top of page


‘’በአርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ ጃዊ ቀበሌና በሮቤ ወረዳ ገባ ቀበሌ በተፈጸመ ጥቃት ቁጥራቸው በውል ያልተለዩ ሰዎች መገደላቸውን አረጋግጫለሁ ’’
የካቲት 25/2018 በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን የካቲት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በዞኑ ሽርካ ወረዳ ጃዊ ቀበሌ እና በሮቤ ወረዳ ገባ ቀበሌ በተፈጸመ ጥቃት ቁጥራቸው በውል ያልተለዩ ሰዎች መገደላቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አረጋግጫለሁ አለ፡፡ የሕይወታቸው ካለፈው በተጨማሪ፣ አካል ጉዳት፣ እገታ እንዲሁም መፈናቀል የደረሰባቸው ሰዎች አንዳሉ በተለያዩ መንገዶች ባሰባሰብኳቸው መረጃዎች አረጋግጫለሁ ብሏል። ጥቅቱንም የፈጸመው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (በተለምዶ “ኦነግ ሸኔ”) መሆኑን ኮሚሽኑ ባወጣው መገልጫ አስረድቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በአርሲ በተለያዩ ወረዳዎች በአዲስ መልክ በቀጠለው ጥቃት የ21 ንጹሐን ህይወት ማለፉን መናገሩ ይታወሳል፡፡ የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ
Mar 42 min read


እስራኤል በመላዋ ኢራን በአገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤት ቢሮዎች እና ፅህፈት ቤቶች በላይ ያነጣጠረ ታላቅ ድብደባ ፈፀምኩ አለች፡፡
የካቲት 25/2018 እስራኤል በመላዋ ኢራን በአገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤት ቢሮዎች እና ፅህፈት ቤቶች በላይ ያነጣጠረ ታላቅ ድብደባ ፈፀምኩ አለች፡፡ በሊባኖስ ድብደባ እየፈፀመች መሆኑን ቢቢሲ ፅፏል፡፡ የርዕሰ ከተማዋ ቤይሩት ደቡባዊ ክፍል ነዋሪዎችም አካባቢውን ለቅቀው እንዲወጡ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች ተብሏል፡፡ እስራኤል እና አሜሪካ በጣምራ በኢራን ላይ ድብደባ መፈፀም ከጀመሩ ወዲህ የሊባኖሱ ታጣቂ ቡድን ሔዝቦላህ ወሰን አሻግሮ ወደ እስራኤል ሮኬቶችን እየተኮሰ መሆኑ ይነገራል፡፡ የሊባኖሷ ርዕሰ ከተማ ቤይሩት ደቡባዊ ክፍል የሄዝቦላህ መሪዎች መናኽሪያ ነው ይባላል፡፡ ሔዝቦላህ የኢራን የጦር እና የፖለቲካ አጋር እንደሆነች መረጃው አስታውሷል፡፡ በሌላ መረጃ ሲሪላንካ አቅራቢያ የኢራን የጦር መርከብ መስመጡ ተሰምቷል፡፡ በኔፓን የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች የ
Mar 41 min read


በበጀት ዓመቱ በመንፈቅ ዓመት በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘ 8,183 ሊትር ነዳጅ መወረሱን የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ተናገረ፡፡
የካቲት 25/2018 በበጀት ዓመቱ በመንፈቅ ዓመት በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘ 8,183 ሊትር ነዳጅ መወረሱን የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ተናገረ፡፡ ህገወጥ የነዳጅ ዝውውሩ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ሲፈፀም የተገኘ ነው፡፡ ቢሮው በውሃ ኮዳ እና በሌሎች ያልተፈቀዱ እቃዎች ሲጓጓዙ ተገኝተዋል ካለው 8,183 ሊትር ነዳጅ ውስጥ ናፍጣ 5,900 ሊትር ከ2,000 ሊትር በላይ ቤንዚን እና ነጭ ጋዝን እንደሆነ ተሰምቷል፡፡ በከተማዋ ባሉት ሁሉም ማዲያዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ ነው ያለው ቢሮው በህገ-ወጥ ንግድ ላይ የተሰማሩትን ፣ ነዳጅ እያላቸው የለንም የሚሉትን እርምጃ እየወሰድንባቸው ነው ብሏል ቢሮው፡፡ በዚህም ባለፉት 6 ወራት ነዳጅ እያላቸው ጨርሰናል በማለት አገልግሎት ያቆሙ ሶስት ማደያዎችን ክስ ተመስርቶባቸው እንዲታሸጉ ተደርጎ እንደገና የ
Mar 41 min read


ከማረሚያ ቤት በሮቶ የሚወጣ ቆሻሻ አስመስለው የህግ ታራሚዎችን ያስመለጡ የማረሚያ ፖሊስ አባላት መቀጣታቸው ተነገረ፡፡
የካቲት 25/2018 ከማረሚያ ቤት በሮቶ የሚወጣ ቆሻሻ አስመስለው የህግ ታራሚዎችን ያስመለጡ የማረሚያ ፖሊስ አባላት መቀጣታቸው ተነገረ፡፡ ይህንን የሰማነው ከፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ነው፡፡ ድርጊቱ ግን ግላዊ ጥቅማቸውን በማስቀደም ከህግ ታራሚዎች ጋር ቀድመው ተመሳጥረው ለማስጠፋት ዘዴ በዘየዱ የማረሚያ ፖሊስ አባላት ተፈፅሟል ሲልም ኮሚሽኑ አክሏል፡፡ በእርምት ላይ ይገኙ የነበሩት 1ኛ የህግ ታራሚ ቢኒያም ካህሳይ ገብሩ እና 2ኛ የህግ ታራሚ ዳንኤል ጎይቶም ተስፋዬ እየታረሙ ከሚገኙበት የከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማዕከል ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ከሚኖሩበት ዞን ውጥተው በመጥፋታቸው ባደረግሁት ክትትል እና ማጣራት ነው ያስመለጧቸው አጃቢ የፖሊስ አባላት እንደሆኑ ደርሼበታለሁ ብሏል ኮሚሽኑ፡፡ ሁለቱ የህግ ታራሚዎች ለመጥፋት ይመቸናል ያሉትን ሃሳብና
Mar 41 min read


በኢትዮጵያ የዛሬ 51 ዓመት በዛሬው ቀን የገጠር መሬት አዋጅ ታወጀ፡፡
#ታሪክን_የኋሊት በኢትዮጵያ የዛሬ 51 ዓመት በዛሬው ቀን የገጠር መሬት አዋጅ ታወጀ፡፡ የካቲት 25 ቀን 1967 የወጣው የመሬት አዋጅ ከዚያ በፊት ሰፍኖ የቆየውን የመሬት አጠቃቀምና ስሪት ለውጦ ከባለርስቱ ወደ አራሹ ገበሬ ያዛወረ አዋጅ ነበር፡፡ የመሬትን ባለቤትነት ላራሹ የማድረግ አስፈላጊነት ጥያቄ በጊዜው ለነበረው ንጉሳዊ መንግስት ከተለያዩ ክፍሎች ሲቀርብ ቆይቷል፡፡ ገበሬዎች በሰላማዊና በአመፅ ጥያቄያቸውን አቅርበዋል፡፡ የጊዜው የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችም በተደራጀ መልኩ በአመፅ ጥያቄውን ሲያነሱ ቆይተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ያለው የመሬት ስሪት ፣ በርስትነት በገባርነት የሚያዝ ሆኖ ቆይቷል፡፡ መሬት በአብዛኛው ትውልድ ቆጥሮ ወይም በውርስ የሚይዙት ፣ ሲሆንም ነባሩን ነዋሪ አፈናቅሎ በአገልግሎትና በስጦታ የሚሰጥ ይዞታ ነበረው፡፡ በአገልግሎትና በስጦታ በሰ
Mar 42 min read


የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን የአየር እና የባህር ሀይሎች እንዳልነበሩ አድርገን አውድመናቸዋል አሉ፡፡
የካቲት 25/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #አሜሪካ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን የአየር እና የባህር ሀይሎች እንዳልነበሩ አድርገን አውድመናቸዋል አሉ፡፡ ትራምፕ የኢራንን የአየር እና የባህር ሀይሎች እንዳልነበሩ አድርገን ደምስሰናቸዋል ያሉት በዋይት ሐውስ ከጀርመኑ መራሄ መንግስት ፍሬድሪክ ሜርዝ ጋር ከተመካከሩ በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሆነ አልጀዚራ ፅፏል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኢራን የባህር እና የአየር ሀይል እንዳይኖራት ማድረጋቸው ትራምፕ ተናግረዋል፡፡ አሜሪካ እና እስራኤል ካለፈው ሳምንት ቅዳሜ አንስቶ በጣምራ በኢራን ላይ ከባድ ድብደባ እየፈፀሙ ነው፡፡ ቢቢሲ እንደፃፈው ትራምፕ የኢራንን የጦር አቅም አነካክቼዋለሁ ቢሉም ፋርሳዊቱ አገር በእስራኤል እና በቀጠናው በሚገኙ የአሜሪካ ተቋሞች ላይ የአፀፋ ጥ
Mar 42 min read


የኤ ኤፍ ጂ ኤርክራፍት ፋይናንስ ጀርመን (AFG) እህት ኩባንያ የሆነው ኤ ኤፍ ጂ አቪየሺን አየርላንድ ኩባንያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው አፍሪካ ሀገራት መግባቱን ተናገረ።
የካቲት 24/2018 በአውሮፕላን ንግድና ሀብት አስተዳደር የሚታወቀው ኤ ኤፍ ጂ ኤርክራፍት ፋይናንስ ጀርመን (AFG) እህት ኩባንያ የሆነው ኤ ኤፍ ጂ አቪየሺን አየርላንድ ኩባንያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው አፍሪካ ሀገራት መግባቱን ተናገረ። ኩባንያው ለአፍሪካ ስራው ሲልም ሁለት ከፍተኛ ባለሞያዎቹን በአፍሪካ ተገኝተው እንዲሰሩ እንደመደባቸው ባወጣው መግለጫ ተናግሯል። AFG አቪዬሽን አየርላንድ የናይጄሪያው ካሊ ኤር ሁለት CRJ1000 አውሮፕላኖች ባለቤት እንዲሆን ማስቻሉን ተናግሯል። በዚህም የተነሳ የአፍሪካ ሀገራት አየር መንገዶች፣ አፕሬተሮች፣ የመንግሥት እና የአቪዬሽን ዘርፍ ሀላፊዎች ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለቸው ተረድቻለሁ ብሏል። ይህ ፍላጎት የአፍሪካ የአቪዬሽን ዘርፍ በአለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እየተቀየረ መምጣቱን ያሳል ሲልም ኩ
Mar 42 min read


በሚቀጥሉት 10 ቀናት በአብዛኛው የኢትዮጵያ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር የሚቴዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ተናገረ
የካቲት 24/2018 በሚቀጥሉት 10 ቀናት አዲስ አበባን ጨምሮ በአብዛኛው የኢትዮጵያ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር የኢትዮጵያ ሚቴዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ተናገረ፡፡ አሁን ያለንበት የየካቲት ወርን ጨምሮ እስከ ግንቦት ድረስ በሚዘልቀው የበልግ ወቅት ሰሞኑን እተስተዋለ ያለው የአየር ሁኔታ ለውጥ የሚጠበቅ ነው ብሏል ኢንስቲትዩቱ፡፡ በዚህ ወቀት የደቡብ አጋማሽ የሃገሪቱ ክፍል ማለትም ሶማሌ ክልል ደቡባዊ ክፍል፣የጉጂና ቦረና ዞኖች፣የሲዳማ ክልል ዞኖች፣የደቡብና ደቡብ ምዕራብ ክፍሎች እስከ 55 በመቶ የሚሆነውን የዝናብ መጠን የሚያገኙበት ዋንኛ የዝናብ ወቅታቸው ነው፡፡ በተጨማሪም የደቡብና ምስራቅ ትግራይ ዞኖች፣የምስራቅ አማራ ዞኖች፣የምስራቅ የሃገሪቱ አካባቢዎች፣አዲስ አበባና የመካከለኛው ኢትዮጵያ ክፍሎች ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው
Mar 31 min read


የአንድ ሀገር መረጃ በሌሎች ሀገሮች እጅ ቢገባ ምን ሊያስከትል ይችላል?
የካቲት 24/2018 በአሁኑ ጊዜ መረጃ ብዙ ነገሮችን የመበየን አቅም እንዳለው ይነገራል፡፡ ሀገራት ከሃገራት ጋር በሚያደርጉት አብሮ ለመስራት የጋራ ስምምነቶች ቀድሞ ከሚነሱ ጉዳዮች መካከል የዲጂታሉ ዘርፍ ይገኝበታል፡፡ ለመሆኑ የአንድ ሀገር የጤና፣ የማዕድን የሌላ ሌላውም ዘርፍ መረጃ በሌሎች ሀገሮች እጅ ቢገባ ምን ሊያስከትል ይችላል? ስንታየሁ ሂርጳሳ(ዶ/ር ) በአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የዳታ ምህንድስና ምርምር መምህር ናቸው፡፡ የአንድ ሀገር መረጃ በሌሎች ሃገራት እጅ ላይ ቢገባ ስለሚያስከትለው ጉዳት ነግረውናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… ማርታ በቀለ
Mar 31 min read


እስራኤል በኢራን ላይ ድንገተኛ የሚሳኤል ጥቃት መፈፀሟ ተነገረ፡፡
የካቲት 21/2018 እስራኤል በኢራን ላይ ድንገተኛ የሚሳኤል ጥቃት መፈፀሟ ተነገረ፡፡ አልጀዚራን ጨምሮ የተለያዩ አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጥቃቱን የተመለከተ መረጃን በሰበር ወሬ ይዘው ቀርበዋል፡፡ እስራኤል በፈፀመችው የሚሳኤል ጥቃት በቴህራን ማዕከላዊ ከተማ የፍንዳታ ድምፅ መሰማቱ ተሰምቷል፡፡ ፋርስ የወሬ ምንጭ እንደዘገበው በማዕከላዊ ቴህራን ዩኒቨርስቲ ጎዳና እና ጃዋሆሪ በተባሉት ማዕከላዊ የቴህራን ክፍል ተደጋጋሚ የሚሳኤል ጥቃት ተሰንዝሯል፡፡ የእስራኤሉ የመከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እርምጃው እራስን ከጥቃት የመጠበቅና ቀርቦ የመከላከል ነው ብለውታል፡፡ አሶሼትድ ፕሬስ የመረጃ ምንጭ ደግሞ የእስራኤል ጥቃት የተፈፀመው በኢራን ዋና ከተማ በከፍተኛ መንፈሳዊው መሪው አያቶ አሊ ካሚኒ ቢሮ አካባቢ ነው ብሏል፡፡ ዝርዝር መረጃ
Feb 281 min read


''ደንብ አስከባሪ ባለሞያዎች በሞያ ስነ ምግባር ታንፀው እንዲሰሩ እያደረግሁ ነው'' የደንብ ማስከበር ባለስልጣን
የካቲት 20/2018 ደንብ አስከባሪዎች ህግን በተከተለ መልኩ እና ሞያዊ ስነ ምግባርን ጠብቀው የተሰጣቸውን ሀላፊነት እንዲወጡ እያደረግሁ ነው ሲል የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ በማስከበር ባለስልጣን ተናገረ። ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከዚህ ቀደም አልፎ አልፎ በደንብ አስከባሪዎች የሚፈጸሙ የሥነ ምግባር ጥሰቶች አሁን እየቀነሱ ነው ብሏል። ከዚህ ቀደም ህግን ለማስከበር አልፎ አልፎ በደንብ አስከባሪዎች በኩል ይስተዋሉ የነበሩ የስነ ምግባር ግድፈቶች እንዳይኖሩ እየሰራ መሆኑንም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ተናግሯል። ደንብ አስከባሪዎች ህግን በተከተለ መልኩ እና ሙያዊ ስነ-ምግባርን ጠብቀው የተሰጣቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ፣ ማህበረሰቡን ስነ-ምግባር በተሞላበት መልኩ እንዲያገለግሉ ለማስቻል የስነ ምግባር ስልጠና እንዲወስዱ እየተደረገ መሆኑን ሰምተናል። ከዚህ ቀደም
Feb 271 min read


ኢትዮጵያ የምታካሄደውን ሀገራዊ ምክክር በተመለከተ መገናኛ ብዙሀን በኃላፊነት ሊሰሩ ይገባል ተባለ፡፡
የካቲት 20 2018 ኢትዮጵያ የምታካሄደውን ሀገራዊ ምክክር በተመለከተ መገናኛ ብዙሀን በኃላፊነት ሊሰሩ ይገባል ተባለ፡፡ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ በሚከውናቸው ስራዎች አካታችነቱን የጠበቀ እንዲሆንና ሃገራዊ ምክክሩ የታለመለትን ዓላማ እንዲያሳካ መገናኛ ብዙሃን ብዙ ሃላፊነት አለባቸው ተብሏል፡፡ ይህ የተባለው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከመገናኛ ብዙሃን ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር ትናንት በአዳማ ከተማ ባደረገው ውይይት ነው፡፡ መገናኛ ብዙሃን በተለይ የሀገራዊ ምክሩን ሂደት በተመለከተ የሚከውኗቸው ስራዎች በደንብ የተጠኑ በኋላም ሊያመጡት የሚችለው ጥሩም ይሁን አሉታዊ ተጽዕኖ ተመዝኖ ሙያዊ ኃላፊነት በተሞላበት መንገድ መሆን አለበት ሲሉ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር ሙሃመድ ድሪር ተናግረዋል፡፡ ሚዲያ በሀገር ግንባታ ላይ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ
Feb 271 min read


የአስር እና አምስት ብር ኖቶችን ልክ እንደ ሳንቲሞች ሁሉ የዋጋ ንረት እየበላቸው፣ ከገበያም እየወጡ ይሆን?
የካቲት 19/2018 የአስር እና አምስት ብር ኖቶችን ልክ እንደ ሳንቲሞች ሁሉ የዋጋ ንረት እየበላቸው፣ ከገበያም እየወጡ ይሆን? የገንዘቦች መነሻ የሆነው ሳንቲም በኢትዮጵያ ገበያ ውስጥ አቅም አጥቶ ተዳክሞ ከወጣ አመታት ተቆጥሯል፡፡ አንድ ብርም የሚገዛው ነገር የለም፤ የአስር እና አምስት ብር የመግዛት አቅምም በእጅጉ አሽቆልቁሏል፡፡ አሁን በአገሪቱ ገበያ ውስጥ ያለው የሚዘዋወረው የአስር እና አምስት ብር ኖትም ያረጀ፣ የተቀዳደደ፣ በማያያዣ የተለጣጠፈ እና በምልልስ የሳሳ መሆኑ ይታያል። የምጣኔ ሀብት እና የፋይናስ ባለሙያዎች የዋጋ ግሽበቱ ሁለቱን ገንዘቦች እየበላቸው እና ከገበያ እያወጣቸው እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ የሁለቱ የገንዘብ ኖቶች አዲስ ህትመትም በገበያ ውስጥ እየታየ አይደለም ፤ይህስ ለምን ሊሆን ቻለ ? የአስር እና አምስት ብር የገንዘብ ኖቶ
Feb 262 min read


በኢራን ወታደራዊ እርምጃ ስለመውሰድ በአሜሪካ በኩል እየተነሳ ያለውን ሀሳብ ኢራን የምር አድርጋ ብትወስደው ይበጃታል ተባለ፡፡
የካቲት 19/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #ኢራን በኢራን ወታደራዊ እርምጃ ስለመውሰድ በአሜሪካ በኩል እየተነሳ ያለውን ሀሳብ ኢራን የምር አድርጋ ብትወስደው ይበጃታል ተባለ፡፡ ይህንን ያሉት የአሜሪካው ምክትል ፕሬዘዳንት ጄዲ ቫንስ ናቸው፡፡ ሁለቱ ሀገሮች በኢራን የኒውክሊየር ፕሮግራም ዙሪያ ለሶስተኛ ዙር ንግግር ጄኔቫ የገቡ ሲሆን ምክትል ፕሬዘዳንቱ ግን ኢራን አሁንም ለሰላማዊው መንገድ ዝግጁ አትመስልም እያሉ ነው፡፡ የኒውክሊየር ፕሮግራሟንም እንዳላቆመች መረጃ አለን ያሉት ምክትል ፕሬዘዳንቱ ያ ለአሜሪካ ትልቅ ችግር ነው ብለዋል፡፡ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ደግሞ የዛሬው የጀኔቫ ስብሰባ በኢራን የኒውክሊየር እና የባለስቲክ ሚሳየል ፕሮግራሟ ዙሪያ ድርድር የሚደረግበት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በኢራን በኩል
Feb 262 min read


በንግድ ስራ መሰማራት ለሚፈልጉ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎች እንዲኖሩ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተናገረ።
የካቲት 19/2018 በንግድ ስራ መሰማራት ለሚፈልጉ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎች እንዲኖሩ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተናገረ። በህጋዊ መንገድ በስራው ለመሳተፍ የሚገጥሙ ችግሮች ሰዎችን ወደ ህገ ወጥ መንገድ እየገፉ ነው ተብሏል። በኢትዮጵያ ህጋዊ ያልሆነ ንግድ ከመቀነስ ይልቅ እየተባባሰ መምጣቱን ከሠሞኑ የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ባዘጋጀው አንድ ውይይት ላይ ሲነገር ሠምተናል። ለዚህ እንደ ማሳያ የሚጠቀሰው በኮንትሮባንድ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባ መድሃኒት ነው። መድሃኒት አምስት በመቶ እንኳን የማይሞላ በጣም አነስተኛ ቀረጥ እና ታክስ ተከፍሎባቸው ወደ ሀገር ውስጥ ከሚገቡ ምርቶች አንዱ እንደሆነ ፤ የኢትዮጵያ ጉሙሩክ ኮሚሽን የህግ ተገዥነት ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር አቶ እዘዘው ጫኔ
Feb 262 min read


የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር በጎርፍ መከላከል ፕሮጀክት አዋሽ፣ የሪፍት ቫሊ ስምጥ ሸለቆና የኦሞ ጊቤ ተፋሰስ ላይ የጎርፍ መከላከል ሥራዎች 170 ሺህ ነዋሪዎችን ከመፈናቀል አድኛለሁ አለ።
የካቲት 19/2018 የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር በጎርፍ መከላከል ፕሮጀክት በተደጋጋሚ ጎርፍ ሲያጠቃቸው በነበሩ አዋሽ፣ የሪፍት ቫሊ ስምጥ ሸለቆና የኦሞ ጊቤ ተፋሰስ ላይ ባለፉት አመታት በሰራኋቸው የጎርፍ መከላከል ሥራዎች 170 ሺህ ነዋሪዎችን ከመፈናቀል አድኛለሁ አለ። ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ በዚህ ሥራ 30 ሺህ ሄክታር የእርሻ መሬትን ከጎርፍ መከላከል ችያለሁ ብሏል። ይህ የተባለው የውሃና ኢነርጂ ሚንስትር ኤስ ደብሊው ኤስ (SWS) ከተባለ የጎርፍ መከላከል አማካሪ ድርጅት ጋር በመሆን የሰሩትን የኦሞ ጊቤ የተፋሰስ ልማት የተግባራዊነት የጥናት ግኝት ሪፖርት ላይ እየመከሩበት ባለ መድረክ ላይ ነው። በመድረኩ የውሃ እና ኢነርጂ ሚንስትሩ ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ ጥናቱ በተሰራባቸው ተፋሰሶች ተደጋጋሚ የጎርፍ አደጋ እየተከሰተ ሰዎችን ከመኖሪያ ቦታቸው ከማ
Feb 261 min read


የቤት ሰራተኞችን በተመለከተ ግልፅ የሆነ ህግ ባለመበጀቱ የሚደርስባቸዉን ጥቃት ለመከላከልና መብታቸዉን ለማስከበር አስቸጋሪ እንዳደረገዉም አንድ ጥናት አመላከተ።
የካቲት 19/2018 የቤት ሰራተኞችን በተመለከተ ግልፅ የሆነ ህግ ባለመበጀቱ የሚደርስባቸዉን ጥቃት ለመከላከልና መብታቸዉን ለማስከበር አስቸጋሪ እንዳደረገዉም አንድ ጥናት አመላከተ። ዕድሜያቸው ከ10 ዓመት በታችየሆኑ ህፃናት በቤት ሰራተኝነትተሰማርተው እንደሚገኙ በጥናቱ ተጠቁሟል። አባዛኛዉን “ከገጠሪቱየሀገራችን ክፍሎችየተሻለ ህይወትን ፍለጋ ወደከተማ በመሰደድ በሰውቤት ተቀጥረው የቤቱን ስራ የሚከዉኑ፣ ልጆችን የሚሳድጉ፣ማዕድ የሚያዘጋጁ የቤት ሴት ሰራተኞች የተለያየጥቃት እንደሚደርስባቸዉም በጥናቱ ተጠቁሟል። ፎረም ፎርሶሻል ስተዲስ (FSS)የተባለው መንግስታዊ ልሆነ የጥናትተቋም ከ2015 እስከ 2016 ዓ.ም አካሄደኩት ባለዉና ሰሞኑን ይፋ ባደረገዉ ጥናት፣ በሴት የቤትሰራተኞች ላይ ስነ ልቦናዊ እና ቃላዊ ጥቃት እንደሚደርስባቸዉ በ
Feb 261 min read


አቢሲንያ ባንክ ‹‹ይጀምሩ፣ ያድሱ እና ይደጉ›› በሚል መሪ ቃል ለሁለት ወራት ያህል ባካሄደው ፕሮግራም ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ ተቀማጭ ገንዘብ መሰብሰብ መቻሉን ተናገረ።
የካቲት 19/2018 አቢሲንያ ባንክ ‹‹ይጀምሩ፣ ያድሱ እና ይደጉ›› በሚል መሪ ቃል ለሁለት ወራት ያህል ባካሄደው ፕሮግራም ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ ተቀማጭ ገንዘብ መሰብሰብ መቻሉን ተናገረ። ከዚህ በተጨማሪም 140 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ ማግኘቱን አስረድቷል። ባንኩ ፕሮግራሙን ሲያካሂድ የነበረው አዳዲስ ደንበኞችን ለመመልመል፣ ነባር ደንበኞችን ከባንኩ ጋር ያላቸውን ደንበኝነት ለማደስ እንዲሁም ተቀማጭና የውጭ ምንዛሬ ግኝቶችን ለማሳደግ አስቦ እንደነበር ተጠቅሷል። ይህ ፕሮግራም ከህዳር 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ጥር 29 / 2018 ዓ.ም. ድረስ ሲካሄድ ቆይቷል ተብሏል። አቢሲኒያ ባንክ በዚህ መርሃግብር ደንበኞቹ ለማበረታታት ሽልማት አዘጋጅቷል። በዚህ መርሀ ግብር ለሽልማቱ ተሳታፊ የሆኑት ከብር 1000 ሺሕ ብር ጀምሮ ተ
Feb 261 min read


ኢትዮጵያ በ2030 የሚደረገውን የዓለም ቱሪስት አስጎብኚ ባለሞያዎች ማህበራት ፌዴሬሽን ጉባኤ የማስተናገድ ፍላጎት አላት ተባለ።
የካቲት 18/2018 ኢትዮጵያ በ2030 የሚደረገውን የዓለም ቱሪስት አስጎብኚ ባለሞያዎች ማህበራት ፌዴሬሽን ጉባኤ የማስተናገድ ፍላጎት አላት ተባለ። ጉባኤውን ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት የሚያስችል ስራ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ቱሪስት አስጎብኚ ባለሙያዎች ማህበር ተናግሯል። ፌዴሬሽኑ በቅርቡ በተደረገው የጃፓኑ ጉባኤ ላይ ከ2 ዓመት በኋላ የሚደረገውን ጉባኤ ለማዘጋጀት ጠይቆ በመጨረሻው ዙር ፔይሩ መመረጧን ተናግሯል። ማህበሩ ይህንን ጥረት እያደረኩ ያለሁት ብቻዬን ነው ከመንግስት በኩል ድጋፍ ያስፈልገኛል ሲልም ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስረድቷል። ማህበሩ የዓለም አቀፍ የቱሪስት አስጎብኚ ባለሙያዎች ማህበራት ፌዴሬሽን አባል መሆኑ ባለሙያዎች የተሻለ ስልጠና እንዲያገኙ ይረዳል፤ ኢትዮጵያም ከአለም አቀፍ የዘርፉ ባለሙያዎች ጋር ለመስራት እንድ
Feb 251 min read


የአካቶ ትምህርት ዘርፉ ከሚጠይቀው ሰፊ ፋይናንስ አቅም እና ካለው የባለሙያ እጥረት አኳያ
የካቲት 17/2018 ትምህርት ለሁሉም ሰው እኩል ማዳረስ የትምህርት ሚኒስቴር ቀዳሚ ግቤ ነው በሚል በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የተለያዩ ስራዎች ሲሰራ ይታያል ፡፡ በተለይም አካል ጉዳት እና ሌሎች ጉዳቶች ላለባቸው ሰዎች ከሌላው እኩል የትምህርት ተጠቃሚ ማድረግ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኢትዮጵያ ህግ ቀርፃ ሰው አሰልጥና ለመስራት ደፋ ቀና እያለች ነው፡፡ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት ትምህርት ቤቶች የአካል ጉዳት ያለባቸው ህፃናት ከእድሜ እኩዮቻቸው እኩል ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ አለባቸው በሚል የአካቶ ትምህርት ትግበራ እንዲተገበር እያደረገ ነው፡፡ ነገር ግን ዘርፉ ከሚጠይቀው ሰፊ ፋይናንስ አቅም እና ካለው የባለሙያ እጥረት አኳያ አተገባበሩ ፈታኝ እያደረገው መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ሲናገሩ ይደመጣል፡፡ ሸገር ራዲዮ ያነጋገራቸው የ
Feb 241 min read


ኢትዮጵያን ከሌሎች ሀገሮች ልዩ ከሚያደርጓት ስርዓቶች አንዱ የቡና አፈላል ስርዓቷ ነው፡፡
የካቲት 17/2018 ኢትዮጵያን ከሌሎች ሀገሮች ልዩ ከሚያደርጓት ስርዓቶች አንዱ የቡና አፈላል ስርዓቷ ነው፡፡ ቡና በኢትዮጵያ ከተሞችም ሆነ ገጠራማ አካባቢዎች ላይ የተለየ የአቀራረብ ስርዓት አለው፡፡ ይህ የቡና አፈላል ሥርዓትና ሂደት ኢትዮጵያ አለማቀፍ ቅርስ አድርጋ ለማስመዝገብ ስራ መጀመሯም እየተነገረ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የቡና አፈላል ሥርዓት (የቡና ሥነ-ሥርዓት) በዓለም አቀፉ የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (UNESCO) በማይዳሰሱ የባህል ቅርሶች መዝገብ ላይ እንዲሰፍር ለማድረግ ስራ ከጀመረች ሰንብታለች፡፡ ኢትዮጵያ የቡና (Arabica Coffee) መገኛ ምድር ብቻ ሳትሆን፣ ቡናን ከመጠጥነት ባለፈ የማኅበራዊ መስተጋብር፣ የሰላም፣ እና የባህል መገለጫዋ እንደሆነ ይነገራል፡፡ በተጨማሪም የቡና አፈላል ሥነ-ሥርዓት በኢትዮጵያውያን ዘንድ የ
Feb 241 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

