top of page


የፌደራል ግብር ከፋዮች በኮቴ ክፍያ፣ ነጋዴዎች ደግሞ በግብር ሰብሳቢዎች ስነ ምግባር ጉድለት መማረራቸው በፓርላማው ተነገረ፡፡
ታህሳስ 3/2018 የፌደራል ግብር ከፋዮች በኮቴ ክፍያ፣ ነጋዴዎች ደግሞ በግብር ሰብሳቢዎች ስነ ምግባር ጉድለት መማረራቸው በፓርላማው ተነገረ፡፡ የገቢዎች ሚኒስቴር በበኩሉ የኬላ ጉዳይ ከፍተኛ አጀንዳ ሆኖ መቆየቱን፤ እስካሁን ግን መፈታት እንዳልተቻለ ተናግሯል፡፡ የኮቴ ክፍያና የገቢ ሰብሳቢ ሰራተኞች ስነ ምግባር ጉዳይ ለህዝብ ተወካዬዎች ምክር ቤት እና ሌሎች ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት ማቅረቡን የፕላን ፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተናግሮ፤ ለዚህም ማብራሪያ እንዲሰጠው የገቢዎች ሚኒስቴርን ጠይቋል፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ይህን የጠየቀው ዛሬ ታህሳስ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የገቢዎችን ሚኒስቴርን የ4 ወራት የስራ ክንውን ሪፖርትን ባደመጠበት ወቅት ነው፡፡ የሪፖርቱን ማብቃት ተከትሎ የቋሚ ኮሚቴውን ሪፖርት በንባብ ያቀረቡት የገቢ ዘ
2 days ago2 min read


ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የተከፈለ ካፒታሉ 5 ቢሊዮን ብር እንደደረሰ ተናገረ፡፡
ታህሳስ 3/2018 ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የተከፈለ ካፒታሉ 5 ቢሊዮን ብር እንደደረሰ ተናገረ፡፡ ይህም ትልቅ ስኬት ነው ብሏል፡፡ በ2016 በጀት ዓመት የባንኩ የተከፈለ ካፒታል 2.4 ቢሊዮን ብር እንደነበር ያስታወሰው ባንኩ በአንድ ዓመት ውስጥ የ102 በመቶ አድገት በማምጣት 5 በሊዮን ብር አንደደረሰ ተናግሯል፡፡ ባንኮች ካፒታላቸውን 5 ቢሊዮን ብር እንዲያደርሱ ብሔራዊ ባንክ ያስቀመጠውን መስፈርት ያስታወሰው ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከጊዜ ገደቡ በፊት ማሳካት መቻሉ በባስለክሲዮኖቹ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ዘንደ ያለውን ተቀባይነት ከጊዜ ወደ ጊዜ አያደገ መመጣቱን ያሳያል ብሏል፡፡ ይህ በመሳካቱ ባንኩ ከሎሎች ባንኮች ጋር መዋሃድ ሳይጠበቅበት እንዲቀጥል እንደሚያስችለው አና የመዋሃድም እቅድ አንደሌለው ተናግሯል፡፡ ይህ እንዲሳካም በተለይ ባለ
2 days ago1 min read
ታህሳስ 3/2018 የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ሃይል ፍጆታ ካለፈው ሃምሌ ወር ወዲህ እያደገ መጥቷል ተባለ።
ኢትዮጵያ ከተለያዩ ምንጮች ከምታመርተው የኤሌክትሪክ ሃይል 90 በመቶው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል እንደሆነ ተጠቅሷል። በዘንድሮው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አራት ወራት ኢትዮጵያ ከውሃ እና ከነፋስ ከ15,300 ጊጋዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨቷ ተነግሯል። በየወሩ በአማካይ 3,800 ጊጋዋት ሰአት የኤሌክትሪክ ሃይል አመንጭታለች እንደማለት ነው። ከመነጨው የኤሌክትሪክ ሃይል ከ90 በመቶ ያላነሰው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ እንደዋለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ነግረውናል። የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ሃይል ፍጆታ ከጊዜ ወደ እያደገ መጥቷል ያሉት ዳይሬክተሩ ከሃምሌ ህዳር የነበረው መረጃ ይህንኑ እንደሚያሳይ ጠቁመዋል። በሀገር ውስጥ ያሉ የኤሌክትሪክ ሃይል ተጠቃሚዎች በቤት ውስጥ ካሉ ደንበኞች እስከ ትላል
2 days ago1 min read


ኢትዮጵያ ከአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት 261 ሚሊዮን ዶላር ብድር ለማግኘት የሚያስችላትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሷ ተሰማ።
ታህሳስ 2/2018 ኢትዮጵያ ከአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት 261 ሚሊዮን ዶላር ብድር ለማግኘት የሚያስችላትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሷ ተሰማ። ይህ የብድር አቅርቦት ስምምነት #IMF ለኢትዮጵያ ለመስጠት ካሰበው የ4 ዓመት የ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር አቅርቦት አካል ነው። የIMF እና የኢትዮጵያ መንግስት ሀላፊዎች በአዲስ አበባ እና በበይነ መረብ ባደረጉት የአራተኛው ዙር የብድር አቅርቦት ውይይት ላይ ኢትዮጵያ 261 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት የሚያስችላት የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተጠቅሷል። ይህን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት የ IMF አስተዳደር እና የስራ አስፈጻሚ ቦርድ በመጪዎቹ ሳምንታት ያፀድቀዋል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተቋሙ ጠቅሷል። የIMF የ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር አቅርቦት የተቋሙ የስራ አስፈ
3 days ago1 min read


የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ እስከ ስምንት ብር ጭማሪ ተደረገ፡፡
ታህሳስ 1 2018 የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ እስከ 8 ብር ጭማሪ ተደረገ፡፡ ጭማሪው ከዛሬ 6:00 ጀምሮ ተግባረዊ የተደረገ መሆኑን የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስረድቷል፡፡ በጭማሪው መሰረት በቤንዚን ላይ የ7 ብር ገደማ ጭማሪ ሲደረግ በኬሮሲን ላይ ደግሞ የ8 ብር ገደማ ጭማሪ ተድርጓል፡፡ ቤንዚን፣ የኬሮሲን እና ነጭ ናፍጣ የሦስቱም የነዳጅ ምርቶች ዋጋ በአዲሱ ጭማሪ መሰረት 129.12 ብር እንዲሆኑ ተድርጓል። ከሰሞኑ በዲስ አበባ ሆነ በክልሎች የነዳጅ ማደያዎች ነዳጅ የለንም ብለው ረጃጅም የተሽከርካሪ ሰልፎች ታይተው ቆይተዋል፡፡ ለዚህም ከታሕሳስ ወር አንስቶ የቫት እና የኤክሳይስ ታክስ በአጠቃላይ የ30 በመቶ ግብር ይጣላል የሚል ምክንያት በብዙዎች ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ዛሬ ለነዳጅ አ
4 days ago1 min read


የኢትዮጵያ የሎጅስቲክስ ዘርፍ በ10 ዓመታት ውስጥ ለመቀየር ከ3 ትሪሊየን ብር በላይ ያስፈልጋል ተባለ፡፡
ታህሳስ 1 2018 ከአለም ሀገራት ሲነጻጸር ቀርፋፋ የተባለውን የኢትዮጵያ የሎጅስቲክስ ዘርፍ በ10 ዓመታት ውስጥ ለመቀየር ከሶስት ትሪሊየን ብር በላይ ያስፈልጋል ተባለ፡፡ ገንዘቡን መንግስት ከሚመድበው በተጨማሪ ከረጂ ድርጅቶች እና ከሌሎች ምንጮች ለማግኘት መታሰቡን ሰምተናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ቴዎድሮስ ወርቁ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw 🟦Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1 💬WhatsApp : https://whatsapp.com/
4 days ago1 min read


የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር የባቡር መሰረተ ልማት እና ደረቅ ወደብ ግንባታን ለብቻው ለመስራት መንገድ መጀመሩን ተናገረ
ታህሳስ 1 2018 ከዚህ ቀደም በውጪ ባለሞያዎች ብቻ ይገነቡ የነበሩ የባቡር መሰረተ ልማት እና ደረቅ ወደብ ግንባታን የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ለብቻው ለመስራት መንገድ መጀመሩን ተናገረ፡፡ ለዚህም ማሳያ የሚሆን በሃገር ልጆች እውቀት እና ጉልበት የባቡር ሀዲድ ንጣፍ ስራ መጀመሩን ሰምተናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ተህቦ ንጉሴ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw 🟦Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1 💬WhatsApp :...
4 days ago1 min read


በመጪው ግንቦት መጨረሻ ስለሚካሄደው ምርጫ ዝግጅት ውይይቶችን ማድረግ ያስፈልጋል ብሏል
ታህሳስ 1 2018 የፖለቲካ ፓርቲዎች ለእጩ ተመራጮቻቸው የድጋፍ ፊርማ እንዲያቀርቡ የሚያስገድደው የህግ አንቀጽ መሻሩ እና ለእጩ ምዝገባ የጊዜ ገደቡ መራዘሙ ለሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ጥርጊያውን ያቀናል ተባለ፡፡ ይሄንን ያለው የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ነው፡፡ በመጪው ግንቦት መጨረሻ ስለሚካሄደው ምርጫ ዝግጅት ግን ውይይቶችን ማድረግ ያስፈልጋል ብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ያሬድ እንዳሻው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw 🟦Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡...
4 days ago1 min read


ግለሰቦች ዲጂታል መታወቂያቸውን ትክክለኛነቱ እና ደህንነቱ በተረጋገጠ መልኩ መጠቀም እንዲችሉ የሚያግዝ አገልግሎት ይፋ ተደረገ።
ህዳር 30 2018 ግለሰቦች ዲጂታል መታወቂያቸውን ትክክለኛነቱ እና ደህንነቱ በተረጋገጠ መልኩ መጠቀም እንዲችሉ የሚያግዝ አገልግሎት ይፋ ተደረገ። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ የደህንነት የዲጅታል ሰርተፍኬት አገልግሎት ስርዓት ተበጅቶለታል፡፡ በዚህም አገልግሎት በፋይዳ ፕሮግራም ስር ለዜጎች የሚሰጠው እያንዳንዱ ዲጂታል መታወቂያ ትክክለኛነት፣ ሊረጋገጥ የሚችል፤ እና ህጋዊ ተቀባይነት ያለው እንዲሆን ያስችላል ተብሏል። ይፋ የተደረገው ዲጂታል ሰርተፍኬት አገልግሎት የሰዎችን የግል መረጃ የመመዝበር እና በሀሰተኛ ስም የሚወጡ መታወቂያዎችን ለመቆጣጠር፣ አመሳስሎ የመስራት የማጭበርበር እና የማንነት መረጃን አላግባብ መጠቀምን ለመከላከልም ይረዳል ተብሎለታል። የፋይዳ መታወቂያን የጀርባ ክፍል ኪው
5 days ago1 min read


ከተሞች ሲለሙ ያለፉበትን የረዥም ታሪክ አሻራ የሚያሳዩ የኪነ ህንፃና መሰል ቅርሶች እንዳይጠፉ ጥናትን እና ወይይትን መሰረት ያደረጉ እንዲሆኑ ተጠይቋል፡፡
ህዳር 30 2018 ከተሞች ሲለሙ ያለፉበትን የረዥም ታሪክ አሻራ የሚያሳዩ የኪነ ህንፃና መሰል ቅርሶች እንዳይጠፉ ጥናትን እና ወይይትን መሰረት ያደረጉ እንዲሆኑ ተጠይቋል፡፡ ጥያቄው የቀረበው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ75ኛ ዓመቱን ምክንያት በማድረግ ልደታ በሚገኘው የቴክኖሎሎጂ እና ቢልት ኢንቫይሮመንት ኮሌጅ ‹‹በቅርስ ጥበቃ እና ጥናት ላይ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች›› በሚል መሪ ቃል ባሰናደው የውይይት መድረክ ላይ ነው፡፡ በቅርስ ጥበቃ እና ጥናት ላይ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች በሚል ርዕስ ጽሁፍ ያቀረቡት አርክቴክት ፋሲል ጊዮርጊስ ስለቅርስ ያለው አረዳድ ዝቅተኛ መሆን፣ የበቂ በለሞያ እጥረት እና መሰል ችግሮች ለዘርፉ እንቅፋት መሆናቸውን ዘርዝረዋል፡፡ የወይይቱ ተሳታፊዎች እና ባለሙያዎች ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ ሀገራት ፖለቲካ ለ
6 days ago1 min read


ጉዳያችን - የከተማ ልማትና የመልሶ ግንባታ
ህዳር 29 2018 ጉዳያችን - የከተማ ልማትና የመልሶ ግንባታ የከተማ ልማትና የመልሶ ግንባታ ስራ ውስጥ መታሰብ ያለባቸው ጉዳዮች ምንድን ናቸው? በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ፕላን መምህር እና ተመራማሪ የሆኑት ውብሸት ብርሃኑ(ዶ/ር) በጉዳዩ ላይ የሰጡንን ማብራሪያ ለማድመጥ… ቴዎድሮስ ወርቁ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw 🟦Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1 💬WhatsApp : https://whatsapp.com/chan
6 days ago1 min read


ሕብረት ባንክ በ2017 በጀት ዓመት ከግብር በፊት የ749.04 ሚሊዮን ብር ማትረፉን ተናገረ፡፡
ህዳር 29 2018 ሕብረት ባንክ በ2017 በጀት ዓመት ከግብር በፊት የ749.04 ሚሊዮን ብር ማትረፉን ተናገረ፡፡ ባንኩ ይህን ያለው 28ኛውን የባለአክሲዮኖች መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በዛሬው እለት ባካሄደበት ወቅት ነው፡፡ በጉባዔው ላይ የባንኩን ዓመታዊ ሪፖርት ያቀረቡት የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ መስፍን ተሰማ የባንኩ ሀብት 113.93 ቢሊየን ብር መድረሱን ተናግረዋል፡፡ ይህም ከቀዳሚው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ17.96 በመቶ ወይም የ17.35 ቢሊዮን ብር ጭማሪ አሳይቷል ብለዋል። የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑን 92.68 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተጠቅሷል። ይህም ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ18.03 ቢሊዮን ብር ወይም የ24.16 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን የቦርድ ሰብሳቢው አስረድተዋል፡፡ ከወለድ ነፃ ፋይናንስን ጨምሮ አጠቃላይ የባ
6 days ago1 min read


ኢትዮጵያ በ10 ዓመት፤ ከተቻለም ከዚያ ባጠረ ጊዜ ውስጥ የኒውክሊየር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ትገነባለች ተባለ።
ህዳር 29 2018 ኢትዮጵያ በ10 ዓመት፤ ከተቻለም ከዚያ ባጠረ ጊዜ ውስጥ የኒውክሊየር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ትገነባለች ተባለ። ዛሬ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት ዝግጅት፣የኒውክሊየር የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱ መጀመር ይፋ ተደርጓል። በቅርቡ የተቋቋመው የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽንም ስራዬን መጀመሬን እወቁት ብሏል። የኒውክሊየር የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱን ለመገንባት ዓለም አቀፉ የአቶሚክ ሀይል ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ (አይ.ኤ.ኢ.ኤ) የሚያስቀምጣቸውን 19 መሠረታዊ የሆኑ መስፈርቶችን ማሟላት ይጠበቃል ተብሏል። ኢትዮጵያም ይህንኑ መስፈርት አሟልታ በተቆጣጣሪ ኤጀንሲው እገዛና ክትትል ለመስራት ዝግጁ ነች ተብሏል። የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ አብዱረዛቅ ዑመር ሲናገሩ እንደሰማነው የስራው ሂደት ሶስት ምዕራፎች ይ
6 days ago1 min read


''ኢትዮጵያን የትኛውም ትንኮሣ ከጀመረችው የብልፅግና ጉዞ አያስቆማትም'' ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ።
ህዳር 29 2018 ''ኢትዮጵያን የትኛውም ትንኮሣ ከጀመረችው የብልፅግና ጉዞ አያስቆማትም'' ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ። የሚገጥመንን እያንዳንዱን ፈተና ወደ ዕድል በመቀየር የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን እናደርጋለንም ብለዋል። 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄር ፤ ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት በሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ነው፡፡ በአከባበሩ ላይ የፌዴራል እና የክልል መንግስታት ከፍተኛ ባለስልጣናት የተገኙ ሲሆን መልዕክቶችም ተላልፈዋል። የዕለቱ የክብር እንግዳ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ባደረጉት ንግግር በዓሉ ሁሉም ኢትዮጵያውያን የሚደምቁበት ነው ብለዋል። ኢትዮጵያውያን መተባበርን እና በአንድነት መቆምን የጋራ ሃብታችን እናድርግ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ በተለያዩ መስኮች የሚደነቁ ውጤቶችን
6 days ago1 min read


ራሚስ ባንክ ጠቅላላ ሀብቱ ከ4.2 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን ተናገረ።
ህዳር 29 2018 ራሚስ ባንክ ጠቅላላ ሀብቱ ከ4.2 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን ተናገረ። ይህም በአንድ ዓመት ውስጥ የ85 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል ሲል ባንኩ ትናንት ባካሄደው ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ባወጣው ሪፖርት ተናግሯል። ራሚስ ባንክ በበጀት ዓመቱ ከ400 ሚሊየን ብር በላይ ጠቅላላ ገቢ በማስመዝገብ ወደ ትርፍ ተሸጋግሬያለሁም ብሏል። ገቢው በዓመቱ ውስጥ የ3,726 ከመቶ እድገት አሳይቷል ተብሏል። ራሚስ ባንክ በ2017 በጀት ዓመት ከ20 ሚሊዮን ዶላር በላይ መሰብሰቡንም ጠቅሷል። የቅርንጫፎቹን ብዛት 47፣ የደንበኞቹ ብዛት ደግሞ 352,000 መድረሳቸው በሪፖርቱ ላይ ሰፍሯል። ባንኩ በበጀት ዓመቱ ማገባደጃ ላይ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያንና የካርድ ባንኪንግ አገልግሎቶቹን ለደንበኞቹ ማስተዋወቁን እና የላቁ የዲጅታል ባንክ አማራጮችን እንደ ኢንተር
7 days ago1 min read


የነዳጅ ዋጋ ይጨምራል በሚል ምክንያት ከሲዳማ ክልል ሃገረ ሰላም እስከ ዝዋይ ባቱ ድረስ ባለው መንገድ በርከት ያሉ ማደያዎች ቢኖሩም አንዳቸውም ናፍጣ የላቸውም።
ህዳር 29 2018 የነዳጅ ዋጋ ይጨምራል በሚል ምክንያት ከሲዳማ ክልል ሃገረ ሰላም እስከ ዝዋይ ባቱ ድረስ ባለው መንገድ በርከት ያሉ ማደያዎች ቢኖሩም አንዳቸውም ናፍጣ የላቸውም። በጄሪካን ግን ይሸጣል። በሲዳማ ክልል ሀገረ ሰላም እስከ ሀዋሳ ከተማ መግቢያ ድረስ፣ ከሃዋሳ እስከ ዝዋይ ባቱ ባሉ ማደያዎች የመኪና ናፍጣ ማግኘት አስቸጋሪ መሆኑን ከቦታው ተመልክተናል። በእዚህ አካባቢ ስንዘዋወር እንደተመለከትነው ማደያዎች ውስጥ ነዳጅ የለም ቢባልም ማደያው አካባቢና ማደያዎች ውስጥ ያሉ አንዳንድ ግለሰቦች በጀሪካን ነዳጅ እንደሚሸጥ ሲናገሩና ሂሳብ ለማስማማት ሲሞክሩም አይተናል። በሲዳማ ክልል ሀገረ ሰላም ላይ ህዳር 27 ቀን 2018 በነበርንበት ወቅት ማደያዎች ውስጥ ናፍጣ የለም የሚል ተደጋጋሚ ምላሾች ቢሰጡንም እዚያው አካባቢ ያሉ ግለሰቦች ግን ናፍጣ በጀ
7 days ago1 min read


በኢትዮጵያ በጨርቃ ጨርቅ እና አልባሳት ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች፤ የሚደርስባቸው የመብት ጥሰት ቀጥሏል ተብሏል፡፡
ህዳር 26 2018 በኢትዮጵያ በጨርቃ ጨርቅ እና አልባሳት ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች፤ የሚደርስባቸው የመብት ጥሰት ቀጥሏል ተብሏል፡፡ ይህ የተባለው ፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ (Forum For Social Studies) የተሰኘ ተቋም በጨርቃ ጨርቅ እና አልባሳት ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞችን በተመለከተ እየሰራው ላለው ፕሮጀክት ከሚመለከታቸው አካላት ግብዓት ለመሰብሰብ ባዘጋጀው መድረክ ላይ ነው፡፡ የፕሮጅክቱ ከዋኝ ብድን አባል የሆኑት ደግነት አበባው(ዶ/ር) በጨርቃ ጨርቅ እና አልባሳት ኢንዱስትሪዎች ተቀጥረው የሚሰሩ ሰራተኞች የበዙ ችግሮች እየገጠሟቸው እንደሆነ አንስተዋል፡፡ ከሀገሪቱ የዋጋ ንረት ጋር የማይጣጣም ክፍያ፣ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል ያለመወሰን፣ እንዳይደራጁ መከልከል፣ ምቹ ያልሆነ የስራ ቦታን ጨምሮ ሌሎች ተደራራቢ ችግሮች
Dec 52 min read


''በሩብ ዓመቱ 3,319 የመድሀኒት እና የክትባት የጎንዮሽ ጉዳት ሪፖርቶች ደርሰውኛል'' የምግብና መድሀኒት ባለስልጣን
ህዳር 26 2018 በሩብ ዓመቱ 3,319 የመድሀኒት እና የክትባት የጎንዮሽ ጉዳት ሪፖርቶች ደርሰውኛል ሲል የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ተናገረ፡፡ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በ2018 ሩብ ዓመት፣ 723 የመድኃኒት የጎንዮሽ ጉዳት ሪፖርቶችን(ADE) እንዲሁም 2,596 የክትባት የጎንዮሽ ጉዳት ሪፖርቶችን (AEFI) በድምሩ 3,319 ሪፖርቶች እንደሰበሰበ ተናግሯል፡፡ በተጨማሪም 15 አስከፊ የመድኃኒት ወይም የክትባት የጎንዮሽ ክስተት ሪፖርቶችን የማጣራት ስራ ሰርቻለሁም ብሏል፡፡ 257 አዳዲስ የህክምና መሳሪያዎች ሰነድ በመገምገም የገበያ ፈቃድ እንደሰጠም ተናግሯል፡፡ ለ13 ህክምና መሳሪያ አስመጪና አከፋፋይ ደግሞ የቅድመ ፈቃድ ኢንስፔክሽን አድርጎ የብቃት ማረጋገጫ እንደተሰጠም አስረድቷል፡፡ የህክም ሙከራ እንድካሄድ የተፈቀደላቸዉን ተቋማት ላ
Dec 51 min read


ትክክል ያልሆኑ መረጃዎችን የሚያሰራጩ ማህበራዊ መገናኛ ብዙሃንን እንዴት በህግ ተጠያቂ ማድረግ ይቻላል?
ህዳር 26 2018 ማህበራዊ የመገናኛ ብዙሃን በብዙ ሰዎች እንደ አማራጭ የመረጃ ምንጭ ይታያሉ። ሁሉም ላይ ባይሆንም ታዲያ በእነዚህ የማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን ላይ ቅሬታዎች ይሰማሉ። መደበኛ መገናኛ ብዙሃን በብዙ ጥረት ያዘጋጁትን መረጃ የራሳቸው አድርገው ያቀርባሉ፣ ጫፍ ብቻ ይዘው ትክክል ያልሆኑ መረጃዎችንም ያሰራጫሉ በሚል ይወቀሳሉ። ለመሆኑ በዚህ አይነቱ ተግባር የሚሳተፉ ማህበራዊ መገናኛ ብዙሃንን እንዴት በህግ ተጠያቂ ማድረግ ይቻላል? ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… ማርታ በቀለ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡...
Dec 51 min read


ሕብረት ኢንሹራንስ በ2017 በጀት ዓመት በታሪኬ ለመጀመሪያ ጊዜ በቢሊዮን የሚቆጠር ትርፍ አገኘሁ አለ።
ህዳር 26 2018 ሕብረት ኢንሹራንስ በ2017 በጀት ዓመት በታሪኬ ለመጀመሪያ ጊዜ በቢሊዮን የሚቆጠር ትርፍ አገኘሁ አለ። በአንድ አክሲዮን የተመዘገበው ትርፍ 68.55 በመቶ መሆኑን ኩባንያው ዛሬ ባካሄደው ዓመታዊ የባለ አክሲዮኖች ጉባኤ ላይ ያቀረበው ሪፖርት ተናግሯል። ሕብረት ኢንሹራንስ በ2017 በጀት ዓመት ከግብር በፊት 1 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማግኘቱን የተናገረ ሲሆን ይህም ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ79 በመቶ ጭማሬ አሳይቷል ብሏል። ኩባንያው ከግብር በኋላ ያገኘው የተጣራ ትርፍ 843 ሚሊዮን ብር ሲሆን ይህም ከቀዳሚው አመት ጋር ሲነፃፀር በተመሳሳይ የ79 በመቶ እድገት ማሳየቱን ከሪፖርቱ ተመልክተናል። በአንድ አክሲዮን የተመዘገበው ትርፍ (Earnings Per Share) አምና ከነበረው በ47.78 ከመቶ ወደ 68.55 ከመቶ ከፍ ያ
Dec 52 min read


ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባካሄደው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ የብር የመግዛት አቅም ከዶላር አንፃር በ6 ብር ተዳክሟል፡፡
ህዳር 25 2018 ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባካሄደው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ የብር የመግዛት አቅም ከዶላር አንፃር በ6 ብር ተዳክሟል፡፡ ከጊዜ ወደ ጊዜ መጠናከር እንዳለበት የሚጠበቀው የብር የመግዛት አቅምን እየተዳከመ ቀጥሏል፡፡ ይህም የሰዎችን የመግዛት አቅም የሚፈትን፤ በተለይ ከውጭ የሚመጡ ቁሶችን ዋጋ ደግሞ እጅጉ የሚያስወድድ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ ከወጭ ንግድ እና ከተለያዩ የውጭ ምንዛሬ ማግኛ ምንጮች እየተገኘ ያለው ዶላር ከአምናው ጋር ሲነፃፀር ከፍ ያለ መሆኑ እና በመሰል ምክንያቶች የውጭ ምንዛሬ ገበያው በራሱ መረጋጋት ይጠበቅበት ነበር ያሉት የፕራግማ ካፒታል መስራችና የፋይናንስና ኢንቨስትመንት ባለሙያው መርዕድ ፍቅረዮሐንስ ናቸው፡፡ ይሁንና በብልሹ አሰራር ፣ በባንኮች ግልፅ ያልሆነ የውጭ ምንዛሬ ግብይትና በተለያዩ ች
Dec 41 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page








