top of page


በኢትዮጵያ በጨርቃ ጨርቅ እና አልባሳት ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች፤ የሚደርስባቸው የመብት ጥሰት ቀጥሏል ተብሏል፡፡
ህዳር 26 2018 በኢትዮጵያ በጨርቃ ጨርቅ እና አልባሳት ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች፤ የሚደርስባቸው የመብት ጥሰት ቀጥሏል ተብሏል፡፡ ይህ የተባለው ፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ (Forum For Social Studies) የተሰኘ ተቋም በጨርቃ ጨርቅ እና አልባሳት ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞችን በተመለከተ እየሰራው ላለው ፕሮጀክት ከሚመለከታቸው አካላት ግብዓት ለመሰብሰብ ባዘጋጀው መድረክ ላይ ነው፡፡ የፕሮጅክቱ ከዋኝ ብድን አባል የሆኑት ደግነት አበባው(ዶ/ር) በጨርቃ ጨርቅ እና አልባሳት ኢንዱስትሪዎች ተቀጥረው የሚሰሩ ሰራተኞች የበዙ ችግሮች እየገጠሟቸው እንደሆነ አንስተዋል፡፡ ከሀገሪቱ የዋጋ ንረት ጋር የማይጣጣም ክፍያ፣ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል ያለመወሰን፣ እንዳይደራጁ መከልከል፣ ምቹ ያልሆነ የስራ ቦታን ጨምሮ ሌሎች ተደራራቢ ችግሮች
Dec 52 min read


''በሩብ ዓመቱ 3,319 የመድሀኒት እና የክትባት የጎንዮሽ ጉዳት ሪፖርቶች ደርሰውኛል'' የምግብና መድሀኒት ባለስልጣን
ህዳር 26 2018 በሩብ ዓመቱ 3,319 የመድሀኒት እና የክትባት የጎንዮሽ ጉዳት ሪፖርቶች ደርሰውኛል ሲል የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ተናገረ፡፡ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በ2018 ሩብ ዓመት፣ 723 የመድኃኒት የጎንዮሽ ጉዳት ሪፖርቶችን(ADE) እንዲሁም 2,596 የክትባት የጎንዮሽ ጉዳት ሪፖርቶችን (AEFI) በድምሩ 3,319 ሪፖርቶች እንደሰበሰበ ተናግሯል፡፡ በተጨማሪም 15 አስከፊ የመድኃኒት ወይም የክትባት የጎንዮሽ ክስተት ሪፖርቶችን የማጣራት ስራ ሰርቻለሁም ብሏል፡፡ 257 አዳዲስ የህክምና መሳሪያዎች ሰነድ በመገምገም የገበያ ፈቃድ እንደሰጠም ተናግሯል፡፡ ለ13 ህክምና መሳሪያ አስመጪና አከፋፋይ ደግሞ የቅድመ ፈቃድ ኢንስፔክሽን አድርጎ የብቃት ማረጋገጫ እንደተሰጠም አስረድቷል፡፡ የህክም ሙከራ እንድካሄድ የተፈቀደላቸዉን ተቋማት ላ
Dec 51 min read


ትክክል ያልሆኑ መረጃዎችን የሚያሰራጩ ማህበራዊ መገናኛ ብዙሃንን እንዴት በህግ ተጠያቂ ማድረግ ይቻላል?
ህዳር 26 2018 ማህበራዊ የመገናኛ ብዙሃን በብዙ ሰዎች እንደ አማራጭ የመረጃ ምንጭ ይታያሉ። ሁሉም ላይ ባይሆንም ታዲያ በእነዚህ የማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን ላይ ቅሬታዎች ይሰማሉ። መደበኛ መገናኛ ብዙሃን በብዙ ጥረት ያዘጋጁትን መረጃ የራሳቸው አድርገው ያቀርባሉ፣ ጫፍ ብቻ ይዘው ትክክል ያልሆኑ መረጃዎችንም ያሰራጫሉ በሚል ይወቀሳሉ። ለመሆኑ በዚህ አይነቱ ተግባር የሚሳተፉ ማህበራዊ መገናኛ ብዙሃንን እንዴት በህግ ተጠያቂ ማድረግ ይቻላል? ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… ማርታ በቀለ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡...
Dec 51 min read


ሕብረት ኢንሹራንስ በ2017 በጀት ዓመት በታሪኬ ለመጀመሪያ ጊዜ በቢሊዮን የሚቆጠር ትርፍ አገኘሁ አለ።
ህዳር 26 2018 ሕብረት ኢንሹራንስ በ2017 በጀት ዓመት በታሪኬ ለመጀመሪያ ጊዜ በቢሊዮን የሚቆጠር ትርፍ አገኘሁ አለ። በአንድ አክሲዮን የተመዘገበው ትርፍ 68.55 በመቶ መሆኑን ኩባንያው ዛሬ ባካሄደው ዓመታዊ የባለ አክሲዮኖች ጉባኤ ላይ ያቀረበው ሪፖርት ተናግሯል። ሕብረት ኢንሹራንስ በ2017 በጀት ዓመት ከግብር በፊት 1 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማግኘቱን የተናገረ ሲሆን ይህም ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ79 በመቶ ጭማሬ አሳይቷል ብሏል። ኩባንያው ከግብር በኋላ ያገኘው የተጣራ ትርፍ 843 ሚሊዮን ብር ሲሆን ይህም ከቀዳሚው አመት ጋር ሲነፃፀር በተመሳሳይ የ79 በመቶ እድገት ማሳየቱን ከሪፖርቱ ተመልክተናል። በአንድ አክሲዮን የተመዘገበው ትርፍ (Earnings Per Share) አምና ከነበረው በ47.78 ከመቶ ወደ 68.55 ከመቶ ከፍ ያ
Dec 52 min read


ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባካሄደው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ የብር የመግዛት አቅም ከዶላር አንፃር በ6 ብር ተዳክሟል፡፡
ህዳር 25 2018 ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባካሄደው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ የብር የመግዛት አቅም ከዶላር አንፃር በ6 ብር ተዳክሟል፡፡ ከጊዜ ወደ ጊዜ መጠናከር እንዳለበት የሚጠበቀው የብር የመግዛት አቅምን እየተዳከመ ቀጥሏል፡፡ ይህም የሰዎችን የመግዛት አቅም የሚፈትን፤ በተለይ ከውጭ የሚመጡ ቁሶችን ዋጋ ደግሞ እጅጉ የሚያስወድድ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ ከወጭ ንግድ እና ከተለያዩ የውጭ ምንዛሬ ማግኛ ምንጮች እየተገኘ ያለው ዶላር ከአምናው ጋር ሲነፃፀር ከፍ ያለ መሆኑ እና በመሰል ምክንያቶች የውጭ ምንዛሬ ገበያው በራሱ መረጋጋት ይጠበቅበት ነበር ያሉት የፕራግማ ካፒታል መስራችና የፋይናንስና ኢንቨስትመንት ባለሙያው መርዕድ ፍቅረዮሐንስ ናቸው፡፡ ይሁንና በብልሹ አሰራር ፣ በባንኮች ግልፅ ያልሆነ የውጭ ምንዛሬ ግብይትና በተለያዩ ች
Dec 41 min read


ከአርሶ አደሮች እና አቅራቢዎች በፈረሡላ 8,000 እና 9,000 ብር ይገዛ የነበረ ቡና ዋጋ በእጥፍ በመጨመሩ ላኪዎች እየተቸገሩ ነው ተባለ።
ህዳር 25 2018 ከአርሶ አደሮች እና አቅራቢዎች በፈረሡላ 8,000 እና 9,000 ብር ይገዛ የነበረ ቡና ዋጋ በእጥፍ በመጨመሩ ላኪዎች እየተቸገሩ ነው ተባለ። ላኪዎች በዚህ ዋጋ ቡና እየገዙ ለአለም ገበያ ማቅረብ እንደሚከብዳቸው የኢትዮጵያ ቡና ማህበር ተናግሯል። አርሶ አደሮች እና ላኪዎች ዋጋውን ከፍ ያደረጉት ወደፊት ይበልጥ ይጨምራል በሚል ግምት እንደሆነም ማህበሩ ጠቅሷል። ወደ ውጪ ቡና የሚልኩ ነጋዴዎች ከአርሶ አደሮች እና አቅራቢዎች ምርቱን የሚገዙበት ዋጋ ከተወሰነ ጊዜ ወዲህ ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን የኢትዮጵያ ቡና ማህበር ተናግሯል፡፡ የማህበሩ ዋና ስራ አስኪያጅ ግዛት ወርቁ እንዳሉት ቀደም ሲል በፈረሱላ ስምንት ሺህ እና ዘጠኝ ሺህ ብር ከአርሶ አደሮችና አቅራቢዎች ይገዛ የነበረ ቡና አሁን በፈረሱላ እስከ ሃያ ሺህ ብር እየተባ
Dec 41 min read
ህዳር 25 2018 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የሁለት ሚኒስትሮችን እና የአንድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሹመትን አፀደቀ።
ሹመታቸው በምክር ቤቱ የፀደቀላቸው የሠላም ሚኒስትሩ አቶ መሃመድ እድሪስ፤ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቢንያም ኤሮ ናቸው። አቶ መሃመድ እድሪስ የሰላም ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተሹመው ስራ የጀመሩት ኀዳር 18 ቀን 2017 ዓ.ም እንደነበር ይታወሳል። አቶ አዲሱ አረጋ ደግሞ ሐምሌ 25/ 2017 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትሩ የግብርና ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል፡፡ አንድ የምክር ቤቱ አባል በተለይ የሠላም ሚኒስትሩ አቶ መሃመድ እድሪስ ከተሾሙ ዓመት እንዳለፋቸው በመጥቀስ ሹመቱ እስከ አሁን በምክር ቤቱ ሳይጸድቅ መቆየቱ አግባብ ነው ወይ? የሚል ጥያቄ አንስተዋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሠ ጫፎ በሰጡት ምላሽ በተለያዩ ምክንያቶች ሹመቱ በምክ
Dec 41 min read


ህዳር 25 2018 በግብርናው ዘርፍ ለመሰማራት ፈቃድ ወስደው ሰፈራ መሬት ከወሰዱ ባለሀብቶች እስከ 75 በመቶው ወደ ልማት ሲገቡ አይታይም፡፡
መሬቱ ላይ ለመስራት ሳይሆን በተሰጣቸው የኢንቨስትመንት ፈቃድ የባንክ ብድር ለማግኘት አልመው ወደዚህ ስራ የሚገቡ አሉ ተብሏል፡፡ በኢትዮጵያ 7,000 የሚሆኑ ባለሃብቶች በእርሻ ኢንቨስትመንት ለመሰማራት 2.2 ሚሊየን ሄክታር መሬት በተለያዩ ክልሎች መውሰዳቸውን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ባለሃብቶቹ መሬቱን የወሰዱት ለገበያ የሚውሉ የተለያዩ ሰብሎችን ለማምረት እንደሆነ መረጃው ያመለክታል። ለግብርና ኢንቨስትመንት ከተሰጠው 2 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት እስከ አሁን ባለሃብቶቹ የለማው ግን 25 በመቶው ብቻ እንደሆነ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ ተናግረዋል። የለማው 25 በመቶ መሬትም ቢሆን ምርታማነቱ አጥጋቢ እንዳልሆነ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ፤ የመስሪያ ቤታቸውን የ2018 በጀት አመት የሶስት
Dec 42 min read


600 ሚሊዮን አፍሪካዊያን አሁን ድረስ የኤሌክትሪክ ብርሃን ማየት እንዳልቻሉ የአፍሪካ ህብረት ተናገረ።
ህዳር 24 2018 600 ሚሊዮን አፍሪካዊያን አሁን ድረስ የኤሌክትሪክ ብርሃን ማየት እንዳልቻሉ የአፍሪካ ህብረት ተናገረ። ባለው የተደራሽነት ችግር ምክንያት 1 ቢሊዮን ገደማ አፍሪካዊያን ምግባቸውን የሚያበስሉት ንፅህናውን ባልጠበቀ እና ባህላዊ በሆነ መንገድ ነውም ተብሏል። ይህ የተባለው ፊታችን ታህሳስ 1 እና 2 2018 ዓ.ም የሚካሄደውን የአፍሪካ ኢነርጂ ብቃት ጉባኤን በተመለከተ ለጋዜጠኞች መግለጫ በተሰጠበት ወቅት ነው። መግለጫውን የሰጡት በአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማትና ኢነርጂ ኮሚሽነር የሆኑት ሌራቶ ማታቦጌ፤ አፍሪካ ኤሌክትሪክን ለህዝቧ ለማዳረስ ገና ብዙ ስራዎች ይጠብቋታል ብለዋል። የጉባኤው አላማ የህብረቱ አባል ሃገራት በኤነርጂው ዘርፍ ያላቸውን ተሞክሮ የሚጋሩበት፣ በየሃገራቱ ያሉ የኤነርጂ ብቃትና ቁጠባ ስትራቴጂዎች አተገ
Dec 31 min read


የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ 100ሚሊዮን ብር ወጪ ያደረገበትንና የቁጥጥር ባለሙያዎቹን የሚከታተልበት ቴክኖሎጂ ወደ ስራ ማስገባቱን ተናገረ።
ህዳር 24 2018 የአዲስ አበባገቢዎች ቢሮ 100ሚሊዮን ብር ወጪ ያደረገበትንና የቁጥጥር ባለሙያዎቹን የሚከታተልበት ቴክኖሎጂ ወደ ስራ ማስገባቱን ተናገረ። ግብር ከፋዮችን ለመከታተል የሚሰማሩ የመስሪያ ቤቱ የቁጥጥር ባለሙያዎችን ካሜራ የተገጠመበት የደምብ ልብስ አልብሶ ማሰማራቱን ቢሮው ዛሬ ጋዜጠኞችን ጠርቶ በሰጠው መግለጫ ተናግሯል። የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ ወደዚህ ስራ የተገባበትን ምክንያት ሲያስረዱ የቁጥጥር ባለሙያዎች ያለ አግባብ ይቀጡናል፤የእጅ መንሻ እንድንሰጥ ይደራደሩናል የሚሉና ሌሎችም ቅሬታዎች ተደጋግመው ከግብር ከፋዩ የሚመጡ በመሆኑ ለዚህ ምላሽ ለመስጠት ነው ብለዋል። ባለሙያዎቹ የሚለብሱት ካሜራ የተገጠመበት የደምብ ልብስ በቀጥታ በማዕከል ከተተከለው የቁጥጥር ካሜራ ጋር የተገናኘ ነው የሚሉት አቶ ቢኒያም፤
Dec 31 min read


በኢትዮጵያ በአለም አቀፍ ለጋሾች ድጋፍ መቀነስ በኤችአይቪ መከላከልና ህክምናው ላይ እያሳደረ ያለው ተፅዕኖ
ህዳር 24 2018 በኢትዮጵያ በአለም አቀፍ ለጋሾች ድጋፍ መቀነስ ምክንያት በኤችአይቪ መከላከልና ህክምናው ላይ ተጽዕኖ እንዳይበረታ ካልተሰራ የበሽታውን መከላከል ስራ ወደኋላ እንዳይመልሰው ያሰጋል ተባለ፡፡ ለዚህም በመንግስት እንዲሁም በአገር በቀል ድርጅቶች በኩል የሚሰራው ስራ መጠናከር እንዳለበት ተነግሯል፡፡ የአለም ኤድስ ቀን በኢትዮጵያ እየታሰበ ነው፤ የዘንድሮ ቀን የሚታሰበው ደግሞ ችግሮችን በመቋቋም የኤችአይቪ ኤድስ ( #HIV_AIDS ) ምላሽ ዘላቂነት ማረጋገጥ ላይ አተኩሮ ነው ተብሏል፡፡ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች የድጋፍ መቀነስ በተለይም የበሽታው መከላከል ላይ ተጽእኖ ከዚህ በላይ እንዳይሰፋ የሀገር ውስጥ ሀብት በማሰባሰብ አገልግሎቶች እንዳይቋረጡ ማድረግ ላይ መሠራት እንዳለበት የተነግሯል፡፡ በኢትዮጵያ በድጋፍ ላይ የሚሰሩት
Dec 32 min read


የአ/አ ት/ት ቢሮ ከት/ቤቶች ጥሩ ውጤት ላስመዘገቡ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት ለወላጆች ቅሬታ ፈጥሯል
ህዳር 24 2018 የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ከመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች ጥሩ ውጤት ላስመዘገቡ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት ለወላጆችና መምህራን ቅሬታ ፈጥሯል፡፡ ቢሮው ከ256 ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ 40,000 ተማሪዎች በ54 ማዕከላት በተሻለ የማስተማር ችሎታቸው በተመረጡ መምህራን ከመደበኛው የትምህርት ቀን ወጪ የማጠናከሪያ ትምህርት እየሰጠሁ ነው ብሎ ነበር፡፡ እንዲህ ዓይነቱ አሰራር በሌሎች ሀገራትም የተለመደ ቢሆንም ከተማሪ ወላጆችና መምህራን በማጠናከሪያው ላልተካተቱ ተማሪዎችስ ምን ታስቧል? የሚል ጥያቄ አስነስቷል፡፡ የተማሪ ወላጆችና መምህራን ጥሩ ውጤት ላላቸው ተማሪዎች ማጠናከሪያ ከመስጠት፣ በትምህርት አቀባበላቸው ደከም ያሉትን ማበረታታት አይሻልም ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ትምህርት ቢሮው
Dec 31 min read


ከተሰጣቸዉ የስልጣን ድንበር ተሻግረዉ የሚሰሩ ኤጀንሲዎች
ህዳር 23 2018 መመሪያዉ በሚጠይቀዉ፣ ህጉ በሚያስገድደዉ ልክ ሆነዉ፣ ቢሮ ከፍተዉ ሰራተኛ ቀጥረው፣ ህጋዊ ሆነዉ፣ ፍቃድ አዉጥተው፣ ሰራተኛን ወደ ውጪ ለመላክ ሃላፊነት ወስደዉ፣ ደንብ አክብረዉ በስነምግባር የሚሰሩ ኤጀንሲዎች አሉ፡፡ ነገር ግን ህጋዊ ፋቃድን ተገን አድርገው፣ የተጣለባቸዉን ሃላፊነት ወደ ጎን ትተው፣ ህግ ጥሰው፣ ደንብ ተላልፈው፣ ከተሰጣቸዉ የስልጣን ድንበር ተሻግረዉ የሚሰሩ ኤጀንሲዎች ቁጥራቸዉ ትንሽ አይደለም፡፡ በተለይም ከተፈቀደላቸዉ ሀገር ውጪ መላክ፣ በተለያዩ ህግ መተላለፎች ፍቃዳቸዉ ከተሰረዘ በኋላ መስራትና ገንዘብ መቀበል በተደጋጋሚ ኤጀንሲዎች የሚጠየቁባቸዉ ጥፋቶች እንደሆነ ይነሳል፡፡ በተለይም ኤጀንሲዎች በምንም ምክንያት ስራ ፈልገዉ ከሚሄዱ ሰዎች ብር መቀበል እንደማይችሉ በህግ ተጠቅሶ፣ በአዋጅ ሰፍሮ ቢገኝም
Dec 22 min read


''በኢትዮጵያ የሚካሄደው የጣሊያን የምግብ ሳምንት የሁለቱን ሀገራት ወዳጅነት ይበልጥ እንዲጠናከር እያደረገ ነው'' የጣሊያን ኤምባሲ
ህዳር 23 2018 በኢትዮጵያ የሚካሄደው የጣሊያን የምግብ ሳምንት የሁለቱን ሀገራት ወዳጅነት ይበልጥ እንዲጠናከር እያደረገ ነው ሲል አዲስ አበባ የሚገኘው የጣሊያን ኤምባሲ ተናገረ፡፡ ለ4 ቀናት የተካሄደው የጣሊያን የምግብ ሳምንት መጠናቀቁንም ሰምተናል፡፡ ዝግጅቱን የጣሊያን የንግድ ኤጀንሲ በኢትዮጵያ ከሚገኘው የጣሊያን ኤምባሲ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን ሲካሄድም ለ10ኛ ጊዜ ነው፡፡ የጣሊያን የምግብ ዝግጅት ሣምንት የጣሊያን የምግብ ባህል ያስተዋወቀ እንዲሁም ጣሊያን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የቆየ ወዳጅነት ያሳየ ሆኖ ተጠናቋል ሲሉ በአዲስ አበባ የጣሊያን ንግድ ኤጀንሲ የንግድ ኮሚሽነር ክላውዲዮ ፓስኳሉቺ ተናግረዋል፡፡ ‘’የጣሊያን ሼፎችን ከኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች እና ተማሪዎች ጋር በማገናኘት የባህል ዲፕሎማሲውን እንዲጠናከር
Dec 21 min read


ከ25 ዓመታት በኋላ ከአውሮፕላን የሚወጣውን በካይ ጋዝ ወደ ዜሮ የተጠጋ ለማድረግ ኢትዮጵያ እንዴት እየተዘጋጀች ነው?
ህዳር 22 2018 ከ25 ዓመታት በኋላ ከአውሮፕላን የሚወጣውን በካይ ጋዝ ወደ ዜሮ የተጠጋ ለማድረግ በአለም ላይ እቅድ አለ፡፡ ኢትዮጵያ ለዚህ እንዴት እየተዘጋጀች ነው? የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣንን ጠይቀናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ቴዎድሮስ ወርቁ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬WhatsApp https://tinyurl.com/ycxjmm3s 🐦X : https://x.com/shegerfm?s=2
Dec 11 min read


በዓመት በአማካይ እስከ 2,000 ጉዳዮች የመጨረሻ ውሳኔ እንዲያገኙ ለፌዴሬሽን ም/ቤት እየላከ መሆኑን፤ የህገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ተናገረ፡፡
ህዳር 22 2018 በዓመት በአማካይ ከ1,500 እስከ 2,000 ጉዳዮች የመጨረሻ ውሳኔ እንዲያገኙ ለፌዴሬሽን ም/ቤት እየላከ መሆኑን የህገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ተናገረ፡፡ የፌዴሬሽን ም/ቤት በዓመት ሁለት ጊዜ ብቻ ስለሚሰበሰብ የሚሰጠው የመጨረሻ ውሳኔ እንዲዘገይ አድርጎታል ሲልም ጉባኤው ነግሮናል፡፡ ጉባኤው ህገ-መንግስታዊ ትርጓሜን የሚሹ አቤቱታዎችን ተቀብሎ በመመርመር የተለያዩ ውሳኔዎችን ያስተላልፋል፡፡ ውሳኔው የመጨረሻ ባለመሆኑ ውሳኔውን በምክረ ሃሳብ መልክ ለፌደሬሽን ምክር ቤት ያቀርባል፤ምክር ቤቱም ጉዳዩን ተመልክቶ የመጨረሻውን ውሳኔ ይሰጣል ሲል ጉባኤው ነግሮናል፡፡ አቶ ደበበ ሃይለገብርኤል የህግ ባለሙያና የጉባኤው አባል ናቸው፤ጉባኤው እነዚህን ስራዎች ሲከውን ቆይቷል በዓመትም በአማካኝ ከ1500 እስከ 2000 ጉዳዮችን ተ
Dec 11 min read


በኢትዮጵያ በዓመት ከ10,000 በላይ ሰዎችን የሚገድለው ኤችአይቪ ኤድስ
ህዳር 22 2018 በኢትዮጵያ በዓመት ከ10,000 በላይ ሰዎች የሚገድለው ኤች አይቪኤድስ የሚያዙ ሲሆን ከአስር ሺህ ባላይ የሚሆኑት ደግሞ ይሞታሉ፡፡ ዛሬ በለም አቀፍ ደረጃ የጸረ ኤችአይቪ ኤድስ ቀን ነው፡፡ በኢትዮጵያ በዓመት ከ7,000 በላይ ሰዎች በኤች አይቪኤድስ የሚያዙ ሲሆን ከአስር ሺህ ባላይ የሚሆኑት ደግሞ ይሞታሉ፡፡ የበሽታው የስርጭት ምጣኔው በተለይ በወጣቶች ላይ ከፍተኛ ነው፡፡ ግንዛቤው ደግሞ ዝቅ ብሎ ይታያል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ምህረት ስዩም የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘F
Dec 11 min read


ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (IGAD) የህይወት ዘመን ጋዜጠኝነት ሽልማት ተሰጣቸው።
ህዳር 22 2018 ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (IGAD) የህይወት ዘመን ጋዜጠኝነት ሽልማት ተሰጣቸው። የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ራዲዮ መስራችና ስራ አስኪያጅ #መዓዛ_ብሩ ሽልማቱ የተሰጣቸው የኢጋድ(IGAD) ዓመታዊ የሚዲያ ሽልማት በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ በተካሄደበት ወቅት ነው። ሽልማቱንም ከኢትዮጵያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስና ከኢጋድ ዋና ፀሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር ) ተቀብለዋል። ኢጋድ በየዓመቱ በተለያዩ ዘርፎች የአባል ሀገራትን የተመለከቱ ዘገባ የሰሩ ጋዜጠኞችን የሚሸልም ሲሆን ዘንድሮም የአየር ንብረት ለውጥን የተመለከቱ ዘገባዎች የሰሩ ጋዜጠኞች ስራ አወዳድሮ ሸልሟል። የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.sheger
Dec 11 min read


በቤታችሁ ያለ ቴሌቭዥን፣ ሪሞታችሁ፣ ስልክ እና ላፕቶፓችሁ የአገልግሎት ዘመኑ ሲያበቃ ምንድነው የምታደርጉት?
ህዳር 19 2018 በቤታችሁ ያለ ቴሌቭዥን፣ ሪሞታችሁ፣ ስልክ እና ላፕቶፓችሁ የአገልግሎት ዘመኑ ሲያበቃ ምንድነው የምታደርጉት? እነዚህን መገልገያዎች ሰብስቦ መወገድ ያለባቸውን የሚያስወግድ እና መልሶ ጥቅም ላይ በመዋል ሀብት እንዲሆኑ በማስቻል የሚሰራ ድርጅት እንዳለ ተነግሯል፡፡ በቤታችሁ ወይም በድርጅቶቻችሁ ውስጥ ያሉ መሰል የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ሲበላሹባችሁ ያላችሁበት ድረስ መጥቼ አስወግድላችኋለሁ ሲል ኢንተር ኢትዮጵያ ሶሉሽን (Inter Ethiopia Solution) የተሰኘ ድርጅት ተናግሯል፡፡ የአገልግሎት ጊዜአቸውን የጨረሱ፣ የተበላሹ፣ የተጎዱ በአጠቃላይ ከጥቅም ውጭ የሆኑ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን የሚሰበስበው ይሄው ተቋሙ የሰበሰባቸውን እቃዎችም እንዲሁ እንደማያስወግዳቸው ነግሮናል፡፡ ይልቁንም ከጥቅም ውጭ ናቸው የተባሉትን እነዚህን እቃዎች
Nov 281 min read


የአካል ጉዳተኞች ፖሊሲ በረቂቅ ደረጃ ተሰናድቶ ለመፅደቅ ዳር መድረሱ ተነግሯል
የህዳር 19 2018 አካል ጉዳተኞች አለብን የሚሏቸውን ችግሮች ይፈታል፤ የተባለ የተጠቃለለ የአካል ጉዳተኞች አዋጅ ወጥቶ ሳይፀድቅ ዓመታትን ወስዷል፡፡ አሁን የአካል ጉዳተኞች ፖሊሲ በረቂቅ ደረጃ ተሰናድቶ ለመፅደቅ ዳር መድረሱ ተነግሯል፡፡ ፖሊሲው ቀድሞ ህጉ ከፖሊሲው የተቀዳ መሆን ቢጠበቅበትም ከፈረሱ ጋሪው ቀድሟል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… ፋሲካ ሙሉወርቅ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/y
Nov 281 min read


ወተት አምራቾች፤ ለእንስሳቶች የሻገቱ እና የተበከሉ መኖ እንዳይሰጡ የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን መከረ።
ህዳር 19 2018 ወተት አምራቾች፤ ለእንስሳቶች የሻገቱ እና የተበከሉ መኖ እንዳይሰጡ የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን መከረ። ደህንነቱ ያልተጠበቀ መኖ ለእንስሳቶች መስጠት ለወተት መበከል ትልቅ አስተዋፅኦ አሏቸው ብሏል ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ። የወተት ምርት በባህሪው በጣም ጥንቃቄ የሚሻ በመሆኑ ከእንስሳት መኖ ጀምሮ ተጠቃሚው ድረስ የሚሳተፉ አካላት ወተቱ እንዳይበከል መስራት አለባቸው ብሏል። በሀገሪቱ መደበኛ ያልሆነ የወተት ሽያጭ በሰፊው እንደሚስተዋልም አስረድቷል። በተለይም በየሰፈሩ በጄሪካን አየዞሩ ከሚሸጡት ላይ ገዝታችሁ እንድትጠቀሙ አልመክርም ሲልም መስሪያ ቤቱ ጠቅሷል፡፡ ወተት ቶሎ የሚበላሽ እና በፋብሪካ ተመርምሮ እስኪመጣ ተሽጦ ሊያልቅ የሚችል መሆኑ ቁጥጥር የሚያደርገው አካል ስራን ውስብስብ የማድረግ እድሉ ሰፊ ነው ተብሏል። እንዲ
Nov 281 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page








