top of page


የካንሰር ህሙማን ለህክምና ወደ ውጪ ሀገራት የሚያደርጉትን ጉዞ እና ወጪ ያስቀራል የተባለለት ግዙፍ ሆስፒታል ሊገነባ መሆኑ ተሰማ፡፡
መጋቢት 18/2018 በተለይ የካንሰር ህሙማን ለህክምና ወደ ውጪ ሀገራት የሚያደርጉትን ጉዞ እና ወጪ ያስቀራል የተባለለት ግዙፍ ሆስፒታል ሊገነባ መሆኑ ተሰማ፡፡ ሆስፒታሉን ገንብቶ ለማጠናቀቅ ከ15 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚጠይቅም ተነግሯል። ሆስፒታሉን የሚያስገነባው ማቴዎስ ወንዱ ፋውንዴሽን የተሰኘው በጎ አድራጎት ድርጅት ሲሆን ግንባታውም በመንግስት ተቋማት፣ በበጎ አድራጎት ድርጅቶችና በህዝብ መዋጮ ጭምር በድጋፍ የሚከወን እንደሆነም ሰምተናል። ሆስፒታሉ በተለይ የካንሰር ህመም ላይ ዋነኛው ትኩረቱ አድርጎ የሚሰራ ቢሆንም ለተለያዩ ተላላፊ ላልሆኑ እና ተላላፊ ለሆኑ ህመም ጭምር አገልግሎት እንደሚሰጥ የማቴዎስ ወንዱ ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወንዱ በቀለ ነግረውናል። የማቴዎስ ወንዱ ፋውንዴሽን የቦርድ ሊቀመንበር የትናየት አበበ(ዶ/ር) በተለይ
Mar 271 min read


የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ለማሳደግ የተሰራው ስራ ውጤት እያመጣ ነው ሲል የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተናገረ።
መጋቢት 18/2018 የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ለማሳደግ የተሰራው ስራ ውጤት እያመጣ ነው ሲል የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተናገረ። ሚኒስቴሩ እንዳለው የፋብሪካዎቹ አማካይ የማምረት አቅም አሁን ላይ 66.3 በመቶ ደርሷል። ከ8ዓመት በፊት አማካይ የማምረት አቅማቸው 46 በመቶ እንደነበር የሚኒስቴሩ የመንግስት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ አበባ ታመነ ተናግረዋል። ከመሠረተ ልማት እና ጥሬ ዕቃ አቅርቦት እንዲሁም ከመንግስታዊ አገልግሎቶች ጋር የተያያዙ ችግሮች እንዲፈቱላቸው የተደረገው ጥረት የፋብሪካዎቹ የማምረት አቅም እንዲሻሻል ረድቷል ብለዋል። የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ጋር በመተባበር የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎችን የስራ ሃደት ከትናንት ጀምሮ የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ባለሞያዎች ተዘዋውረው እንዲመለከቱ
Mar 271 min read


በሶማሌ ክልል የአቦ ሸማኔ ንግድ የተጧጧፈ ሆኗል ተባለ።
መጋቢት 17/2018 በሶማሌ ክልል የአቦ ሸማኔ ንግድ የተጧጧፈ ሆኗል ተባለ። አቦሸማኔዎች በህገ-ወጥ የዱር እንስሳት አዘዋዋሪዎች ምክንያት የከፋ አደጋ እየደረሰባቸው ነው ተብሏል። በተለይም ግልገሎቹ እንደ ተወለዱ ከእናታቸው ተነጥለውለው ለንግድ ተግባራት እንደሚውሉ ተነግሯል። ይህ ህገ ወጥ ድርጊት በዋናነት የሚፈጸመው በአካባቢው በሚገኙ አርብቶ አደሮች አማካኝነት እንደሆነም የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን ተናግሯል። እነዚህ ግልገሎች ገና በጨቅላነታቸው ታድነው ተይዘው ፣ ህገ-ወጥ አዘዋዋሪዎች በ70 እና በ80 የአሜሪካ ዶላር ዋጋ ከአርብቶ አደሮቹ እንደሚረከቧቸው በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ህግ ማስከበር ዴስክ ሀላፊ አቶ ዳንኤል አሰፋ ነግረውናል። ህገ ወጥ የአቦሸማኔ ዝውውሩን እያጧጧፉት ያሉት በዋናነት ተጠቃሚ ሀገራት እንደሆነ የጠቀ
Mar 261 min read


የእስራኤል ጦር ከኢራን ባህር ሀይል ከፍተኛ አዛዦች መካከል አንዱ የነበሩት አል ሬዛ ታንጂ ሲሪን ገደልኩት አለ፡፡
መጋቢት 17/2018 የእስራኤል ጦር ከኢራን ባህር ሀይል ከፍተኛ አዛዦች መካከል አንዱ የነበሩት አል ሬዛ ታንጂ ሲሪን ገደልኩት አለ፡፡ ታንጂ ሲሪ የተገደሉት ኢራን በከፊል ዝግ አድርገው በሰነበተችው የሆርሙዝ ሰርጥ ቅኝት ያደርጉ በነበረበት ወቅት እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡ ታንጂሲሪ ለሆርሙዝ ሰርጥ መዘጋት ከፍተኛ ድርሻ ከነበራቸው የኢራን የጦር መሪዎች መካከል አንዱ እንደነበሩ የእስራኤሉ የመከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ ተናግረዋል፡፡ ወደ ወር በተቃረበው ጦርነት በአሜሪካ እና እስራኤል ጥምር ድብደባ በርካታ የኢራን ሲቪል እና የጦር መሪዎች መገደላቸው ይነገራል፡፡ ታንጂ ሲሪ በእስራኤል የአየር ጥቃት ተገድለዋል ስለመባሉ ለጊዜው ከኢራን በኩል የተሰማ አስተያየት የለም ተብሏል፡፡ ያም ሆኖ ኢራንን በአሜሪካ እና በእስራኤል ለሚፈፀምባት ድብደባ ምላሽ ከመ
Mar 261 min read


በአዲስ አበባ መንገዶች ከተሰሩበት አላማ ውጪ እየዋሉ መሆኑን የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ተናገረ፡፡
መጋቢት 17/2018 በአዲስ አበባ መንገዶች ከተሰሩበት አላማ ውጪ እየዋሉ መሆኑን የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ተናገረ፡፡ ባለስልጣኑ እንዳለው በኮሪደር ልማቱ ስራ የመኪና ማቆሚያዎች በተለያዩ ስፍራዎች ተገንብተዋል ያለ ሲሆን በከተማው መውጪያ እና መግቢያ አካባቢ ትላልቅ መኪኖች እቃ ጭነው ለረጅም ሰዓት ሲቆሙ እየተመለከትሁኝ ነው ብሏል፡፡ የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ እያሱ ሰለሞን ባለፉት 8 ወራት ውስጥ 111 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ ጥገና መከናወኑን ነግረውናል፡፡ ክረምት እየመጣ መሆኑን ተከትሎ የጎርፍ ስጋ ባለባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ድልድዮች፣ የፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦዎች ጥገና እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ አዲስ አበባ ወስጥ መንገዶች በየጊዜው ነው እድሳት የሚደረግላቸው ምክንያቱ ደግሞ ህብረተሰቡ የኔነት ስሜት ኖሮት መ
Mar 261 min read


በአንድ ይዞታ ላይ ሁለት እና ሶስት ካርታ ወይም የይዞታ ማረጋገጫ ለምን ሊወጣ ይችላል?
መጋቢት 17/2018 በአዲስ አበባ ከመሬትና መሬት ነክ ጉዳዮች ጋር በተገናኘ ዛሬም አሁንም ከፍተኛ ቅሬታና የአፈፃፀም ችግር እንዳለ ይሰማል። ከተማ አስተዳደሩ በተለያየ ዙር በሊዝ የጨረታ ቦታዎችን እያወዳደረ ለባለሀብቶች እያስተላለፈ ነው። የተወሰኑ የልማት ተነሺዎችም ሆኑ በጨረታ ከከተማ አስተዳደሩ አሸንፈው የወሰዱ ፤ ቦታ ለማግኘት ከማእከል ከጨረሱ በኋላ የተሰጣቸውን ቦታ ለመቀበል እንደተቸገሩ ሰምተናል። የዚህ ዋነኛ ችግር ደግሞ በተለይ የአርሶ አደር ቦታ ነው ፤ ካሳ አልተሰጠንም አልተወሰደም እና ሌሎች ምክንያቶችም ለከተማ አስተዳደሩ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ራስ ምታት እንደሆነበት ሰምተናል። ለመሆኑ የፕላን ተቃርኖ ያለበት ወይም ለአረንጓዴ ስፍራ ቦታ የተያዘ ቦታ የሆነ አገልግሎት ግንባታ የተፈጸመበት ቦታስ ሊስተካከልና አገልግሎቱ ሊስማማ የ
Mar 261 min read


ጋዜጠኞች ያላግባብ መታፈንና እስርን የመሰለ የሰብአዊ መብት ጥሰት ሲደርስባቸውም በፍርድ ቤት ጭምር ክርክር የሚያደርግ ድርጅት ስራ ጀምሯል፡፡
መጋቢት 17/2018 ጋዜጠኞች ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲሰሩ ፣ የሚድያ ምህዳሩ እንዲሰፋ ፣ ጋዜጠኞች ያላግባብ መታፈንና እስርን የመሰለ የሰብአዊ መብት ጥሰት ሲደርስባቸውም በፍርድ ቤት ጭምር ክርክር የሚያደርግ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በይፋ ስራ ጀምሯል፡፡ በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ተመዝግቦ በይፋ ትናንት ስራ ጀምሯል የተባለው ሎውየርስ ፎረ ሚዲያ (Lawyers for media) የተሰኘ ስያሜ የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ በዩኔስኮ እገዛ በፕሮጀክት ደረጃ የጀመርናቸው ስራዎች ራሱን ችሎ በተቋም ደረጃ በስፋት እየሰራ ይቀጥላል ያሉን የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች ህብረት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ መሱድ ገበየሁ ናቸው፡፡ በሁሉም ክልሎች የሚሰሩ የህግ ባለሙያዎች የተካተቱበት ለሚድያው ዘርፍ መጠናከርና የሚያስፈልገው የህግ ድጋፍ የሚሰጥ
Mar 261 min read


መጋቢት 17/2018 - የኔዘርላንድ ኢንስቲትዩት ፎር መልቲ ፓርቲ በመጪው ምርጫ የሚሳተፉ 80 ሴት እጩዎችን በመያዝ ውይይት ማድረጉ ተሰማ፡፡
መጋቢት 17/2018 የተለያዩ ሀሳቦችን በመያዝ በፖለቲካ ውስጥ የሚሳተፉ ሰዎች ከእርስ በእርስ ጥላቻ እና ካልተገባ መጠላለፍ ወጥተው በጋራ እንዲነጋገሩ እና በሀሳብ የበላይነት እንዲያምኑ እየሰራሁ ነው ያለው የኔዘርላንድ ኢንስቲትዩት ፎር መልቲ ፓርቲ በመጪው ምርጫ የሚሳተፉ 80 ሴት እጩዎችን በመያዝ ውይይት ማድረጉ ተሰማ፡፡ የኢትዮጵያ ባለዕራይ መሪዎች ማህበር ስራ አስፈፃሚ አካል ወ/ሪት ትዕግስት ወርቅነህ ፍፁም የተለያዩ አመለካከቶች እና የፓርቲ አቋም የያዙ ሰዎች በጋራ ሆነው ንግግር እንዲያደርጉ አካዳሚው እየሰራ ነው ሲሉ ለሸገር ነግረዋል፡፡ በተለያዩ ወቅቶች በዴሞክራሲ አካዳሚው ስልጠና መሰጠቱን የተናገሩት ወ/ት ትዕግስት ወጣት ሴቶች ለስልጠና የሚመጡት በአብዛኛው ከፖለቲካ ፓርቲ በመወከል ነው ይላሉ፡፡ አክቲቪስቶችም በስልጠናው ተሳትፈዋል ተብሏል
Mar 261 min read


ቴክኖሎጂውን ተገን አድርገው ‘'የዲጂታል ዘመን ቀማኞች’ ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነው።
መጋቢት 16/2018 ያለንበት የዲጂታሉ ዓለም የሰውን ልፋት በመጋራት ትልቅ እፎይታን አስገኝቷል፡፡ ድካምን መቀነሱ፣ ኑሮን ማቅለሉ፣ የራቀ የመሰለውን አቅርቦ ፣ ሁሉንም በቀላሉ መረጃን በእጁ መዳፍ፣ ግብይትን በጣቶቻቹ ንክኪ እንዲሆን እድልን ፈጥሯል። ነገር ግን ቴክኖሎጂውን ተገን አድርገው ‘የዲጂታል ዘመን ቀማኞች’ ቁጥርም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነው። በዚህ በዲጅታል አለሙ የማታለያ ዘርፉ ብዙ ነዉ፡፡ በየጊዜው አዳዲስ የማጭበርበሪ መላዎች ይሰማሉ። አታላዮች የሚዘረጉት መረብ እንደየሰው ማንነት ይለያያል። ለወጣቱ ያልሰራህበት ትርፍ፣ ለአዛውንቱ የልጅነት ፍቅርና ርህራሄ፣ ለተቸገረው ፈጣን ብድር ሌላም ሌላም ብዙ ነገሮች አማራጭ ሆነዉ ይቀርባሉ፡፡ በዚህ መንገድ አሁን አሁን ላይ ተጭበረበርኩ፣ ይህን ገንዘብ ተወሰደብኝ፣ ለአመታት ኳ
Mar 252 min read


የኢትዮጵያዊያን የቆየ የጋራ አብሮነት እሴቶች እንደ ቡና መጠራራት፣ እድርና ማህበር ያሉ ማህበራዊ ትስስሮች ወንጀልን በመከላከል ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸው ተባለ።
መጋቢት 16/2018 የኢትዮጵያዊያን የቆየ የጋራ አብሮነት እሴቶች እንደ ቡና መጠራራት፣ እድርና ማህበር ያሉ ማህበራዊ ትስስሮች ወንጀልን በመከላከል ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸው ተባለ። እነዚህ ማህበራዊ ቅርርቦሾች በሚላሉበት ወቅት ደግሞ ወንጀል በተደጋጋሚ የመከሰት ዕድሉ ሰፊ እንደሚሆን ተጠቁሟል። በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የስነ-ወንጀል የስነ ልቦና መምህሩ ዋና ኢንስፔክተር ጉግሳ ገብረግዚአብሔር አንድ ማህበረሰብ ጠንካራ የጋራ እሴቶች ሲኖሩት ወንጀልን የመቆጣጠር አቅሙ ይጨምራል ብለዋል። በአንድ አካባቢ የሚኖር ማህበረሰብ ወንጀል እንዳይፈጠር፣ ስርቆት እንዳይኖር፣ ግድያን እንዳይከሰት፣ ከማህበረሰቡ እሳቤ ያፈነገጠ ባህሪም እንዳይኖር የሚቆጣጠርበት ስልት ማህበራዊ ቅርርቦሹን ማጠናከር ነው የሚሉት ወ/ኢ/ር ጉግሳ ቡና ተጠራርቶ በ
Mar 251 min read


መጋቢት 16/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ኢራን ለኢራን ጠቅላይ የደህንነት ምክር ቤት አዲስ የበላይ ተሰየሙ፡፡ የምክር ቤቱ የበላይ ሆነው የተሰየሙት ሞሐመድ ባጌር ዘልግ ሐድር እንደሆኑ ሚድል ኢስት ሞኒተር ፅፏል፡፡ የቀድሞው የምክር ቤቱ የበላይ ዓሊ ላርጃኒ ባለፈው ሳምንት በእስራኤል ጥቃት መገደላቸው ሲነገር ሰንብቷል፡፡ ላርጃኒን ተከትሎም የቀድሞው የደህንነት ሚኒስትርም ተገድለዋል፡፡ ከ3 ሳምንታት በላይ ባስቆጠረው ጦርነት የቀድሞው ጠቅላይ መሪ አሙያቶላህ ዓሊ ሐሚኒን ጨምሮ በርካታ ሹሞች መገደላቸው ይነገራል፡፡ በጦርነቱ በአገሪቱ ከ1300 በላይ ሰዎች ተገድለዋል ተብሏል፡፡ ኢራንም በእስራኤል እና የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች በሚገኙባቸው የአረብ አገሮች የአፀፋ የሚሳየል እና የድሮን ጥቃት እየሰነዘረች መሆኑን መረጃው አስታውሷል፡፡ #አሜሪካ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ በጦርነቱ ማብቂያ
Mar 252 min read


የድንበር ላይ ስልጠና ወስደው ሰርተፊኬት የሌላቸው ሰዎች፤ የሀገር ድንበር ተሻግረው መገበያየት እንዳይችሉ ሊደረግ ነው፡፡
መጋቢት 16/2018 የድንበር ላይ ስልጠና ወስደው ሰርተፊኬት የሌላቸው ሰዎች፤ የሀገር ድንበር ተሻግረው መገበያየት እንዳይችሉ ሊደረግ ነው፡፡ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ለድንበር አካባቢ ነዋሪዎች የድንበር ተሻጋሪ ንግድ ሥልጠና እሰጣለሁ ብሏል። ከስልጠናው በኋላ ሰርተፊኬት የሌላቸው ሰዎች ድንበር ተሻግረው መገበያየት አይችሉም ተብሏል። ይህ የተባለው የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ተቋም (IOM) እና ከጃፓን መንግስት ጋር በጋራ በመሆን ያዘጋጁትን የድንበር ተሻጋሪ ንግድ የሥልጠና ማኑዋል ባስተዋወቁበት መድረክ ላይ ነው። በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ትስስር እና ኤክስፖርት ፕሮሞሽን አማካሪ የሆኑት አቶ ፀጋው በለጠ፤ በድንበር አካባቢ የሚኖሩ የኮንትሮባንድ ንግድ እና በድንበር ተሻጋሪ ንግድ ላይ ነዋሪዎ
Mar 251 min read
በትምህርት ዘርፍ የተሰሩ ቴክኖሎጂዎችን የሚያሳይ ኤድቴክ ኤግዚቢሽን በሳይንስ ሙዝየም ተከፈተ።
መጋቢት 16/2018 በትምህርት ዘርፍ የተሰሩ ቴክኖሎጂዎችን የሚያሳይ ኤድቴክ ኤግዚቢሽን በሳይንስ ሙዝየም ተከፈተ። በኤግዚቢሽኑ የቀረቡ ቴክኖጂዎቹን የፈጠሩ ባለሙያዎች በማስተርካርድ ፋውንዴሽን ኤድቴክ ፌሎውሺፕ ስልጠና ያገኙ ወጣቶች መሆናቸው ተነግሯል። የሪች ፎር ቼንጅ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር መቅድም ጉልላት እነዚህ ሰልጣኞች ሁለተኛ ዙር መሆናቸውን የጠቀሱ ሲሆን አሁንም 3ተኛ ዙር ሰልጣኞች በቅርቡ ወደ ስልጠና ይገባሉ ብለዋል። የሚሰሩት የፈጠራ ስራዎች የሀገሪቱን ትምህርት ዘርፍ የሚያሳድግና የሚደግፍ ሆኖ እንደሚዘጋጅ የተነገረ ሲሆን በ2ተኛ ዙር የኢድ ቴክ ኤክስፖ ላይ የቀረቡ የቴክኖሎጂ የፈጠራ ስራ ውጤቶች ወደ ስራ እንዲገቡ ከባለሀብቶች ጋር ለማገናኘት መታለሙን ተጠቅሷል። በሁለተኛው ዙር ሰልጥነው የተመረቁ ባለሙያዎች 60 ሺህ ዶላር ድጋፍ እንደተደረ
Mar 251 min read


መጋቢት 15/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
መጋቢት 15/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #አሜሪካ_እና_ኢራን የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ሹሞች ጋር በጦርነቱ ማብቂያ ጉዳይ ተነጋግረን ተግባብተናል ማለታቸውን የቴህራን ሹሞች በጭራሽ ሐሰት ነው አሉ፡፡ ትራምፕ የኢራንን የኤሌክትሪክ አውታሮች በጦር ለመመነቃቀር የነበራቸውን እቅድ በተጨማሪ 5 ቀናት ያራዘሙት ከዚሁ ንግግር በኋላ እንደነበር እወቁልኝ ብለው ነበር፡፡ የኢራን ፓርላማ አፈ ጉባኤ ግን ከአሜሪካ ሹሞች ጋር በየትም ቦታ በየትኛውም የመገናኛ ዘዴ የተደረገ ንግግር የለም ማለታቸው ቢቢሲ ፅፏል፡፡ ትራምፕ ከኢራን ሹሞች ጋር በተደረገ ንግግር የመካከለኛው ምስራቅ ልዩ መልዕክተኛቸው ስቴቭ ዊትኮፍ እና አማቻቸው ጃሬድ ኩችነር አሜሪካን በመወከል የተሳተፉበት ነበር ብለዋል፡፡ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ ኢራን የሆር
Mar 242 min read


እናት ባንክ በባንክ ዘርፍ በአመራርነት ደረጃ የሴቶችን ተሳትፎ እንዴት ማሳደግ ይቻላል በሚለው ጉዳይ በተለያዩ የሞያ ዘርፎች ከተሰማሩ ባለሞያዎች ጋር ተወያዩ።
መጋቢት 15/2018 እናት ባንክ በባንክ ዘርፍ በአመራርነት ደረጃ የሴቶችን ተሳትፎ እንዴት ማሳደግ ይቻላል በሚለው ጉዳይ በተለያዩ የሞያ ዘርፎች ከተሰማሩ ባለሞያዎች ጋር ተወያዩ። ከከተመሰረተ ከ14 ዓመት በላይ ያስቆጠረው እናት ባንክ ሴቶች በኢኮኖሚው እንዲበቁ የተለያየዩ ስራዎችን እየከወኑ እንደሆኑ የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ አስቴር ሰለሞን ተናግረዋል። ሴቶች ወደ አመራርነቱ እንዲመጡ የተለያዩ እና እነሱን ብቁ የሚያደርጉ ስልጠናዎችን በመስጠት ወደ ከፍታ ሃላፊነት ማምጣት እንደሚቻል ተወያዩቹ ተናግረዋል። በዚህም ሴቶች የሚገጥማቸውን ችግር መለየት እና እንቅፋቶቻቸውን በማንሳት ወደ አመራርነቱ ማምጣት እንደሚቻልም ሲነገር ሰምተናል። እራሳቸው ሴቶቹም የማንንም እገዛ ሳይፈልጉ እችላለሁ በሚል ወደፊት በመምጣት ብቁ እና ለቦታው የሚመጥኑ መሆናቸውን
Mar 241 min read


ለስኳር በሽታና ለደም ግፊት የሚሆኑ የባህል መድሃኒቶች በዘመናዊ መልኩ ተመርተው ወደ ገበያ ሊቀርቡ ነው ተባለ፡፡
መጋቢት 15/2018 ለስኳር በሽታና ለደም ግፊት የሚሆኑ የባህል መድሃኒቶች በዘመናዊ መልኩ ተመርተው ወደ ገበያ ሊቀርቡ ነው ተባለ፡፡ ከስኳር እና ደም ግፊት ባሻገር የተለያዩ በሽታዎችን ያክማሉ ተብለው የተመረጡ ስምንት የባህል መድሃኒቶች በዘመናዊ መንገድ ተመርተው ለገበያ ሊርቡ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ ምርቶቹ በስፋት በአምራች ኢንዱስትሪዎች ተመርተው ለተጠቃሚ ከመቅረባቸው በፊት ተቆጣጣሪ የመንግስት ተቋማት ተገቢውን ፍተሻ አድርገው ይሁንታ መስጠት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህን ያለው አርማወርሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩ ነው፡፡ እነዚህ የተመረጡ የባህል መድሃኒቶች ከመመረታቸው በፊት ፈዋሽነታቸው እና የጎንዮሽ ጉዳታቸውን በተመለከተ በላብራቶሪ የተላረጋገጡ መሆናቸውን ተነግሯል፡፡ ይህን የነገሩን በአርማወርሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩ የፋርማስቲካል ኢንዱስትሪ ልማት ዘ
Mar 241 min read


ህንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው አፍሪካ የሚገኙ ዜጎቿን አቅም ተጠቅማ የህንድና አፍሪካ ግኑኝነትን ለማጠናከር በብርቱ ለመመስራት ማሰቧ ተሰማ።
መጋቢት 15/2018 ህንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው አፍሪካ የሚገኙ ዜጎቿን አቅም ተጠቅማ የህንድና አፍሪካ ግኑኝነትን ለማጠናከር በብርቱ ለመመስራት ማሰቧ ተሰማ። ይህንን ለማድግ ያግዛል የተባለ ውይይት አዲስ አበባ በሚገኘው የህንድ ኤምባሲ ትናንት ምሽት ተደርጓል። ህንድ ኢትዮጵያ ጨምሮ በመላው አፍሪካ 3 ሚሊዮን ዲያስፖራ እንዳላት ተነግሯል። የሀገሪቱ ዜጎች ኒው ዴሊ ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላትን ግኑኝነት ለማጠናከር በምን በምን ዘርፎች ቢሰሩ ይሻላል፣ምን ጉድለት አለ? ምንስ ፈተናዎች አሉ በሚለው ላይ በየዘርፉ ገለፃ ተደርጎ ውይይት ተካሂዷል። በሰው ሰራሽ አስተውህሎት ወይም AI ዘርፍ ህንድ በአለም ዙሪያ ተፅዕኖ እያሳደረች መሆኑ የተነገረ ሲሆን በአፍሪካም በተለይም በAI የታገዘ በግብርና፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ ዘርፎች ዜጎቿ በስፋት መሰማራት የሚች
Mar 242 min read


የኮንትሮባንድ እቃዎች ጭኖ የተገኘተሽከርካሪ በመንግስት እንዲወረስ የሚያስገድድ አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ፡፡
መጋቢት 15/2018 የኮንትሮባንድ እቃዎች ጭኖ የተገኘተሽከርካሪ በመንግስት እንዲወረስ የሚያስገድድ አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ፡፡ እንደገና ተሻሽሎ ዛሬ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት በቀረበው የጉምሩክ አዋጅ የኮንትሮባንድ እቃዎችን ለማሳለፍ የሚሆን መደበቂያ ቦታ የተሰራለት ተሽከርካሪ ወይም ሙሉ በሙሉ የኮንትሮባንድ እቃ የጫነ መሆኑ ከተረጋገጠ መኪናው በመንግስት እንዲወረስ ተደንግጓል፡፡ ከሰባት አመት በፊት በፀደቀው የአዋጁ ማሻሻያ ተሽከርካሪዎች በኮንትሮባንድ ንግድ ስራ ላይ ተሰማርተው ቢገኙም ባለቤቶቹ በወንጀሉ ተሳታፊ ባልሆኑበት ሁኔታ ንብረታቸው እንዲወረስ መደረጉ ፍትሃዊ አይደለም በሚል 100 ሺህ ብር ቅጣት እንዲጣልባቸው ተደንግጎ እንደነበር ለፓርላማ የቀረበው የማሻሻያ አዋጁ ማብራሪያ ያስታውሳል፡፡ ይሁንና ኮንትሮባንዲስቶች ራሳቸው ይሄንኑ የ100 ሺ
Mar 242 min read


ኢትዮጵያ በአለም አምስተኛዋ ግዙፍ አበባ ላኪ ሀገር ሆናለች ተባለ።
መጋቢት 15/2018 ኢትዮጵያ በአለም አምስተኛዋ ግዙፍ አበባ ላኪ ሀገር ሆናለች ተባለ። በ2017 ብቻ ወደ ውጪ ከተላከ አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ከ564 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ መገኘቱ ተነግሯል። በግብርናው ዘርፍ የ #አበባ ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ንዑስ ዘርፍ ከቡና በመቀጠል ለኢትዮጵያ ከፍተኛውን የውጪ ምንዛሪ አስገኝቷል። ንዑስ ዘርፉ አብዛኞቹ ሴቶች እና ወጣቶች ለሆኑ 200 ሺህ ሰዎች የስራ ዕድል መፍጠሩን ሰምተናል። ከንዑስ ዘርፉ አበባ ከፍ ያለውን ድርሻ መያዙ የተጠቀሰ ሲሆን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከኬንያ በመቀጠል ምርቱን ወደ ውጪ በመላክ ሁለተኛዋ ሀገር እንደሆነች የተናገሩት የግብርና ሚኒስትር ድኤታ የሆኑት ሶፊያ ካሣ ናቸው። ከአለም ደግሞ አምስተኛ እንደሆነች ጠቅሰዋል። በጥቂት ዓመታት ውስጥ ኬንያን በመብለጥ በአፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር ት
Mar 241 min read


በኢትዮጵያ ንፁህ መጠጥ ውሃ የሚያገኘው ህዝብ ቁጥር 81.2 ሚሊየን ደርሷል ተባለ።
መጋቢት 15/2018 በኢትዮጵያ ንፁህ መጠጥ ውሃ የሚያገኘው ህዝብ ቁጥር 81.2 ሚሊየን ደርሷል ተባለ። ኢትዮጵያ ለጅቡቲ በቀን 100 ሺህ ሜትር ኪዩብ የመጠጥ ውሃን እያቀረበች መሆኑም ተነግሯል። በቢሾፍቱ እየተካሄደ ባለው የውሃ ዲፕሎማሲና ኮሚኒኬሽን ጉባኤ ላይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ.ር) ሲናገሩ እንደሰማነው ንፁህ የመጠጥ ውሃ የሚያገኘው ህዝብ 81.2 ሚሊየን ደርሷል። ግን ዛሬም ከመጠጥ ውሃ አቅርቦት ጋር በተገናኘ ብዙ ጥያቄ ይነሳል። በሳምንት አንዴና ሁለቴ ነው የምናገኘው ከሚለው አንስቶ በየቦታው ከንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ጋር በተገናኘ የሚነሳው ጥያቄ ብዙ ነው። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ.ር) ይህ ጥያቄ በየጊዜው እንደሚነሳ እናውቃለን ይላሉ። በውሃ እጥረት ምክንያት ሁሉም ሰው በግቢውና በቤቱ ጣራ ማጠራቀሚያ
Mar 242 min read


ፓርቲዎች በየመገናኛ ብዙሃኑ የሚያቀርቡት የምርጫ ማኒፌስቶ ለህዝብ ግልፅ በሆነ መልኩ እንዲያቀርቡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ድርጅት ህብረት ጠየቀ፡፡
መጋቢት 15/2018 ፓርቲዎች በየመገናኛ ብዙሃኑ የሚያቀርቡት የምርጫ ማኒፌስቶ ለህዝብ ግልፅ በሆነ መልኩ እንዲያቀርቡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ድርጅት ህብረት ጠየቀ፡፡ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ እስካሁን እየቀረቡ ያሉት የፖለቲካ ፓርቲዎች የመገናኛ ብዙሃን ክርክር ጠንካራም ደካማ ጎንም አላቸው ብሏል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ፖሊሲያቸውን ለህዝቡ ግልጽ ማድረግ እና ባሉት አማራጮች ሁሉ ማግኘት የሚቻል አድርጎ ማስቀመጥ አለባቸውም ተብሏል፡፡ ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ለማድረግ በጣት የሚቆጠር ወር ቢቀረውም በምርጫው ከሚወዳደሩት 47 ፓርቲዎች ክርክር የሚያደርጉትና ፖሊሲያቸውን በግልጽ የሚያስተዋወቁት ጥቂቶቹ ብቻ እንደሆኑ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች ህብረት ዋና ዳይሬክተር አቶ መስዑድ ገበየሁ ያስረዳሉ። መራጮች አንድን ፓርቲ የሚመርጡት አስቀድ
Mar 241 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

