top of page


በጋሞ ዞን በየመሬት መንሸራተት አደጋ መሞታቸው ከተረጋገጡ 125 ሰዎች አስክሬናቸው የተገኘው የ81 ሰዎች ብቻ ነው ተባለ፡፡
መጋቢት 7/2018 በጋሞ ዞን ከሳምንት በፊት በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ መሞታቸው ከተረጋገጡ 125 ሰዎች እስካሁን አስከሬናቸው የተገኘው የ81 ሰዎች ብቻ ነው ተባለ፡፡ የቀሪዎቹን አስከሬን ለማውጣት ሲደረግ የቆየው በቁፋሮ የታገዘ የማፈላለግ ስራም እንዲቆም መደረጉን ሰምተናል፡፡ ይህን ያለው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ነው። እንደ ቢሮው መረጃ ከሆነ አስክሬን የማፈላለግ ስራው ቆሞ የ44 ሰዎች አስከሬን አደጋው በተከሰተበት በዚያው ስፍራ የቀብር ቦታው ሆኖ እንዲቀጥል ተወስኗል ተብሏል፡፡ እዚህ ውሳኔ ላይ የተደረሰው አስከሬኑ 7 ቀን አልፎታል በሚል ነው፡፡ በአደጋው ምክንያትም ከ16 ሺህ በላይ ሰዎች ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውንም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ሃላፊ አቶ ኃይለማርያም ተ
2 hours ago1 min read


በኢትዮጵያ የኦዲት ስራ በዝቅተኛ ዋጋ የሚከወን እና ጥራቱን ያልጠበቀ በመሆኑ በገበያው ችግር እየፈጠረ ነው ተብሏል።
መጋቢት 7/2018 በሀገር የፋይናንስ ሥርዓት ከሚረበሹበት፤ ከሚታመሙበት ጉዳዮች መካከል አንደኛው የተዝረከረ የሂሳብ አያያዝና ጥራት የሌለው ጥንቅቅ ያላለ የኦዲት ሪፖርት ነው ። የኦዲት ሪፖርት ጥራቱ የደረጃውን ጠብቆ ካልተሰራ ዞሮ ዞሮ የሕዝብ ጥቅም ያለባቸውን ተቋሞች መነካካቱ አይቀርም። በፋይናንስ ሥርዓት በባንክ ፤ ማይክሮ ፋይናንስ ፤ኢንሹራንስና ሌላውም የሚደረገው የኦዲት ስራ የህዝብ ጥቅም የሀገርን ኢኮኖሚ በአንድም ሆነ በሌላ ስለሚነካ ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት ባለሙያዎች ይመከራሉ። በኢትዮጵያ የኦዲት ስራ በዝቅተኛ ዋጋ የሚከወን እና ጥራቱን ያልጠበቀ በመሆኑ በገበያው ችግር እየፈጠረ ነው ተብሏል። በዚህም ምክንያት ምክንያታዊ የኦዲት ክፍያ ስራ ላይ እንዲውል ያግዛል የተባለ አዲስ መመሪያ መውጣቱ ተሰምቷል፡፡ የኦዲት ስራ ደረጃው ዝቅ
2 hours ago1 min read


ከአዲስ አበባ ከተማ መሬት 52 በመቶው ለመንገድ፤ ለወንዝ ዳርቻ እና ለአረንጓዴ ልማት የተያዘ ነው ተብሏል።
መጋቢት 7/2018 ከአዲስ አበባ ከተማ መሬት 52 በመቶው ለመንገድ፤ ለወንዝ ዳርቻ እና ለአረንጓዴ ልማት የተያዘ ነው ተብሏል። ለመኖሪያ እንዲሁም ለመስሪና ማምረቻ ሊውል የሚችለው የከተማዋ መሬት 48 በመቶ ብቻ እንደሆነ የከተማ ልማት ባለሞያው አቶ ሢሣይ ዘነበ ይናገራሉ። ፍላጎቱን ከአቅርቦቱ ጋር እንዳይጣጣም ያደረገው አንዱ ምክንያትም ይኸው እንደሆነ ባለሞያው ይጠቅሳሉ። በየጊዜው የሚጨምረው የህዝብ ቁጥር እና ወደ ከተማዋ የሚደረግ ፍልሰት ነገሩን ከድጡ ወደ ማጡ አድርጎታልም ብለዋል። የከተማ አስተዳደሩ ይህን እጥረት ያለበት ሃብት ለግለሰቦች ከሚያስተላልፍባቸው መንገዶች አንዱ ሊዝ እንደሆነ የጠቀሱት አቶ ሢሣይ የዚህ ክፍያ ግን ከፍተኛ እንደሆነ ተናግረዋል። ይህ ከፍተኛ ክፍያ ደግሞ ግለሰቡ መሬቱ ላይ ገንዘቡን ስለሚጨርስ ለግንባታ የሚተርፈው ነገር እ
3 hours ago1 min read


በስራቸው ውጤታማ የሆኑ የአዲስ አበባ አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች የቆይታ ጊዜያቸው
መጋቢት 7/2018 በስራቸው ውጤታማ የሆኑ የአዲስ አበባ አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች የቆይታ ጊዜያቸው ቢያበቃም በተሰጣቸው የማምረቻ ቦታ ለተጨማሪ አንድ ዓመት እንዲሰሩ በከተማዋ ካቢኔ ከሠሞኑ እንደተፈቀደላቸው ተነገረ። የከተማ አስተዳደሩ በ43 ሄክታር መሬት ላይ ያስገነባቸባቸውን የማምረቻ ሼዶች በቅርቡ ለመካከለኛ እና አነስተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች ሊያስረክብ እንደሆነም ሠምተናል። በአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰማሩ አንቀሳቃሾች በተሰጣችሁ የማምረቻ ቦታ ላይ ለአምስት ዓመት ከሰራችሁ በኋላ ፤ ለሌሎች መልቀቅ አለባቸው የሚለው መመሪያ ስጋት ላይ እንደጣላቸው ተናግረዋል፡፡ በአንዳንድ አካባቢዎች የተፈቀደላችሁ ጊዜ አብቅቷል በሚል ሼዶች እየታሸጉ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት ከሠሞኑ ባዘጋጀው አንድ መድረክ ላይ
5 hours ago1 min read


በጋሞ ዞን በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ 3,461 ሰዎች ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለው ለከፍተኛ ሰብአዊ ቀውስ መጋለጣቸውን ኢሰመኮ ተናገረ፡፡
መጋቢት 4/2018 በጋሞ ዞን በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ህይወታቸው ካለፈው ሰዎች በተጨማሪ 3,461 ሰዎች ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለው ለከፍተኛ ሰብአዊ ቀውስ መጋለጣቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ተናገረ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ሙሉ በሙሉ የወደሙ መኖሪያ ቤቶች እና ማሳዎችን ጨምሮ በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ኢሰመኮ አረጋግጫለሁ ብሏል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ጋሞ ዞን፣ ጋጮ ባባ፣ ቦንኬ፣ ካምባ ዙሪያ እና ምዕራብ አባያ ወረዳዎች በሚገኙ 6የተለያዩ ቀበሌዎች የተከሰቱ የመሬት መንሸራተት፣ የናዳ እና የጎርፍ አደጋዎችን ተከትሎ የደረሱ ጉዳቶችን እየተከታተለ አንደሆነ አስረድቷል። ኮሚሽኑ መግለጫውን ዛሬ እስካወጣበት ቀን ድረስ በድምሩ የ65 ሰዎች ሕይወ
3 days ago1 min read


547 - ስለ ህገወጥ የስራ ስምሪት እና ጉዳቶቹ በተግባር ካለፉበት በላይ ማን ሊያወራ ይችላል?
ስለ ህገወጥ የስራ ስምሪት እና ጉዳቶቹ በተግባር ካለፉበት በላይ ማን ሊያወራ ይችላል? ሙሉ ዝግጅቱን ያድምጡ…… አዘጋጅ የኔነህ ሲሳይ
4 days ago1 min read


በጋሞ ዞን ሰሞኑን በተከሰተው የመሬት መንሸራተት እና የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 64 መድረሱ ተነገረ።
መጋቢት 3/2018 በጋሞ ዞን ሰሞኑን በተከሰተው የመሬት መንሸራተት እና የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 64 መድረሱ ተነገረ። የተጎዱትን በህይወት የማትረፉ ስራ ከዚህ በውሃላ ብዙም ተስፋ የለውም፣ቀሪ የአስከሬን ፍለጋ ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ ነው ተብሏል። የሟቾቹ ቁጥር 52 ስለመድረሱ አስቀድመን ነግረናችሁ የነበረ ሲሆን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የተጨማሪ ሰዎች አስክሬን መገኘቱን ተናግሯል። እስካሁን አስከሬናቸው የተገኘ የሟቾች ቁጥርም 64 ደርሷል ብሏል። የዞኑ ፖሊስ መምሪያ በአካባቢው ነዋሪ የነበሩና በአደጋው የጠፉ ሰዎች ቁጥር 128 መሆኑን ተናግሯል። እስካሁን ባለው መረጃ ከዚህ ውስጥ የ64ቱ ሰዎች አስክሬን መገኘቱን የጋሞ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር አብረሀም ቡሔ ተናግረዋል። ኢንስፔክተሩ በሶስት ወረዳዎች አደጋ ተመዝጋቧል ያሉ ሲሆን ከሁሉም
4 days ago1 min read


የዱር እንስሳት አደንና ሽያጭ ፣ የፓርኮች መራቆት፣ ግጭት እና የፋይናንስ እጥረት የዱር እንስሳትና የፓርኮች ጥበቃ ስራ ፈተና ሆኗል ተባለ።
መጋቢት 3/2018 የዱር እንስሳት አደንና ሽያጭ ፣ የፓርኮች መራቆት፣ ግጭት እና የፋይናንስ እጥረት የዱር እንስሳትና የፓርኮች ጥበቃ ስራ ፈተና ሆኗል ተባለ። ይህ የተባለው የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን የተመሰረተበትን 60ኛ ዓመት ዛሬ ሲያከብር ነው። የቱሪዝም ሚኒስትር ድኤታው አቶ ስለሺ ግርማ የኢኮ ቱሪዝምና የብርቅዬ እንስሳት ቱሪዝም ኢትዮጵያ ውስጥ እየሰፋ መጥቷል ብለዋል። ላለፉት 60 ዓመታት ህገወጥ የዱር እንስሳት አደንና ሽያጭ፣ የፓርኮች መራቆት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የፋይናንስ እጥረት ዘርፉን ሲገጥሙት የነበሩ ችግሮች ናቸው ተብሏል። የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኩመራ ዋቅጅራ በኢትዮጵያ 30 ፓርኮች፣ ከ90 በላይ ጥብቅ ስፍራዎች ስለመኖራቸው ተናግረዋል። ከነዚህ ውስጥ የባሌ ብሔርራዊ ፓርክና ሰሜን
4 days ago1 min read
በኢትዮጵያ የንግዱን ማህበረሰብ እየገጠሙ ካሉ ችግሮች 40 በመቶ ያህሉ ከገንዘብ አቅርቦት ጋር የተገናኙ ናቸው ተባለ ።
መጋቢት 3/2018 በኢትዮጵያ የንግዱን ማህበረሰብ እየገጠሙ ካሉ ችግሮች 40 በመቶ ያህሉ ከገንዘብ አቅርቦት ጋር የተገናኙ ናቸው ተባለ ። በአጠቃላይ በኢትዮጵያ 2 ሚሊየን የሚጠጉ ጥቃቅን ፣ አነስተኛና መካከለኛ የንግድ ኢንዱስትሪ ተቋማት እንዳሉ ተነግሯል። የእነዚህ ኢንዱስትሪ ባለቤቶችና ኢ-መደበኛ በሆኑ ሌሎች ንግዶች የተሠማሩ ሰዎች በአጠቃላይ የብድር ፍላጎታቸው በአገሪቱ ባሉ ሁሉም ባንኮችና የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ተቆጥቦ ከሚገኘው ገንዘብ ግማሽ ያህሉን ይሆናል ተብሏል። በኢትዮጵያ ባሉ ባንኮችና የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ተቆጥቦ ያለ አጠቃላይ ገንዘብ 3.7 ትሪሊዮን ብር እንደሆነ የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት በካፒታል ሆቴል እያካሄደው ባለው ውይይት ላይ ሲነገር ሠምተናል። በውይይቱ ላይ የንግዱ ማህበረሰብ ስለሚገጥመው የመስ
4 days ago1 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

