top of page

በኢትዮጵያ እያንዳንዱ ብሄረሰብ የራሱን ታሪክ ብቻ ለይቶና አጉልቶ የሚያቀርብበት ስርዐት መቀየር እንዳለበት የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ተናገሩ ።

  • 2 hours ago
  • 1 min read

ሐምሌ 23 2018


በኢትዮጵያ እያንዳንዱ ብሄረሰብ የራሱን ታሪክ ብቻ ለይቶና አጉልቶ የሚያቀርብበት ስርዐት መቀየር እንዳለበት የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ተናገሩ ።


በኢትዮጵያ የብሄረሰቦች ታሪክ ጥልቅ ትስስር እና መስተጋብር ያለው ነው ብለዋል።


የኢትዮጵያ የታሪክ ባለሞያዎች ማህበር ከላይፍ ኤንድ ፒስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው እና ትኩረቱን በኢትዮጵያ ታሪክ ዙሪያ ያደረገ ጉባዔ እየተካሄደ ነው፡፡


"ኢትዮጵያን ከፖለቲካ አመፃ ታሪክ እንዴት ነፃ ማውጣት ይቻላል" በሚል ርዕስ እየተካሄደ ባለው በዚህ ጉባዔ ላይ የተለያዩ ጥናታዊ ፅሁፎች እየቀረቡ ነው ።


የማህበሩ ፕሬዚዳንት የሆኑት የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ጉባዔው በኢትዮጵያ ታሪክ አፃፃፍ ዙሪያ ያሉ ችግሮችን የሚጠቁም እንደሆነ ነግረውናል።


አሁን ያለው የታሪክ አቀራረብ እያንዳንዱ ብሄረሰብ የራሱን ብቻ ለይቶና አጉልቶ የሚያቀርብበት እንደሆነ ጠቅሰዋል ።


ንጋቱ ረጋሳ



Recent Posts

See All
በ2018 በጀት ዓመት ከ1.2 ቢሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።

ሐምሌ 23 2018 በ2018 በጀት ዓመት ከ1.2 ቢሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። በየዓመቱ በሀገሪቱ የሚገኘው የምርት መጠን እያደገ እንደሚመጣ ሪፖርቶች ያመልክታሉ። በገበያው ውስጥ ግን የምርት ዋጋ ከአመት አመት እየጨመረ እንጂ ሲቀንስም አይታይም። ይህ ለምን ሆነ? እውነትስ

 
 
 
እድሜያቸው ከ14 እስከ 24 የሆኑ አፍላ ወጣቶች በተለይም ሴቶች ላይ እየታየ ያለው የኤች አይ ቪኤድስ ስርጭት በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ መምጣቱን፣ ይህም ከፍተኛ ትኩረትእንደሚያስፈልገው ኔፕ ፕላስ (NEP+) የተባለ ድርጅት ተናገረ።

ሐምሌ 23 2018 እድሜያቸው ከ14 እስከ 24 የሆኑ አፍላ ወጣቶች በተለይም ሴቶች ላይ እየታየ ያለው የኤች አይ ቪኤድስ ስርጭት በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ መምጣቱን፣ ይህም ከፍተኛ ትኩረትእንደሚያስፈልገው ኔፕ ፕላስ (NEP+) የተባለ ድርጅት ተናገረ። Network of Networks of HIV Positives in

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page