top of page


የፌደራል ግብር ከፋዮች በኮቴ ክፍያ፣ ነጋዴዎች ደግሞ በግብር ሰብሳቢዎች ስነ ምግባር ጉድለት መማረራቸው በፓርላማው ተነገረ፡፡
ታህሳስ 3/2018 የፌደራል ግብር ከፋዮች በኮቴ ክፍያ፣ ነጋዴዎች ደግሞ በግብር ሰብሳቢዎች ስነ ምግባር ጉድለት መማረራቸው በፓርላማው ተነገረ፡፡ የገቢዎች ሚኒስቴር በበኩሉ የኬላ ጉዳይ ከፍተኛ አጀንዳ ሆኖ መቆየቱን፤ እስካሁን ግን መፈታት እንዳልተቻለ ተናግሯል፡፡ የኮቴ ክፍያና የገቢ ሰብሳቢ ሰራተኞች ስነ ምግባር ጉዳይ ለህዝብ ተወካዬዎች ምክር ቤት እና ሌሎች ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት ማቅረቡን የፕላን ፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተናግሮ፤ ለዚህም ማብራሪያ እንዲሰጠው የገቢዎች ሚኒስቴርን ጠይቋል፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ይህን የጠየቀው ዛሬ ታህሳስ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የገቢዎችን ሚኒስቴርን የ4 ወራት የስራ ክንውን ሪፖርትን ባደመጠበት ወቅት ነው፡፡ የሪፖርቱን ማብቃት ተከትሎ የቋሚ ኮሚቴውን ሪፖርት በንባብ ያቀረቡት የገቢ ዘ
18 minutes ago2 min read


ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የተከፈለ ካፒታሉ 5 ቢሊዮን ብር እንደደረሰ ተናገረ፡፡
ታህሳስ 3/2018 ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የተከፈለ ካፒታሉ 5 ቢሊዮን ብር እንደደረሰ ተናገረ፡፡ ይህም ትልቅ ስኬት ነው ብሏል፡፡ በ2016 በጀት ዓመት የባንኩ የተከፈለ ካፒታል 2.4 ቢሊዮን ብር እንደነበር ያስታወሰው ባንኩ በአንድ ዓመት ውስጥ የ102 በመቶ አድገት በማምጣት 5 በሊዮን ብር አንደደረሰ ተናግሯል፡፡ ባንኮች ካፒታላቸውን 5 ቢሊዮን ብር እንዲያደርሱ ብሔራዊ ባንክ ያስቀመጠውን መስፈርት ያስታወሰው ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከጊዜ ገደቡ በፊት ማሳካት መቻሉ በባስለክሲዮኖቹ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ዘንደ ያለውን ተቀባይነት ከጊዜ ወደ ጊዜ አያደገ መመጣቱን ያሳያል ብሏል፡፡ ይህ በመሳካቱ ባንኩ ከሎሎች ባንኮች ጋር መዋሃድ ሳይጠበቅበት እንዲቀጥል እንደሚያስችለው አና የመዋሃድም እቅድ አንደሌለው ተናግሯል፡፡ ይህ እንዲሳካም በተለይ ባለ
2 hours ago1 min read
ታህሳስ 3/2018 የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ሃይል ፍጆታ ካለፈው ሃምሌ ወር ወዲህ እያደገ መጥቷል ተባለ።
ኢትዮጵያ ከተለያዩ ምንጮች ከምታመርተው የኤሌክትሪክ ሃይል 90 በመቶው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል እንደሆነ ተጠቅሷል። በዘንድሮው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አራት ወራት ኢትዮጵያ ከውሃ እና ከነፋስ ከ15,300 ጊጋዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨቷ ተነግሯል። በየወሩ በአማካይ 3,800 ጊጋዋት ሰአት የኤሌክትሪክ ሃይል አመንጭታለች እንደማለት ነው። ከመነጨው የኤሌክትሪክ ሃይል ከ90 በመቶ ያላነሰው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ እንደዋለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ነግረውናል። የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ሃይል ፍጆታ ከጊዜ ወደ እያደገ መጥቷል ያሉት ዳይሬክተሩ ከሃምሌ ህዳር የነበረው መረጃ ይህንኑ እንደሚያሳይ ጠቁመዋል። በሀገር ውስጥ ያሉ የኤሌክትሪክ ሃይል ተጠቃሚዎች በቤት ውስጥ ካሉ ደንበኞች እስከ ትላል
5 hours ago1 min read
ታህሳስ 3/2018 ባለፉት 4 ወራት በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ የሚገባ የኮንትሮባንድ እቃዎች ቁጥር መጨመሩን የገቢዎች ሚኒስቴር ተናገረ፡፡
የገቢዎች ሚኒስቴር ይሄን ያለው ዛሬ በሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ለፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ4 ወር የስራ ክንው ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት ነው፡፡ ሪፖርቱን ያቀረቡት የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ ከገቢ ኮንትሮባንድ ከ8 ቢሊዮን ብር በላይ ፣ ከወጪ ኮንትሮባንድ ደግሞ 0.6 ቢሊየን ብር ማዳን መቻሉን ተናግረዋል፡፡ በድምሩ 8.7 ቢሊየን ብር የሚያወጣ የኮንሮባንድ እቃ መያዙን ተናግረዋል፡፡ የገቢ ኮንትሮባንድ በእጥፍ መጨመሩን የተናገሩት ሚኒስትሯ መድሃኒት፣ አልባሳት ጨርቃ ጨርቅ ፣ ኤሌክትሮኒክስ እና የማዕድን ውጤቶች ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዝ አስረድተዋል፡፡ ባለፉት 4 ወራት 27 ኪሎ ግራም የሚመዝን ጥፍጥፍ ወርቅ መያዙንም ሚኒስትሯ አክለዋል፡፡ የወጪ ኮንትሮባንድ አብዛኛውን ድርሻ የሚይዘው የግብርና ምርት ነው የተባለ
5 hours ago1 min read


ኢትዮጵያ ከአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት 261 ሚሊዮን ዶላር ብድር ለማግኘት የሚያስችላትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሷ ተሰማ።
ታህሳስ 2/2018 ኢትዮጵያ ከአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት 261 ሚሊዮን ዶላር ብድር ለማግኘት የሚያስችላትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሷ ተሰማ። ይህ የብድር አቅርቦት ስምምነት #IMF ለኢትዮጵያ ለመስጠት ካሰበው የ4 ዓመት የ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር አቅርቦት አካል ነው። የIMF እና የኢትዮጵያ መንግስት ሀላፊዎች በአዲስ አበባ እና በበይነ መረብ ባደረጉት የአራተኛው ዙር የብድር አቅርቦት ውይይት ላይ ኢትዮጵያ 261 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት የሚያስችላት የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተጠቅሷል። ይህን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት የ IMF አስተዳደር እና የስራ አስፈጻሚ ቦርድ በመጪዎቹ ሳምንታት ያፀድቀዋል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተቋሙ ጠቅሷል። የIMF የ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር አቅርቦት የተቋሙ የስራ አስፈ
1 day ago1 min read


የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ እስከ ስምንት ብር ጭማሪ ተደረገ፡፡
ታህሳስ 1 2018 የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ እስከ 8 ብር ጭማሪ ተደረገ፡፡ ጭማሪው ከዛሬ 6:00 ጀምሮ ተግባረዊ የተደረገ መሆኑን የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስረድቷል፡፡ በጭማሪው መሰረት በቤንዚን ላይ የ7 ብር ገደማ ጭማሪ ሲደረግ በኬሮሲን ላይ ደግሞ የ8 ብር ገደማ ጭማሪ ተድርጓል፡፡ ቤንዚን፣ የኬሮሲን እና ነጭ ናፍጣ የሦስቱም የነዳጅ ምርቶች ዋጋ በአዲሱ ጭማሪ መሰረት 129.12 ብር እንዲሆኑ ተድርጓል። ከሰሞኑ በዲስ አበባ ሆነ በክልሎች የነዳጅ ማደያዎች ነዳጅ የለንም ብለው ረጃጅም የተሽከርካሪ ሰልፎች ታይተው ቆይተዋል፡፡ ለዚህም ከታሕሳስ ወር አንስቶ የቫት እና የኤክሳይስ ታክስ በአጠቃላይ የ30 በመቶ ግብር ይጣላል የሚል ምክንያት በብዙዎች ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ዛሬ ለነዳጅ አ
2 days ago1 min read


የኢትዮጵያ የሎጅስቲክስ ዘርፍ በ10 ዓመታት ውስጥ ለመቀየር ከ3 ትሪሊየን ብር በላይ ያስፈልጋል ተባለ፡፡
ታህሳስ 1 2018 ከአለም ሀገራት ሲነጻጸር ቀርፋፋ የተባለውን የኢትዮጵያ የሎጅስቲክስ ዘርፍ በ10 ዓመታት ውስጥ ለመቀየር ከሶስት ትሪሊየን ብር በላይ ያስፈልጋል ተባለ፡፡ ገንዘቡን መንግስት ከሚመድበው በተጨማሪ ከረጂ ድርጅቶች እና ከሌሎች ምንጮች ለማግኘት መታሰቡን ሰምተናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ቴዎድሮስ ወርቁ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw 🟦Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1 💬WhatsApp : https://whatsapp.com/
2 days ago1 min read


የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር የባቡር መሰረተ ልማት እና ደረቅ ወደብ ግንባታን ለብቻው ለመስራት መንገድ መጀመሩን ተናገረ
ታህሳስ 1 2018 ከዚህ ቀደም በውጪ ባለሞያዎች ብቻ ይገነቡ የነበሩ የባቡር መሰረተ ልማት እና ደረቅ ወደብ ግንባታን የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ለብቻው ለመስራት መንገድ መጀመሩን ተናገረ፡፡ ለዚህም ማሳያ የሚሆን በሃገር ልጆች እውቀት እና ጉልበት የባቡር ሀዲድ ንጣፍ ስራ መጀመሩን ሰምተናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ተህቦ ንጉሴ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw 🟦Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1 💬WhatsApp :...
2 days ago1 min read


በመጪው ግንቦት መጨረሻ ስለሚካሄደው ምርጫ ዝግጅት ውይይቶችን ማድረግ ያስፈልጋል ብሏል
ታህሳስ 1 2018 የፖለቲካ ፓርቲዎች ለእጩ ተመራጮቻቸው የድጋፍ ፊርማ እንዲያቀርቡ የሚያስገድደው የህግ አንቀጽ መሻሩ እና ለእጩ ምዝገባ የጊዜ ገደቡ መራዘሙ ለሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ጥርጊያውን ያቀናል ተባለ፡፡ ይሄንን ያለው የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ነው፡፡ በመጪው ግንቦት መጨረሻ ስለሚካሄደው ምርጫ ዝግጅት ግን ውይይቶችን ማድረግ ያስፈልጋል ብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ያሬድ እንዳሻው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw 🟦Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡...
2 days ago1 min read








