top of page


በተመድ በአለም አቀፍ ደረጃ 2026 የአርብቶ አደር እና የግጦሽ መሬት ዓመት እንዲሆን በተወሰነው መሰረት አዲስ አበባ ላይ ጉባኤ መደረጉ ተሰማ
ጥር 19/2018 የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እና የአየር ጠባይ ለውጥንም ለመቋቋም ይረዳል ተብሎ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአለም አቀፍ ደረጃ 2026 የአርብቶ አደር እና የግጦሽ መሬት ዓመት እንዲሆን በተወሰነው መሰረት አዲስ አበባ ላይ ጉባኤ መደረጉ ተሰማ፡፡ ከግብርና ሚኒስቴር ፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሰላም እና ፀጥታ ኢንስቲትዩ ጋር በመተባበር የመንግስታቱ ድርጅት በወሰነው መሰረት በርዕሰ ጉዳዩ ዙሪያ ምሁራንና የአርብቶ አደሮች መወያየታቸው ተሰምቷል፡፡ በኢትዮጵያ ከ12 እስከ 15 በመቶ የሚደርሱ የማህበረሰብ አባላት አርብቶ አደር መሆናቸው የሚነገር ሲሆን ኢኮኖሚው ላይ ከፍተኛ ድርሻ አላቸውም ተብሏል፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ ከ300 ሚሊዮን በላይ አርብቶ አደሮች መኖራቸው የሚናገሩት የፓስቶራሊስት ፎረም ኢትዮጵያ ዳይሬክተር
8 hours ago1 min read


ጥር 19/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ፈረንሳይ ፈረንሳይ እድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ አዳጊዎችን የኢንተርኔት ማህበራዊ ትስስር ገጾች ተጠቃሚነትን ልታስቀር ነው፡፡ አዳጊዎችን እንደ ፌስ ቡክ እና ቲክ ቶክ ካሉ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ተጠቃሚነት የሚከለክል ረቂቅ ተሰናድቶ ለአገሩቱ ፓርላማ መቅረቡን ቢቢሲ ፅፏል፡፡ ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ሕጉ ከመጪው አዲስ የትምህርት ዘመን በፊት ስራ ላይ እንዲውል ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ ሕጉ አዳጊ ወጣቶችን ከተለያዩ ማህበራዊ ጠንቆች ለመጠበቅ ሁነኛ መፍትሄ እንደሚሆን ታምኖበታል ተብሏል፡፡ በብዙ አገሮችም አዳጊዎችን ከተለያዩ ማህበራዊ ትስስር ድረ ገጾች የማቅረቡ እርምጃ እያነጋገረ ነው ተብሏል፡፡ አውስትራሊያ እድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ አዳጊዎችን የማህበራዊ ትስስር ገፆች ተጠቃሚነት በመከልከል ቀዳሚዋ አገር እንደሆነች መረ
8 hours ago2 min read


ዘመን ባንክ አጠቃላይ ሀብቴ ከ100 ቢሊዮን ብር አለፈ አለ፡፡
ጥር 19/2018 ዘመን ባንክ አጠቃላይ ሀብቴ ከ100 ቢሊዮን ብር አለፈ አለ፡፡ የተከፈለ ካፒታሉም14 ቢሊዮን ብር መድረሱን በላከልን መግለጫ ላይ ጠቅሷል፡፡ ባንኩ በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የመጀመሪያ መንፈቅ አጠቃላይ ሀብት 106 ቢሊዮን ብር፣ ተቀማጭ ገንዘብ ደግሞ 80 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተናግሯል፡፡ ይህም ባንኩ የተረጋጋ ዕድገትና ጠንካራ የደንበኞች አመኔታ እንዳለው የሚያሳይ ነው ሲሉ የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደረጀ ዘበነ አስረድተዋል፡፡ ዘመን ባንክ በዚህ ጊዜ ውስጥ ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ ማስመዝገቡም ተጠቅሷል፡፡ ዋና ስራ አስፈጻሚው የባንኩ የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የመጀመሪያ መንፈቅ ስኬት ካለፈው ዓመት ከነበረው የሥራ አፈፃፀም ጋር ሲወዳደር የዘንድሮው የላቀና ስኬታማ የሥራ ጊዜ ያሳለፍንበት ነበር ሲሉ አስረድተዋል
9 hours ago1 min read


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሚሰጠው አገልግሎት ደንበኞቹ የእርካታ ደረጃ ከ80 ከመቶ መድረሱን ባካሄድኩት ጥናት አረጋግጫለሁ አለ፡፡
ጥር 19/2018 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሚሰጠው አገልግሎት ደንበኞቹ የእርካታ ደረጃ ከ80 ከመቶ መድረሱን ባካሄድኩት ጥናት አረጋግጫለሁ አለ፡፡ ባንኩ ይህን ያለው ዘሬ ማካሄድ በጀመረው የደንበኞች አገልግሎት ሳምንት የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንከ ከዚህ ቀደም በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ በጥቂቱም ቢሆን የታዩ ነበሩ ያላቸውን ከአሠራር ግልጽነት፣ ከአገልግሎት ጥራት መዋዠቅ፣ ከአገልግሎት መዘግየት፣ ከኔትወርክ መቆራረጥ፣ ከሲስተም ብልሽት፣ ከሥራ ክፍሎች ቅንጅት፡ ከሠራተኞች አመለካከት እና ከሥራ ባህል ጋር የተያያዙ ችግሮችን ለመፍታት ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረኩ ነው ብሏል፡፡ የደንበኞች አገልግሎት ሳምንት የሚከበረው በዋናነት ከደንበኞች ጋር በሚካሄዱ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና ግብረ መልስ መሰብሰቢያ ውይይቶች ሲሆን፣ እንደ
10 hours ago1 min read


በመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ በሰሜኑ ጦርነት ስጋት አድሮባቸው ስራ አቁመው የቆዩ ባለሃብቶች ዳግም ወደ ማምረት ለመመለስ ፍቃደኝነታቸውን እያሳዩ ነው ተባለ
ጥር 19/2018 በመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ የነበሩ እና በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ስጋት አድሮባቸው ስራ አቁመው የቆዩ ባለሃብቶች ዳግም ወደ ማምረት ለመመለስ ፍቃደኝነታቸውን እያሳዩ ነው ተባለ። መንግስትም መሰረተ ልማቶችን መልሶ ሊያሟላላቸው እና የተለያዩ ማበረታቻዎችን ሊሰጣቸው እንደተስማማ ሠምተናል። በአሁኑ ወቅት በኢነዱስሪ ፓርኩ እየሰራ ያለው አንድ ባለሃብት ብቻ ነው ተብሏል፡፡ ለሁለት ዓመት ያህል በቆየው የሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ስራ አቁሞ የቆየው የመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዳግም ወደ ማምረት እንዲመለስ ከአራት ወር በፊት ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እየሰራ እንደሚገኝ ተጠቅሷል። ግብረ ሃይሉ በፓርኩ ውስጥ ሲሰሩ የነበሩ እና በጦርነቱ ምክንያት ለቀው የሄዱ ባለሃብቶችን በኢንተርኔትና ሌሎች አማራጮች አግኝቶ ማነጋገሩን፤ የኢንዱስትሪ ፓርኮች
12 hours ago2 min read
ከኢትዮ ቴሌኮም እና መሰል አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ለአገልግሎት ከሚያስከትሉት እስከ 5 መቶ እንዲቆረጥ የሚያስገድድ ደንብ ወጥቷል
ጥር 19/2018 በተለያየ ምክንያት ለችግር የተጋለጡ ሰዎችን እርዳታ ከመጠበቅ ይልቅ ኢትዮጵያ በራሷ አቅም ምላሽ ለመስጠት ከኢትዮ ቴሌኮም እና መሰል አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ለአገልግሎት ከሚያስከትሉት እስከ 5 መቶ እንዲቆረጥ የሚያስገድድ ደንብ ወጥቷል፡፡ ደንቡ የቢዝነስ ሰዎች ንግድ ፈቃድ ሲያስወጡ እና ሲያድሱ ፓስፖርት ለማውጣትም አገልግሎት ሲጠይቁ በቁርጥ እስከ 200 ብር እንዲከፍሉ ያስገድዳል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ያሬድ እንዳሻው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://sh
12 hours ago1 min read


በፍትህ ሚኒስቴር የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ 1800 የሚሆኑ ሰዎችን በሕገ-ወጥ መንገድ አዘዋውሯል ባላቸው 28 ተከሳሾች ላይ ክስ መመስረቱን ተናገረ፡፡
ጥር 19/2018 በፍትህ ሚኒስቴር የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ 1800 የሚሆኑ ሰዎችን በሕገ-ወጥ መንገድ አዘዋውሯል ባላቸው 28 ተከሳሾች ላይ ክስ መመስረቱን ተናገረ፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በህገ ወጥ መንገድ ሲያዘዋውሯቸው ከነበሩት ሰዎች ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰባቸውን ዐቃቤ ህግ በክሱ ጠቅሷል፡፡ የዐቃቤ ሕግ ክስ እንደሚያስረዳው ክስ የመሰረተባቸው 28ቱ ግለሰቦች በሰው ልጅ ለመነገድ በማሰብ #የወንጀል_ቡድን በማደራጀት እንዲሁም የቡድኑ አመራር እና አባላት በመሆን በወንጀል ድርጊቱ ላይ ተሳተፈዋል በሚል የተጠረጠሩ ናቸው፡፡ በስራቸው ሌሎች አነስተኛ ስራ የሚሰሩ ደላሎችን በመመልመል ሰዎች በሊቢያ በኩል አድርገው ወደ አውሮፓ ከገቡ የተሻለ ኑሮ እንደሚኖሩ በማሳመን ወደ ባህርዳር እና ጎንደር ሲልኩ ቆይተዋል ብሏል፡፡ ተከሳሾቹ በባህር ዳር እና ጎንደር አካባ
12 hours ago2 min read


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ከምንግዜውም የላቀ የግማሽ ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ እያካሄደ ነው፡፡
ጥር 19/2018 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ከምንግዜውም የላቀ የግማሽ ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ እያካሄደ ነው፡፡ በዚህም ከ70 ቢሊዮን ብር በላይ ከባንኮች በመሰብሰብ የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ያለመ ሊሆን ይችላል ተብሏል፡፡ የብርን የመግዛት አቅም ባለበት ለማቆምና ለማጠናከርም ያለመ መሆኑን ከፍተኛ የተባለው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ጠቃሚ ነው ይላሉ የዘርረፉ ባለሙያዎች፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ትዕግስት ዘሪሁን የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsAp
12 hours ago1 min read
የኤሌክትሪክ ሀይል አጠራቅሞ በመያዝ የሀይል ማቋረጥ በሚያጋጥም ጊዜ የኤሌክትሪክ አገልግሎት መስጠት የሚችል አሰራር ሊጀመር ነው፡፡
ጥር 19/2018 የኤሌክትሪክ ሀይል አጠራቅሞ በመያዝ የሀይል ማቋረጥ በሚያጋጥም ጊዜ የኤሌክትሪክ አገልግሎት መስጠት የሚችል አሰራር ሊጀመር ነው፡፡ በአንድ የሃገር በቀል ተቋም እና በቻይና ኩባንያ መካከል በፈረመው ስምምነት መሰረት በታዳሽ ሀይል በሚሰራ ባትሪ ስራው ይከናወናል ተብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ምንታምር ፀጋው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx X :- https://x.c
13 hours ago1 min read








