጣት ሰላም ላይ መስራት ያስፈልጋል ተብሏል፡፡ የሰዎች ገቢ በተገቢው ሁኔታ ሳይጨምር የ1.5 ትሪሊዮን ብር ከግብር ለመሰብሰብ መታቀዱስ ምን ያህል ያስኬዳል? የሚል ጥያቄም ያስነሳል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ… ያሬድ እንዳሻው
7 days ago1 min read


በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ግብአትን ጨምሮ የተለያዩ ችግሮች እንደተፈቱላቸው ተነግሯል፡፡
ሰኔ 9/2018 በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ግብአትን ጨምሮ የተለያዩ ችግሮች እንደተፈቱላቸው ተነግሯል፡፡ በሌላ በኩል ዛሬም ግብአቶች ከውጪ የሚያስገቡ አምራች ኢንዱስትሪዎች አሉ ተብሏል። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ስራ ያቆሙ ፋብሪካዎች ወደ ማምረት እንዲመለሱ ማስቻል እንደሆነ ይነሳል። ያሉባቸው የመሬት፤ የብድር፤ የመሠረተ ልማትና የግብአት አቅርቦት ችግሮች ተፈትተውላቸው 800 የሚሆኑ ፋብሪካዎች ወደ ምርት መመለሳቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባለፈው ሚያዝያ ወር ተናግረዋል። አንዳንድ ፋብሪካዎች ስራ ባያቆሙም የማምረት አቅማቸው በጣም ዝቅተኛ እንደነበር ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ በዚህ ንቅናቄ የፋብሪካዎቹ የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ብቻ ወደ 67 በመቶ እንዲያድግ መደረጉን አመልክተዋል።
7 days ago2 min read


መድኃኒቶችን በአግባቡ አለመጠቀም፤ ዜጎች ወጪ አውጥተው ታክመውም እንዳይድኑ አንዱ ምክንያት እየሆነ ነው ተባለ፡፡
ሰኔ 8/2018 መድኃኒቶችን በአግባቡ አለመጠቀም፤ ዜጎች ወጪ አውጥተው ታክመውም እንዳይድኑ አንዱ ምክንያት እየሆነ ነው ተባለ፡፡ የሚታዘዙ መድኃኒቶችን በተገቢው እና በሀኪም ትዕዛዝ አለመወሰድ በሀገር ኢኮኖሚ ጉዳት እየደረሰ እና ዜጎችም ህይወታቸው እያጡ እንደሆነ ተነግሯል፡፡ ይህ ልማድ በተለይም የፀረ-ተህዋሲያን መድሃኒቶች ጀርሞች እንዲላመዷቸው ስለሚያደርግ፤ እያደረሰ ያለው ጉዳት ከፍተኛ እንደሆነ ተነግሯል፡፡ ይህንን ችግር ለመቀነስ ሰዎች የመድኃኒት አጠቃቀማቸው ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል ሲል የተናገረው የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ነው። ይህ ችግር ከኢትዮጵያም በተጨማሪ በአለም ደረጃ ስጋት እየሆነ ነው ተብሏል፡፡ የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መለመድ (Antimicrobial Resistance / #AMR Day) የግንዛቤ
7 days ago1 min read


በኢትዮጵያ በተፈጥሯዊው የወር አበባ ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው ከስራቸው የሚስተጓጎሉ ሴቶች ቁጥር ከፍተኛ ነው፡፡
ሰኔ 8/2018 በኢትዮጵያ በተፈጥሯዊው የወር አበባ ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው ከስራቸው የሚስተጓጎሉ ሴቶች ቁጥር ከፍተኛ ነው፡፡ በወር አበባ ምክንያት ከሚፈጠርባቸው ህመም በተጨማሪ ግን እለት ከለት እየናረ የመጣው የንጽህና መጠበቂያ ሞዴስ ዋጋ አሳሳቢ ሆኗል፡፡ በተለይ ዝቅተኛ የገቢ መጠን ያላቸው እንደ ኢንደስትሪ ፕርኮች ባሉ ቦታዎች ላይ የሚሰሩ ሴቶች በዚህ እየተቸገሩ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ የወር አበባ ጤና ቀንን አስመልክቶ ኤድስ ሄልዝ ኬር ፋውንዴሽን ወይም ኤ ኤች ኤፍ ኢትዮጵያ በአዳማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ባሰናዳው ዝግጅት ላይ ተገኝተን እንደሰማነው በንጽህና መጠበቂያ እጥረት ምክንያት 46 ከመቶ ሴቶች ከትምህርት ቤት ይቀራሉ፡፡ በሌላ በኩል በስራቸው ምክንያት ያልተመቸ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙና ህመም የሚገጥማቸው ሴቶችም በተፈጥሯቸው ሳቢያ ለብዙ ስቃ
Jun 152 min read


ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተነገረ፡፡
ሰኔ 8/2018 ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተነገረ፡፡ ዛሬ ሰኔ 8/2018 ማለዳ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ የሕዝብ ማጓጓዣ አውቶቡስ በተለምዶ ሐረጎ እየተባለ በሚጠራው መንገድ ላይ በደረሠበት አደጋ እስካሁን የ28 ሰው ሕይወት አልፏል ተብሏል፡፡ በአደጋው የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉ የተነገረ ሲሆን ከሞቱት ሰዎች በተጨማሪም በርካታ ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተጠቅሷል፡፡ አደጋ የደረሰበት የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው በግምት 100 ሜትር ጥልቀት ወዳለው ገደል ውስጥ መግባቱ ተነግሯል፡፡ በሕይወት የተረፉትን ወደ ሕክምና ቦታ ለማድረስ ርብርብ እየተደረገ ነው ሲል የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘግቧል፡፡ ንጋቱ ሙሉ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች
Jun 151 min read


ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ሐዋርያዊ ኃላፊነታቸውን አስረከቡ።
ሰኔ 5/2018 የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ እና የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ሐዋርያዊ ኃላፊነታቸውን አስረከቡ። ብፁዕ ካርናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ኃላፊነታቸውን ያስረከቡት በጡረታ ምክንያት እንደሆነ ቤተክርስቲያኗ አስታውቃለች፡፡ የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዎ 14ኛ ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ላቀረቡት ከሃላፊነት የመነሳት ጥያቄ፤ በዛሬው ዕለት መቀበላቸውን በቅድስት መንበር ልዩ መልዕክተኛ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ አማካይነት ይፋ መደረጉን በቤተክርስቲያኗ መግለጫ ላይ ተጠቅሷል፡፡ የብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ተተኪ በመሆን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ረዳት ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ተስፋስላሴ የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ ሆነው ተሹ
Jun 121 min read


በአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት የተሰማሩ ባለሃብቶች ለዓመታት ሲያቀርቡት የነበረው ለኢንቨስትመንት የሚውል መሬት ጥያቄ ምላሽ አግኝቷል ተባለ።
ሰኔ 5/2018 በአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት የተሰማሩ ባለሃብቶች ለዓመታት ሲያቀርቡት የነበረው የማስፋፊያ እና ለአዲስ ኢንቨስትመንት የሚውል መሬት ጥያቄ ምላሽ አግኝቷል ተባለ። በግብርና ሚኒስቴር ድጋፍ ለማስፋፊያ እና ለአዲስ ኢንቨስትመንት የሚውል ተጨማሪ 33,000 ሄክታር መሬት በተለያዩ ክልሎች መገኘቱ ተነግሯል፡፡ እስከ አሁን ልማቱ ሲካሄድ የቆየው በ12,000 ሄክታር መሬት እንደነበር ከኢትዮጵያ አበባ ፤ አትክልትና ፍራፍሬ አምራቾችና ላኪዎች ማህበር ሠምተናል። በኢትዮጵያ አሁን ላይ 120 የሚሆኑ ባለሃብቶች በአበባ ፤ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ተሰማርተው እንደሚገኙ ተነግሯል። እነዚህ ባለሃብቶች እየሰሩ ያሉት 12,000 ሄክታር መሬት ላይ እንደሆነ ከኢትዮጵያ አበባ ፤ አትክልትና ፍራፍሬ አምራቾች እና ላኪዎች ማህበር ዋና ዳይሬክተር አቶ ቴዎ
Jun 121 min read


በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የነዳጅ አቅርቦት ችግር የወርቅ ምርትን በ30 በመቶ እንዲቀንስ ምክንያት ሆኗል
ሰኔ 5/2018 የወርቅ ማዕድን ከሚመረትባቸው ክልሎች መካከል የሆነው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ የነዳጅ እጥረቱ፤ በወርቅ መገኘት የነበረበትን ገቢ እያሳጣ መሆኑን ተናገረ፡፡ ባለፉት 2 ወራት ብቻ የነዳጅ አቅርቦት ችግር የወርቅ ምርትን በ30 በመቶ እንዲቀንስ ምክንያት ሆኗል ብሏል፡፡ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ የማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ፤ የነዳጅ አቅርቦት ችግሩ ከባለፉት ወራት የተሻለ ቢሆንም አሁንም ግን ችግሩ በማዕድን ዘርፉ ላይ ጥላውን እንዳጠላበት ተናግሯል። በሌላ በኩል ክልሉ በዘንድሮው 9 ወራት 6222.5 ኪ.ግ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ማድረጉንም ሰምተናል። ባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከ47 ኩንታል በላይ ወርቅ ገቢ እንዳደረገም ተነግሯል። በዚህም አጠቃላይ በማዕድን ዘርፉ ከ83 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል ሲል ቢሮው ነግሮናል። የክልሉ የማዕድን
Jun 121 min read


በየቤት ሰራተኞች እና በአሰሪዎች መካከል የሚፈጠሩት መቃቃር፣ አለመተማመኖች እና ችግሮችን ለመፍታት
ሰኔ 5/2018 በየቤት ሰራተኞች እና በአሰሪዎች መካከል የሚኖርን አሰራር ህጋዊ ለማድረግ አዲስ ደንብ እየተዘጋጀ እንደሆነ ይታወቃል። ደንቡ እየተዘጋጀ ያለው በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ሲሆን ከሁለቱም ወገን ሊፈጠር የሚችልን አካላዊ እና ሥነ ልቦናዊ ጥቃቶችን ለመከላከል ያስችላል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ ይህንን ደንብ ማውጣት አንዱ መሰራት ያለበት ስራ ቢሆንም የቤት ሰራተኞች ወደ ስራ ከመግባታቸው በፊት እና አሰሪዎችም እነሱን ከመቅጠራቸው አስቀድሞ ስልጠና ቢወስዱ መልካም እንደሚሆን በጉዳዩ ላይ ጥናት ያደረጉ አንድ ባለሙያ ያስረዳሉ፡፡ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሁለቱም ወገን ያለው መቃቃር፣ አለመተማመኖች እና ችግሮች ክፍተቶቹ እየሰፉ መጥተዋል ያሉት ባለሙያው ህጉን ወረቀት ላይ ከማስፈር ባለፈ የሞያ ልምድ፣ ሰራተኞች ካሰሪዎቻቸው ጋር ስለሚደርጉት ተግባ
Jun 121 min read


ከምስራቅ ወለጋ በአዲስ መልክ ተፈናቅለናል ያሉ ሰዎች በደብረ ብርሃን በከፋ ችግር ውስጥ መሆናቸውን ተናገሩ፡፡
ሰኔ 5/2018 ከምስራቅ ወለጋ በአዲስ መልክ ተፈናቅለናል ያሉ ሰዎች በደብረ ብርሃን በከፋ ችግር ውስጥ መሆናቸውን ተናገሩ፡፡ የምስራቅ ወለጋ አደጋ ስጋት በበኩሉ አዲስ ከአካባቢው የተፈናቀለ የለም ብሏል፡፡ ከዚህ ቀደም ከተለያዩ የኦሮሚያ ክልል ተፈናቅለው በደብረብርሃን የመጠለያ ጣቢያ የሚኖሩ ተፈናቃዮች ከ5 ዓመት በላይ እንደሆናቸ እና ቁጥራቸ ከ26,000 በላይ እንደሆነ ሰምተናል፡፡ እነዚህ ተፈናቃዮች በቻይና፣ በወይንሸት፣ እንዲሁም በባቄሎ የመጠለያ ካምፖች ይገኛሉ፡፡ አሁን ደግሞ ከ3,000 በላይ የሚሆኑ ተፈናቃዮች ወደ ወይንሸት ካምፕ መምጣታቸውን ተከትሎ በብዙ መቸገራቸውን ከተፈናቃዮች ሰምተናል፡፡ አዳዲስ የገቡትን ተፈናቃዮች በምን ምክንያት ወደ ደብረብርሃን ሄዳችሁ ስንል ጠይቀናቸዋል፡፡ እነሱም በነበሩበት ምስራቅ ወለጋ አሁንም የጸጥታ ችግር እ
Jun 121 min read


በመጪው ዓመት የመንግስትን ገቢ ለማሳደግ ያግዝ ዘንድ ከታክስ ነፃ እና የግብር እፎይታ አሰራሮች ሊቀሩ መሆኑ ተሰምቷል፡፡
ሰኔ 5/2018 በመጪው ዓመት የመንግስትን ገቢ ለማሳደግ ያግዝ ዘንድ ከታክስ ነፃ እና የግብር እፎይታ አሰራሮች ሊቀሩ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ በዚህም ከዚህ ቀደም ከጉምሩክ ቀረጥ ነፃ ተደርገው ወደ ሀገር ይገቡ የነበሩ እቃዎች ከመጪው በጀት ዓመት ጀምሮ ቅናሽ የጉምሩክ የቀረጥ ምጣኔ እንዲከፍሉ ይደረጋል ተብሏል፡፡ በዚህም 22.5 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን የገንዘብ ሚኒስቴር ለፓርላማው ያቀረበው ረቂቅ በጀት ያሳያል፡፡ በተጨማሪም የገቢ ግብር እፎይታ አሰራርን ቀሪ በማድረግ የግብር እፎታ ይሰጣቸው የነበሩ በቅናሽ ምጣኔ ግብር በማስከፈል ሌላ 22 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር እንደሚሰበሰብ በረቂቁ ሰፍሯል፡፡ ከዚህ ቀደም የሴቶችን ስራ ለማቃለል በሚል የልብስና የእቃ ማጠቢያ ማሽኖች ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ ከተፈቀዱ መካከል ነበሩ፡፡ በተጨማሪም የጤናና የግብር ዘር
Jun 121 min read


‘’መንግስት ከታክስ ገቢ ወደ 1.5 ትሪሊዮን ብር ለመሰብሰብ ማቀዱ በዜጎች ላይ ጫና ይፈጥራል’’
ሰኔ 4/2018 መንግስት ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በሚጀምረው በጀት ዓመት፤ ከታክስ ገቢ ወደ 1.5 ትሪሊዮን ብር ለመሰብሰብ ማቀዱ በዜጎች ላይ ጫና ይፈጥራል የሚል ትችት ከፓርላማ አባል ቀረበበት፡፡ ዛሬ ለፓርላማ የቀረበው የፌዴራል መንግስት የ2019 በጀት ረቂቅ 2 ነጥብ 3 ትሪሊዮን ሲሆን ከዚህ ውስጥ 1.5 ትሪሊዮን ብሩን መንግስት ከታክስ ለመሰብሰብ ማቀዱን ተናግሯል፡፡ ይህም መንግስት ባለፈው ዓመት ከታክስ ለመሰብሰብ አቅዶት የነበረውን በጀት በግማሽ ትሪሊዮን ብር ይበልጣል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት መንግስት ከታክስ ገቢ ለማግኘት አቅዶት የነበረው የገንዘብ መጠን 1 ትሪሊዮን ነበር፡፡ በበጀት ረቂቁ ላይ ሀሳባቸውን የሰጡት የፓርላማ አባሉ እና የኢዜማ ተወካይ አብርሃም በርታ (ዶ/ር) ከግብር ለመሰብሰብ የታቀደው የገንዘብ መጠን ከፍተኛ መሆኑን ተ
Jun 111 min read


ከተረፈ ምርቶች፣ አገልግሎቶቻቸውን ከጨረሱ ባትሪዎች አካባቢን የማይጎዱ ምርቶችን የሚሰሩትን ወጣቶች
ሰኔ 3 2018 ከተረፈ ምርቶች፣ አገልግሎቶቻቸውን ከጨረሱ ባትሪዎች አካባቢን የማይጎዱ ምርቶችን የሚሰሩትን ወጣቶችንና እነሱን የሚረዱ ተቋማት እንዲደገፉ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጠየቀ፡፡ ከተረፈ ምርቶች የንፅህና መጠበቂያ፣ ከሰል የመሳሰሉ ምርቶች የሰሩ ወጣቶችም፤ ቆሻሻ ሀብት እየፈጠረላቸው እንደሆነ ነግረውናል፡፡ ወጣቶቹ ወደ ስራ ሲገቡ አስፈላጊውን የሞያና የገንዘብ ድጋፍ እንደተደረገላቸው ተናግረዋል፡፡ ገንዘብና ሞያዊ ድጋፍ ካደረጉት መካከል ሪችፎር ቼንጅ አንዱ ነው፡፡ ድርጅቱ በሃሳብ ደረጃ የነበሩ 33 ድርጅቶች ንግድ መጀመር እንዲችሉ የሞያ ስልጠና እና ለእያንዳንዳቸው የ200 ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ተናግሯል፡፡ ወደ ሥራ ገብተው እራሳቸውን በሀሳብ እና በፋይናንስ በማሳደግ ላይ ለሚገኙ 8 ድርጅቶች ደግሞ 1.5 ሚሊዮን ብር
Jun 111 min read


የፌዴራል መንግስት ለክልሎች የደለደለው የበጀት
ሰኔ 4/2018 የፌዴራል መንግስት ለክልሎች ከደለደለው የበጀት ድጋፍ ትንሹ ለአዲስ አበባ የተመደበው 74.5 ሚሊዮን ብር ነው፡፡ ከፍተኛው ደግሞ ለኦሮሚያ ክልል 179.3 ቢሊዮን ብር ሆኖ መደልደሉን ከረቂቅ በጀቱ ተመልክተናል፡፡ ለመጪው የ2019 በጀት ዓመት የገንዘብ ሚኒስቴር ለፓርላማው ካቀረበው ረቂቅ በጀት እንደተመለከትነው ለ12 ክልሎች እና ለሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የተመደበው አጠቃላይ የበጀት ድጋፍ 520.5 ቢሊዮን ብር ነው፡፡ ከመካከሉ ሁለተኛው ትልቁ ድጋፍ ለአማራ ክልል የተያዘው 112.4 ቢሊዮን ብር ነው፡፡ ሶማሌ ክልል በሶስተኛ ደረጃ 51.9 ቢሊዮን ብር ለ2019 ዓ.ም በጀት ተደልድሎበታል፡፡ ለደቡብ ኢትዮጵያ 36.5 ቢሊዮን ፣ ለትግራይ 31.3 ቢሊዮን፣ ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ 30.9 ቢሊዮን ፣ ለሲዳማ ክልል ደግሞ 20.9 ቢሊዮን ብር ተ
Jun 111 min read


ኢትዮጵያ ለመጪው በጀት ዓመት ከያዘችው አጠቃላይ በጀት ከ542 ቢሊዮን ብር በላዩን ያለባትን የብድር እዳ ለመክፈል የተደለደለ ነው፡፡
ሰኔ 4/2018 ኢትዮጵያ ለመጪው በጀት ዓመት ከያዘችው አጠቃላይ በጀት ከ542 ቢሊዮን ብር በላዩን ያለባትን የብድር እዳ ለመክፈል የተደለደለ ነው፡፡ ይህም ለክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች መደገፊያ ከያዘው በጀት ከ21 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ ያለው ነው፡፡ መንግስት አጠቃላይ በዓመቱ ለተለያዩ ክፍያዎች ከመደበው ደግሞ የ59.9 በመቶው ድርሻ የያዘ ነው፡፡ በበጀት ዓመቱ እዳ ለመክፈል የተጠየቀው 581.1 ቢሊዮን ብር ሲሆን የተያዘው በጀት ደግሞ 542.1 ቢሊዮን ብር መሆኑን ረቂቅ በጀቱ ያሳያል፡፡ ይህም እዳ ለመክፈል ከሚያስፈልገው ገንዘብ የ78.8 ቢሊዮን ብር ልዩነት መኖሩን ያሳያል፡፡ በሌላ በኩል ለ2019 በጀት ዓመት 124.4 ቢሊዮን ብር ለመጠባበቂያ እና ለሌሎች ክፍያዎች በሚል 904.6 ቢሊዮን ብር በጀት ተይዟል፡፡ ለሌሎች ክፍያዎች ተብሎ ከተ
Jun 111 min read


የድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ድርጅት፣ በሳምንት ሁለቴ የሚሰጠውን የትራንስፖርት አገልግሎት ወደ ሶስት ማሳደጉን ተናገረ።
ሰኔ 3/2018 የድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ድርጅት፣ በሳምንት ሁለቴ የሚሰጠውን የትራንስፖርት አገልግሎት ወደ ሶስት ማሳደጉን ተናገረ። ድርጅቱ በድንገተኛ ጎርፍ ምክንያት በሀዲዱ ላይ በደረሰ ጉዳት ለሁለት ሳምንት ያህል ስራ አቁሞ እንደነበርና ጥገና በማድረግ ወደ ስራ መመለሱም ተነግሯል። ከድሬዳዋ እስከ ደወሌ የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጠው ድርጅቱ፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከሰራው ስራ ከ33 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱ ተነግሯል። ድርጅቱ 20ኛ የቦርድ መደበኛ ጉባኤውን ከትናንት በስቲያ ማክሰኞ ያደረገ ሲሆን የዘጠኝ ወራት የስራ ክንውኑን ገምግሟል። በሚኒሊክ ዘመነ መንግስት የተቋቋመው ከጅቡቲ እስከ አዲስ አበባ የሚደርሰውና 781 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የባቡር መስመር፣ ከ5 ዓመት በፊት በሚኒስትሮች ምክር ቤት በተወሰነው መሰረት ሀብትና ንብረ
Jun 111 min read


መንግስት ሐምሌ 1/2018 ዓ.ም በሚጀምረው በጀት ዓመት፤ ከታክስ ገቢ ወደ 1.5 ትሪሊዮን ብር ለመሰብሰብ ማቀዱ ታወቀ፡፡
ሰኔ 4/2018 መንግስት ሐምሌ 1/2018 ዓ.ም በሚጀምረው በጀት ዓመት፤ ከታክስ ገቢ ወደ 1.5 ትሪሊዮን ብር ለመሰብሰብ ማቀዱ ታወቀ፡፡ በበጀት ዓመቱ መንግስት ለጠቅላላ ገቢ የውጪ ብድርን ጨምሮ ከ2 ትሪሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ እንዳቀደ ዛሬ ወደ ቋሚ ኮሚቴ ይመራል ተብሎ የሚጠበቀው የፌደራል መንግስት የ2019 የገቢ በጀት ረቂቅ ሰነድ ያሳያል፡፡ በ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት ጠቅላላ ገቢ የውጪ ዕርዳታን ጨምሮ 1.8 ትሪሊዮን ብር እንደሚሆን ተገምቷል የሚለው ሰነዱ ይህም በ2018 በጀት ዓመት ይሰበሰባል ተብሎ ከተገመተው ጠቅላላ ገቢ አንጻር የ17.4 በመቶ እድገት ያለው እንደሆነ ዘርዝሯል፡፡ ከዚህ ውስጥ 1.5 ትሪሊዮን ብር ወይም 82 በመቶው ከታክስ ገቢ እንደሚሆን አስረድቷል፡፡ በዚህም መሰረት፡- ጠቅላላ ገቢና ዕርዳታ 1,816,5
Jun 112 min read


በኢትዮጵያ ትምህርት የቻይንኛ ቋንቋን ለማስተማር የሚያስችል የሁለትዮሽ የትብብር ስምምነት መፈረሙ ትምህርት ሚኒስቴር ተናገረ።
ሰኔ 4/2018 በኢትዮጵያ ትምህርት የቻይንኛ ቋንቋን ለማስተማር የሚያስችል የሁለትዮሽ የትብብር ስምምነት መፈረሙ ትምህርት ሚኒስቴር ተናገረ። ስምምነቱን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ክንደያ ገብረሕይወት(ፕ/ር) እና በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቺን ሃይ በጋራ ፈርመውታል ተብሏል። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ታሪካዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር እና በተለይም በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በባህል ልውውጥ ዙሪያ አዳዲስ ምዕራፎችን የሚከፍት ነው ብሏል ትምህርት ሚኒስቴር። በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ክንደያ ገብረሕይወት(ፕ/ር) ፣ ስምምነቱ ከዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ባለፈ በቱሪዝም፣ በህዝብ ለህዝብ ትስስር እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ሲሉ አስረድተዋል። "ዜጎቻችን የተለ
Jun 111 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

