top of page


በአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ የተሻለ የስራ ዕድል ቢፈጠርም አሁንም ብዙ ቀሪ ስራዎች አሉ ተባለ።
ህዳር 11 2018 በአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ የተሻለ የስራ ዕድል ቢፈጠርም አሁንም ብዙ ቀሪ ስራዎች አሉ ተባለ። ዘርፉ ለ200,000 ሰዎች የስራ ዕድል መፍጠሩ የተነገረ ሲሆን 80 በመቶዎቹ ሴቶች መሆናቸው ተጠቅሷል። መዋዕለ ነዋይ በማፍሰስ ወደ ዘርፉ ልማት መግባት ለሚፈልጉ ሴቶች ግን አሁንም ሁኔታዎች ብዙም ምቹ አለመሆናቸው ተነግሩዋል፡፡ የመሬትና የብድር አቅርቦት በዘርፉ መሠማራት የሚፈልጉ ሴቶችን ይገጥማሉ ከተባሉ ችግሮች መካከል ናቸው። ዘርፉ ላይ በአመራር ደረጃ ያሉ ሴቶች ቁጥርም ዝቅተኛ ነው። የኢትዮጵያ አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ አምራቾችና ላኪዎች ማህበር ትኩረቱን በሴቶች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ላይ ያደረገ ኮንፈረንስ እያካሄደ ነው። ኢትዮጵያ አሁን ላይ ከአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ከ500 ሚሊየን ዶላር በላይ በያመቱ እንደምታገ
Nov 201 min read


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ከሀገር ከወጡ ከመቶ ዓመት በላይ ያስቆጠሩ ቅርሶች ተቀበለ
ህዳር 11 2018 ከሀገር ከወጡ ከመቶ ዓመት በላይ ያስቆጠሩ ቅርሶች፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ተቀበለ። ቅርሶቹ 12 ሲሆኑ በአንድ ቤተሰብ አባላት ተጠብቀው የቆዩ መሆናቸውን ሰምተናል። ከቅርሶቹ መካከል ፎቶግራፎች፣ ጋሻ፣ ዘውድ፣ ዝናር፣ ጎራዴ እና ሌሎች ይገኙበታል። ቅርሶቹ ከ1913 እስከ 1921 ዓ.ም በወቅቱ በነበሩት ንግስተ ነገስታት ዘውዲቱ እና ከአልጋወራሽ ተፈሪ መኮንን በኢትዮጵያ የጀርመን መልዕክተኛ ለነበሩት ቪስ ትሪዝ በስጦታ መልክ የተበረከተላቸው እንደሆኑም ሰምተናል። ቅርሶቹን በአሁኑ ሰዓት በስዊዲን ሀገር የሚኖሩት የመልዕክተኛው የልጅ ልጅ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም በዛሬው ዕለት በራስ መኮንን አዳራሽ በተከናወነ ሥርዓት አስረክበዋል። ቅርሶቹ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለ
Nov 201 min read


''ያለ ረዳት አገልግሎት የሚሰጡ የህዝብ ማመለሽ ተሽከርካሪዎችን እቀጣለሁ'' የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ
ህዳር 10 2018 የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ያለ ረዳት አገልግሎት የሚሰጡ የህዝብ ማመለሽ ተሽከርካሪዎችን እቀጣለሁ አለ። ቢሮው ያለ ረዳት አገልግሎት የሚሰጡ ታክሲዎች በከተማዋ እየበዙ ነው ያለ ሲሆን ከዚህ በኋላ በመመሪያው መሰረት ረዳት የሌላቸውን ታክሲዎች እቀጣለሁ ብሏል። የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የትራንስፖርት አገልግሎት ክትትልና ኢንስፔክሽን ዳይሬክተር አቶ ጌትነት ታመነ ያለ ረዳት ማሽከርከር ገንዘብ በመቀበል፣ገቢና ወራጅ በመቆጣጠር የሹፌሩን ትኩረት ስለሚሰርቅ ለአደጋ ያጋልጣል ብለውናል። ኃላፊው ከዚህ ቀደም ለሌሎች የትራንስፖርት እንቅስቃሴዎች ብቻ ትኩረት በመስጠታችን ረዳት ያላቸውና የሌላቸውን ተሽከርካሬዎች የመለየት ውስንነት ታይቶብናል ብለዋል። ከዚህ በኋላ ግን የታክሲ ረዳት መኖር አንዱ የትራፊክ ደህንነት አካ
Nov 191 min read


ላለፉት 6 ዓመታት በጉምሩክ ተይዘውብኝ የነበሩት ኮምፒውተሮች ተለቀውልኛል ሲል ራዕይ የህፃናት መርጃ ድርጅት ተናገረ፡፡
ህዳር 10 2018 ላለፉት 6 ዓመታት በጉምሩክ ተይዘውብኝ የነበሩት ኮምፒውተሮች ተለቀውልኛል ሲል ራዕይ የህፃናት መርጃ ድርጅት ተናገረ፡፡ ይህ የሆነው ጉዳዩን ወደ ሚዲያ ካመጣሁት በኋላ ነውም ብሏል፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት የአዕምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸውን ህፃናት ለማሰልጠን ሊውል የነበረና በልገሳ ከውጭ ሃገር ያስገባሁት ኮምፒውተር በጉምሩክ ተይዞ 6 ዓመት ሆነው ሲል የህፃናት መርጃ ድርጅቱ ተናግሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ከድርጅቱ የኢትዮጵያ ተጠሪ ወ/ሮ ሰሎሜ ኩምሳ እንደሰማነው መረጃው በሚዲያ በተሰራጨ ማግስት ከድርጅቱ የክብር አምባሳደር አትሌት መሰረት ደፋር ጋር በመሆን ድርጅቱ ለጉምሩክ ኮሚሽን ኮምፒውተሮቹ እንዲመለሱለት ያቀረበው ጥያቄ ወዲያውኑ ምላሽ አግኝቶ፤ 107 ኮምፒውተሮች፣ እንደ ኪቦርድ፣ ጊታር፣ ድራም ያሉ የሙዚቃ መሳሪያዎችን፣ የል
Nov 192 min read


በላይአብ ሞተርስ እና የቻይናው ዩቺ አይ ኩባንያ በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት መስማማታቸውም ተሰምቷል
ህዳር 10 2018 በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ የትኞቹ ተሽከርካሪዎች ናቸው ወደ ሀገር ቤት መግባት ያለባቸው? የሚለውን የሚወስን መመሪያ ተዘጋጅቷል፤ በቅርቡም ይፀድቃል ሲል የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር ተናገረ፡፡ በላይአብ ሞተርስ እና የቻይናው ዩቺ አይ ኩባንያ በ #ተፈጥሮ_ጋዝ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት መስማማታቸውም ተሰምቷል፡፡ አሁን የተለያዩ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን በማስመጣት ላይ የሚገኘው በላይ አብ ሞተርስ ከዶንግ ፊንግ ሞተርስ ጋር በመሆን በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ለማቅረብ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ተናግሯል፡፡ የመኪናዎቹ ሽያጭ ወደ ገበያ በሚገባበት ወቅት አስፈላጊውን የመኪና መለዋወጫና ሌሎች ግብአቶችን ለማቅረብ ከስምምነት መድረሱንም ሰምተናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ማርታ በቀለ የሸገርን ወ
Nov 191 min read


‘’አዲስ ወደ ስራ ለሚገቡ ኢንተርፕራይዞች ብድር የሚሰጡ ተቋማት እጅግ ዝቅተኛ ናቸው’’ የኢንተርፕራይዝ ልማት ኢንስቲትዩት
ህዳር 10 2018 ‘’አዲስ ወደ ስራ ለሚገቡ ኢንተርፕራይዞች ብድር የሚሰጡ የፋይናንስ ተቋማት እጅግ ዝቅተኛ ናቸው’’ ሲል የኢንተርፕራይዝ ልማት ኢንስቲትዩት ተናገረ፡፡ በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ ውስጥ የኢንተርፕራይዞች ቁጥር በሚፈለገው ልክ እንዳያድግና ዘርፉ ለውጥ እንዳያመጣ አድርጓል ተብሏል፡፡ የኢንተር ፕርነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን(ዶ/ር) እንደ አፍሪካ እንኳን ቢታይ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የኢንተርፕራይዞች ቁጥር እጅግ አነስተኛ ነው ይላሉ፡፡ ለዚህ ብዙ ምክንያቶች ቢኖርም ዋነኞቹ መንግስት በሚፈለገው ልክ አስቻይ ሁኔታ አለመዘርጋቱ ፣ ሀሳብ ያላቸው ወጣቶች ወደ ስራ ለመግባት ድፍረት ማጣት ተጠቃሽ ናቸው ይላሉ፡፡ ከዚህ ባለፈም ሀሳባቸውን ወደ ስራ ለማስገባት የሚጥሩ ስራ ፈጣሪዎች የፋይናንስ አቅርቦት እጥረ
Nov 192 min read


''በህገ ወጥ መንገድ ወደ አረብ ሀገራት ሄደው ጉዳት ደርሶባቸው ከሚመለሱት መካከል የኤችአይቪና ካንሰር ህመም ተጋላጭ ሆነው አግኝቻቸዋለሁ'' አጋር ኢትዮጵያ
ህዳር 10 2018 በህገ ወጥ መንገድ ወደ አረብ ሀገራት ሄደው ጉዳት ደርሶባቸው ከሚመለሱት መካከል አብዛኞቹ የኤች አይ ቪ ኤድስ እና ካንሰር ህመም ተጋላጭ ሆነው አግኝቻቸዋለሁ ሲሉ ተመላሽ ስደተኞች የሚረዳው አጋር ኢትዮጵያ የተባለ ድርጅት ተናገረ፡፡ ከስደት ተመላሾቹ ህገ-ወጡን መንገድ ይዘው ወደ አረብ ሀገራት እንዲሄዱ የሚገፋፋቸው ብዙውን ጊዜ ዘመድ ቤተሰቦቻቸው ስለሚሆኑ ተጎጂዎቹ እነሱን ለመክሰስም፣ ለመውቀስም እየተቸገሩ መሆኑን ሰምተናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… ገዛ ጌታሁን የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘
Nov 191 min read


ባለሞያ ቀጥረው ለመከራከር አቅም ለሌላቸውና መንግስት ነፃ የህግ አገልግሎት የሚሰጣቸው ሰዎች
ህዳር 10 2018 በፍርድ ቤቶች ጠበቃ አቁመው የህግ ባለሞያ ቀጥረው ለመከራከር አቅም ለሌላቸው ሰዎች መንግስት ነፃ የህግ አገልግሎት ይሰጣል፡፡ ነፃ የህግ አገልግሎት በተለይም በሴቶች፣ በህፃናት፣ በአካል ጉዳተኞችና በአረጋዊያን ላይ ትኩረት እንደሚያደረግ በፍትህ ሚኒስቴር የንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት ከፍተኛ አቃቢ ህግ አቶ ተሰማ ግደይ ነግረዉናል፡፡ ዐቃቢ ህጉ ባለፉት 3 ወራት ውስጥ በፍትህ ሚኒስቴር 178 ፤ በጠቅላይ ፍ/ቤት ደግሞ ከ1300 በላይ ሰዎች ነፃ የህግ አገልግሎት አግኝተዋል ብለዋል፡፡ ይህም ፍትህ እንዳይጓደል፣ ድሃ እንዳይበደል፣ ሁሉም ሰው በህግ ፊት እኩል ነው የሚለውን መርህ ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ አቶ ተሰማ ጠቁመዋል፡፡ ይሁን እንጂ ነፃ የህግ አገልግሎቱን እንዲሰጡ ሀላፊነት የሚሰጣቸው የህግ ባለሙ
Nov 191 min read


በኢትዮጵያ በሰብአዊ ድጋፎች ላይ የሚከወኑ ስራዎችን የሚደግፉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ተሳትፎ የቀነሰ ነው፡፡
ህዳር 9 2018 በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ሰብአዊ ድጋፎች ላይ የሚከወኑ ስራዎችን የሚደግፉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ የቀነሰ ነው፡፡ በዚህም ሀገሪቱ ፊቷን ሀገር በቀል ወደሆኑና በራስ አቅም ዘላቂ ድጋፍ ወደ ሚገኝበት መንገድ እያዞረች መሆኑ ተነግሯል። በኢትዮጵያ በተቀናጀ መንገድ የሰብአዊ እርዳታ ለማድረግ የሚያስችል ጥምረት ተመስርቷል። በተለያዩ የድጋፍ ዘርፎች ላይ የሚሰሩ 20 ሀገር በቀል የእርዳታ ድርጅቶች የመሰረቱት ''the consortium of humanitarian actors for national grow empowerment'' ወይም CHANGE የሚል ስያሜ የተሰጠው ጥምረቱ ዛሬ በስካይላይት ሆቴል ይፋ ሆኗል፡፡ የሰብአዊ ድጋፍ ስራዎችን ሀገር በቀል በሆኑ ተቋማት መስራት በተለይም የሰብአዊ እርዳታ የሀገር ጥቅምን በማይጎዳ መ
Nov 192 min read


ወደ አውሮፓ ህብረት የሚላክ በአነስተኛ አርሶ አደሮች ማሣ የተመረተ ቡና ከደን ምንጣሮ ነፃ ስለመሆኑ ለማረጋገጥ የሚያስችል ስራ ኢትዮጵያ ጀምራለች ተባለ
ህዳር 10 2018 ወደ አውሮፓ ህብረት የሚላክ በአነስተኛ አርሶ አደሮች ማሣ ላይ የተመረተ ቡና ከደን ምንጣሮ ነፃ ስለመሆኑ ለማረጋገጥ የሚያስችል ስራ ኢትዮጵያ ጀምራለች ተባለ። ስራው የተጀመረው ህብረቱ ወደ አባል ሀገራቱ የሚላክ የግብርና ምርት ከደን ምንጣሮ ነፃ መሆን እንዳለበት የሚያስገድደውን ህግ ለመተግበር እየተዘጋጀ ባለበት ወቅት ነው። የህብረቱ ህግ የህፃናትን ጉልበት በመጠቀም የሚለቀም ቡና ወደ አባል ሀገራቱ እንዳይገባ የሚከለክል መሆኑንም ሠምተናል። ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ንጋቱ ረጋሣ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerF
Nov 191 min read


አርተፊሻል ኢንተለጀንስ ስጋት ወይስ ዕድል?
ህዳር 9 2018 ሰው ሰራሽ አስተውህሎት Artificial_Intelligence በፍጥነት እየተስፋፋ ነው፡፡ ትምህርቱም ፣ ፊልሙም ፣ ሙዚቃውም አርተፊሻል ኢንተለጀንስ #AI ያልገባበት ማግኘት ያስቸግራል፡፡ በዚህ ዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂ ላይ ስጋታቸውን የሚናገሩ እንዳሉ ሁሉ ፣ ከመስጋት ይልቅ ቀረብ ብሎ ማወቅ ይበጃል የሚሉም አሉ፡፡ ይሁን እንጂ ከሰዎች በላይ የሚያስብና ዓለምን መረዳት የሚችል ማሽን ከመጣ "ሰው የሚለው ትርጉም የትኛውን ቦታ ይይዛል" የሚለው አሁንም የዘርፉ ባለሙያዎች ጥያቄ ሆኖ ቀጥሏል፡፡ በአንድ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ስራ ተቋም ውስጥ በአማካሪነት የሚሰሩት መቅደስ አሰፋ ግን AI ስጋት ነው በሚለው ሃሳብ አይስማሙም፡፡ ባለሙያዋ AI ሰውን የሚተካ ሳይሆን፣ AIን የሚጠቀም ሰው AIን የማይጠቀምን ሰው ይተካል ይ
Nov 182 min read


ህዳር 9 2018 -የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#አሜሪካ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ አገራቸው ለሳውዲ አረቢያ ዘመን አፈራሾቹን F 35 የጦር ጄቶች እንደምትሸጥ ፍንጭ ሰጡ፡፡ ቀደም ሲል አሜሪካ F 35 የጦር ጄቶች በአረብ አገሮች እጅ እንዲገቡ ፍላጎት እንዳልነበራት አልጀዚራ ፅፏል፡፡ አሁን ግን ትራምፕ ለሳውዲ F 35 የጦር ጄቶችን እንሸጥላታለን ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ ሳውዲዎች ታላቅ አጋሮቻችን ናቸው ይሄንንም እናደርገዋለን ብለዋል ትራምፕ፡፡ ትራምፕ የአብርሃም ስምምነቶች በሚሰኘው ማዕቀፍ ሳውዲ አረቢያ ከእስራኤል ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንድትመሰርትላቸው ይሻሉ ተብሏል፡፡ ሳውዲ አረቢያ ግን ከእስራኤል ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከመመስረቴ አስቀድሞ የፍልስጤማውያን ነፃ መንግስት በሚቋቋምበት መላ አስተማማኝ ዋስትና ማግኘት እሻለሁ እያለች ነው፡፡ ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሳውዲው
Nov 182 min read


በርካታ ወርቅ አምራች ድርጅቶች አፈፃፀማቸው "እጅግ በጣም ዝቅተኛ" እንደሆነ ተነገረ
ህዳር 9 2018 በርካታ ወርቅ አምራች ድርጅቶች አፈፃፀማቸው "እጅግ በጣም ዝቅተኛ" እንደሆነ በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ተነገረ። ይህ የተነገረው በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የኢንዱስትሪ እና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የማዕድን ሚኒስቴርን የ3 ወራት የስራ ክንውን ሪፖርት ትናንት ህዳር 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ባደመጠበት ወቅት ነው። የወርቅ ልማትን በተመለከተ ወደ ስራ የገቡ የወርቅ አምራች ኩባንያዎች፤ ለምሳሌ ዋይ ኤም ጂ (YMG) 10.74 ኪሎ ግራም አቅዶ 0.45 ኪሎ ግራም፣ ኢዛና 84.3 ኪሎ ግራም አቅዶ 42.1 ኪሎ ግራም፣ ዙምባራ 19.17 ኪሎ ግራም አቅዶ 3.4 ኪሎ ግራም፣ እስቴላ ትሬዲንግ ኢንዱስትሪ 9 ኪሎ ግራም አቅዶ 5.4 ኪሎ ግራም እንዲሁም ሲዳማ 3 ኪሎ ግራም ለማግኘት አቅዶ ምንም አለማግኘቱ በፓርላማ ጥያቄ አስ
Nov 182 min read


''በአሁኑ ሰዓት በአባይ ወንዝ ውሃ አጠቃቀም ግብፅን የምታሰጋት ሱዳን እንጂ ኢትዮጵያ አይደለችም'' ኢንጂነር ስለሺ በቀለ
ህዳር 8 2018 በአሁኑ ሰዓት በአባይ ወንዝ ውሃ አጠቃቀም ግብፅን የምታሰጋት ሱዳን እንጂ ኢትዮጵያ አይደለችም ሲሉ የታላቁ የህዳሴ ግድብ መሪ ተደራዳሪ ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ተናገሩ፡፡ ከህዳሴ ግድብ መገንባት በፊት ሱዳን በጎርፍና ደለል ትቸገር እንደነበር አሁን ግን ይሄ እየቀረ መሆኑንን ኢንጂነር ስለሺ ጠቁመዋል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ቴዎድሮስ ወርቁ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm
Nov 171 min read


የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ባለፉት 3 ወራት ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን ተከትሎ በተቋሙ ተልዕኮ ላይ ከፓርላማ ጥያቄ ቀረበበት።
ህዳር 8 2018 የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ባለፉት 3 ወራት ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን ተከትሎ በተቋሙ ተልዕኮ ላይ ከፓርላማ ጥያቄ ቀረበበት። በተቋሙ ላይ ጥያቄ የተነሳበት አገልግሎቱ የ3 ወራት የስራ ክንውን ሪፖርቱን በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነት እና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ዛሬ ከሰዓት በፊት ባቀረበበት ወቅት ነው። የተቋሙን የ3 ወራት የስራ ክንውን ሪፖርት በንባብ ያቀረቡት የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት ባለፉት 3 ወራት ከ545,000 በላይ የሚሆኑ ዜጎች የፓስፖርት አገልግሎት አግኝተዋል ብለዋል። ከዚህ ውስጥ ለ373,000 በላይ ዜጎች መደበኛ፣ ከ136 በላይ ለሚሆኑት አስቸኳይ ፣ ከ14,000 በላይ ኢ-ፓስፖርት እንዲሁም ከ20,000 በላይ ለሚሆኑት
Nov 172 min read


ሁለተኛው ግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ፕሮጀክት በነገው ዕለት ይፋ እንደሚደረግ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ተናገረ
ህዳር 8 2018 ሁለተኛው ግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ፕሮጀክት በነገው ዕለት ይፋ እንደሚደረግ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ተናገረ፡፡ ስራውን ለመተግበርም 128 ሚልዮን ዶላር ያስፈልጋል ተባለ፡፡ የመጀመሪያው የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ስራ ላለፉት 6 ዓመት ሲተገበር ነበር የተባለ ሲሆን 102 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ተደርጎበታል ተብሏል፡፡ በ2012 ዓ.ም በ600,000 ሄክታር መሬት ወደ ስራ ያስገባው የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር 4.4 ሚልየን ገበሬ በክላስተር ተደራጅቶ የቴክኖሎጂና የተሻለ ግብዓት ተጠቃሚ ለማድረግ እንደተሰራ ሰምተናል፡፡ ባለፉት 6 ዓመታት በተሰራው ስራ 12 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በክላስተር እየታረሰ ነው ያሉት በኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር
Nov 171 min read


ጉዳያችን - የሳይበር ጥቃት
ህዳር 8 2018 #ጉዳያችን - የሳይበር ጥቃት በየጊዜው የሚደርሱ የሳይበር ጥቃቶች አይነታቸው ተለዋዋጭ ነው። ለመሆኑ ልናውቃቸው የሚገቡ የሳይበር ጥቃት አይነቶች የትኞቹ ናቸው? በዚህ ጉዳይ ላይ የኤ.አይ.ቲ ቴክኖሎጂ ስራ አስኪያጅና የቴክኖሎጂ ባለሙያው አቶ እስራኤል ብሩክ የሰጡንን ማብራሪያ ለማድመጥ… ቴዎድሮስ ወርቁ ነው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s 🐦X : https://x.co
Nov 171 min read


ወደ ትግራይ ክልል ገብቶ አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት ለመጀመር እስካሁን ያደረገው ጥረት የሚፈለገውን ውጤት እንዳላመጣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተናገረ፡፡
ህዳር 8 2018 ወደ ትግራይ ክልል ገብቶ አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት ለመጀመር እስካሁን ያደረገው ጥረት የሚፈለገውን ውጤት እንዳላመጣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተናገረ፡፡ ኮሚሽኑ ይህንን ያለው ካሳለፍነው ህዳር 5 እስከ 7 2018 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ከፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር በመከተበት ወቅት ነው፡፡ የተሳታፊ ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራዎችን በማገባደድ ወደ ሃገራዊ ምክክር ጉዳኤው ለመሸጋገር የሚያስችሉትን ስራዎች እየከወነ መሆኑን የሚናገረው ኮሚሽኑ በሂደቱ የገጠሙትን ፈተናዎችም ጠቅሷል፡፡ ከችግሮቹ መካከል ቀዳሚው ነው ያለው እስካሁን ድረስ በትግራይ ክልል አጀንዳ የማሰባሰብ ስራዎች አለመጀመራቸውን ነው፡፡ የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር መላኩ ወልደማሪያም ስለዚህ ሲያስረዱ ኮሚሽኑ ከፕሪቶሪያው ስምምነት መፈረም ማግስት ጀምሮ በትግራይ ክል
Nov 172 min read


የአዲስ ቄራዎች ድርጅት አካባቢውን መበከል ካላቆመ ካለበት ቄራ አካባቢ እንዲነሳ የሚል የፍርድ ውሳኔ አፈፃፀም እንደተከፈተበት ተሰምቷል
ህዳር 5 2018 አካባቢን በመበከል በነዋሪው ላይ የጤና ጉዳት እያደረሰ ነው በሚል ክስ ቀርቦበት የነበረው የአዲስ ቄራዎች ድርጅት አካባቢውን መበከል ካላቆመ ካለበት የቄራ አካባቢ እንዲነሳ የሚል የፍርድ ውሳኔ አፈፃፀም እንደተከፈተበት ተሰምቷል፡፡ ቄራዎች ከአካባቢው ይነሳል አይነሳም የሚለውን ለመወሰን ለፊታችን ህዳር 15 በፍርድ ቤት ቀጠሮ ተሰጥቷል ተብሏል፡፡ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ከ30 ዓመታት በላይ አጥንት፣ደም፣ ቁርጥራጭ ስጋና መሰል የእርድ ተረፈ ምርቶችን በመልቀቅ አካባቢውን ሲበክል ቆይቷል በሚል ቁም ለአካባቢህ በተባለው ሃገር በቀል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት በፍርድ ቤት ክስ ቀርቦበት እንደነበር ይታወሳል፡፡ ፍርድ ቤቱም ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ በሰጠው ውሳኔ የቄራዎች ድርጅት በሚለቅቀው በካይ ፈሳሽ፣ጠጣርና ጋዝ የነዋሪ
Nov 142 min read


ሬፍሌክስሎጂ (Reflexology) ምንድነው?
ሬፍሌክስሎጂ (Reflexology) ምንድነው? በጥንታዊ ግብጻውያን ፣ ቻይና እና ህንድ ውስጥ በባህላዊ መንገድ እንደተጀመረ የሚነገርለት ሬፍሌክስሎጂ በ1900 በተደረገ ጥናት መሰረት የውስጥ እግር ላይ እያንዳንዱን የሰውነትን ክፍልን የሚወክል ነርቭ እንዳለ በሳይንስ ተረጋግጧል ይላሉ። ሬፍሌክስሎጂ (Reflexology) በእግር ፣ በእጅ መዳፍ እና በጆሮ አከባቢ የሚገኙ የነርቭ ጫፎችን በማሸት የተለያዩ የሰውነት ክፍሎች ጋር የሚደርስ በሳይንስ የተረጋገጠ አጋዥ ህክምና እንደሆነ የሬፍሌክስሎጂ ባለሙያ የሆኑት ብርሃኑ ጣሰው ይናገራሉ። ሳይንሱ እንደ ደም ግፊት ፣ ካንሰር ፣ ስኳር የመሳሰሉ ክሮኒክ ካልሆኑ በሽታዎች በስተቀር ሬፍሌክስሎጂ ከ8 እስከ 12 ዙር ቢታሹ እንደሚመክር አስረድተው ደም ግፊት ያለበት ሰው ግን አንገቱ አከባቢ ጫና ፣ ራስ
Nov 142 min read


ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ስምምነት ምክንያት የውጪ ባለሃብቶች ለኢንቨስትመንት እየመረጧት ነው ተባለ
ህዳር 5 2018 ኢትዮጵያ ከወር ግድም በፊት በይፋ በተቀላቀለችው የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ስምምነት ምክንያት የውጪ ባለሃብቶች ለኢንቨስትመንት እየመረጧት ነው ተባለ። በስምምነቱ መሰረት ወደ ተለያዩ ሀገራት የሚላኩ ምርቶች ጥራታቸውን የጠበቁ ስለመሆናቸው ጥብቅ የማረጋገጥ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ነግሮናል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠናን ባለፈው መስከረም ወር መጨረሻ በይፋ መቀላቀሏ ይታወሳል። ወደ አራት የአፍሪካ ሀገራት ምርቶችን በአየር እና በየብስ ትራንስፖርት በመላክ ነው የንግድ ቀጠናውን የተቀላቀለችው። በአየር ትራንስፖርት የተላኩት ስጋ እንዲሁም የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶች ሲሆኑ ፤በየብስ ትራንስፖርት ደግሞ የተላኩት ቡና፣ የጥራጥሬ ምርቶችና የቅባት እህሎች ናቸው። ኬንያ
Nov 142 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page








