top of page


የካቲት 2/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
የካቲት 2/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #ጃፓን በጃፓን LDP መራሽ ገዢ የፖለቲካ ጥምረት አብዛኛውን የፓርላማ መቀመጫ አሸነፈ ተባለ፡፡ ጥምረቱ 465 መቀመጫዎች ባሉት የህዝብ ተወካዮቹ ምክር ቤት 352ቱን ማሸነፉን ቢቢሲ ፅፏል፡፡ LDP ብቻውን 316 መቀመጫዎችን ማሸነፉ እንደ ታላቅ የምርጫ ስኬቱ ተቆጥሮለታል፡፡ ይሄ የፓርላማ አብላጫነት ለአዲሲቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሳናኤ ታካይቺ ከፍተኛ አቅም ይፈጥርላቸዋል ተብሏል፡፡ ታካይቺ በአገሪቱ ታሪክ የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ናቸው፡፡ ከሳቸው ቀዳሚ የነበሩ ሁለት የLDP ጠቅላይ ሚኒስትሮች የፓርላማውን አብላጫነት አጥተው እንደነበር መረጃው አስታውሷል፡፡ #ሶማሊያ የሶማሊያ የፀጥታ ሀይሎች 8 የአልሸባብ ፅንፈኛ ቡድን ታጣቂዎችን ገደልን አሉ፡፡ 8ቱ የአልሸባብ ታጣቂዎች የተገደሉት በመካከለኛ ጁባ ግዛት ቡ
Feb 91 min read


የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የፖሊሲ አውጪዎች የሚመክሩበት አህጉራዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነዉ ።
ጥር 29/2018 በበርካታ አፍሪካ ሀገራት የሚገኙ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የፖሊሲ አውጪዎች የሚመክሩበት PANAF (Pan-African Network for Artistic Freedom) አህጉራዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነዉ ። በሰላም ኢትዮጵያ (Selam Ethiopia) እና በአጋሮቹ አዘጋጅነት "ለመፍጠር ነፃነት በድጅታል እና በኢኮኖሚ መልክዓ ምድር ውስጥ ያሉ ሃይል ፣ተፅኖ እና እድሎች " በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ይህ ጉባኤ፣ የተለያዩ የፓናል ውይይቶች እንደሚቀርቡበት ተነግሯል። በተለያዩ ፖለቲካዊ ጫናዎች ምክንያት ስጋት ላይ የሚገኙ የጥበብ ባለሙያዎችን መብት መጠበቅ ፣የማህበራዊ ሚዲያ እና የዲጂታል መድረኮች መስፋፋትን ተከትሎ የሚመጡ አዳዲስ የሳንሱር አይነቶችን መከላከል፣የአፍሪካ መንግስታት ለኪነ-ጥበብ ዘ
Feb 61 min read


በአማራ እና በትግራይ ክልል፤ ለትምህርት ዘርፍ ማጠናከሪያ የሚውል ወደ 10 ሚሊዮን ዶላር የተጠጋ በጀት የተያዘለት ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ፡፡
ጥር 29/2018 በአማራ እና በትግራይ ክልል፤ ለትምህርት ዘርፍ ማጠናከሪያ የሚውል ወደ 10 ሚሊዮን ዶላር የተጠጋ በጀት የተያዘለት ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ፡፡ ፕሌይፉል ኢዱኬሽን ፓዝዌይስ ኢን ኢትዮጵያ(PEPE) የተሰኘው ይህ ፕሮጅክት በአማራ እና ትግራይ ክልሎች ከትምህርት ውጪ ያሉና በግጭት የተጎዱ አካባቢዎች ውስጥ ከትምህርት ውጪ የሆኑ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ለመመለስ ታሳቢ ያደረገ ነው ተብሏል፡፡ የማጠናከሪያ ፕሮግራሙ በኢንተርናሽናል ሬስኪው ኮሚቴ (IRC) መሪነት፣ ከሉሚኖስ ፈንድ(Luminos Fund)፣ ኢማኑኤል ደቨሎፕመንት አሶሴሽን(EDA) እና ከሌሎች ባለድርሻ ተቋማት ጋር በመተባበር ይተገበራል ተብሏል። ለዚህ ስራ 9,980,000 ዶላር እንደተያዘለትም ሰምተናል፡፡ የPEPE ፕሮግራም የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ዬዲት ፀጋዬ፤ ስራው በ3 ዓመት
Feb 61 min read


የተሰጠው የስራ ጊዜ ሲጠናቀቅ 2 ሳምንት የቀረው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል አለ፡፡
ጥር 29/2018 የተሰጠው የስራ ጊዜ ሲጠናቀቅ 2 ሳምንት የቀረው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል አለ፡፡ የካቲት 14 ቀን 2018 ዓ.ም የተሰጠው ጊዜ ገደብ የሚጠናቀቀው የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን "የጀመርኩት ስራ ተንጠልጥሎ እንዳይቀር " ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል ብሏል። መሰረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ተነጋግሮ መፍትሄ ለመስጠት በ2014 ዓ.ም እና አላግባብ ብለው በቆዩ ሃገራዊ የተቋቋመው የምክክር ኮሚሽን መጀመሪያ የተሰጠው የጊዜ ገደብ 3 ዓመት ነበር። በሰላም እጦት፣ በፖለቲካ አለመረጋጋት እና በተለያዩ ምክንያቶች በተሰጠው 3 ዓመት ተልዕኮውን ማጠናቀቅ ባለመቻሉ የህዝብ እንዳራሴዎች ምክር ቤት የካቲት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው አስቸኳይ ሰብሰባ ነበር የኮሚሽኑን የስራ ዘመን በአንድ ዓመት ያራዘመው። ኮሚሽኑም በተሰጠው
Feb 61 min read


የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ የፋይናንስ ተቋም ኪሳራ ላይ ሲወድቅ ለገንዘብ አስቀማጮች የሚከፍለውን ኢንሹራንስ ከፍ ለማድረግ እያሰበበት እንደሚገኝ ተናገረ፡፡
ጥር 29/2018 የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ የፋይናንስ ተቋም ኪሳራ ላይ ሲወድቅ ለገንዘብ አስቀማጮች የሚከፍለውን ኢንሹራንስ ከመቶ ሺህ ብር ከፍ ለማድረግ እያሰበበት እንደሚገኝ ተናገረ፡፡ አሁን ላይ ኪሳራ ለደረሰበት አንድ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ገንዘብ አስቀማጮች ኢንሹራንስ እየከፈልኩ እገኛለሁም ብሏል፡፡ የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ በባንኮች እና በማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ገንዘብ ላስቀመጡ ግለሰቦች እና ድርጅቶች ፤ የኢንሹራንስ ሽፋን በመስጠት ለገንዘብ አስቀማጮች ጥበቃ ለማድረግ የተቋቋመ ነው። ከተቋቋመ ወደ ሶስት ዓመት እየተጠጋ ሲሆን በዚህ ጊዜ ውስጥ በአጠቃላይ ከአባል ፋይናንስ ተቋማት የሰበሰበው አረቦን 17 ነጥብ 80 ቢሊየን ብር መድረሱን ሠምተናል። እስከ አሁን ከተሰበሰበው አጠቃላይ አረቦን ውስ
Feb 62 min read


በደቡብ ምስራቅ እስያ ይሰሩ የነበሩ ባለሃብቶች በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የታሪፍ ተጽዕኖ ምክንያት መዳረሻቸውን ኢትዮጵያ እያደረጉ ነው ተባለ።
ጥር 29/2018 በደቡብ ምስራቅ እስያ ይሰሩ የነበሩ ባለሃብቶች በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የታሪፍ ተጽዕኖ ምክንያት መዳረሻቸውን ኢትዮጵያ እያደረጉ ነው ተባለ። ኢትዮጵያም ዕድሉን በመጠቀም በተለይ ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ተጨማሪ ባለሃብቶችን ከአካባቢው ሀገራት ለመሳብ ጠንክራ እየሰራች እንደምትገኝ ተነግሯል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢትዮጵያን ጨምሮ አንድ መቶ በሚደርሱና ምርቶቻችውን ወደ አሜሪካ በሚልኩ ሀገራት ላይ ታሪፍ መጣላቸው ይታወሳል። ትራምፕ ከ10 በመቶ እስከ 54 በመቶ የሚደርስ ታሪፍ ነው በሀገራቱ ላይ የጣሉት። አስር በመቶ ታሪፍ ከተጣለባቸው ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ ፤ ኬንያ፣ ኤርትራ፣ ጅቡቲ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ይገኙባቸዋል። የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት የሆኑ
Feb 62 min read


በ2018 በጀት ዓመት በመንፈቅ ጊዜ 52.26 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ።
ጥር 29/2018 በ2018 በጀት ዓመት በመንፈቅ ጊዜ 52.26 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ። አጠቃላይ ወጪው ደግሞ 52.02 ቢሊዮን ብር መሆኑን አንስቷል። አገልግሎቱ ከኢነርጂ ሽያጭ፣ ከአዲስ ደንበኛ መስተንግዶ፣ ከማያገለገሉ ንብረቶች ሽያጭና ከልዩ ልዩ ገቢ በጠቅላላው 54.23 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ሲሰራ እንደነበር ተነግሯል። የተቋሙ የሰበሰበው ገቢ ከእቅዱ 96 በመቶ ያሳካ ነው ተብሏል፡፡ አገልግሎቱ ይህንን ያለው የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት አፈፃፀሙን በተመለከተ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው። በመጀመሪያ ስድስት ወራት ከኢነርጂ ሽያጭ 34.34 ቢሊዮን ብር፣ ከአዲስ ደንበኞች መስተንግዶ 16.7 ቢሊዮን ብር፣ እንዲሁም የማያገለግሉ ንብረቶችን በማስወገድና ከልዩ ልዩ ገቢ 1.2 ቢሊዮን
Feb 61 min read


ከመንግስትጋር እርቅ አድርጎ ወደ ሰላማዊ ትግል የገባው አፋሕድ አጀንዳ ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረከበ።
ጥር 28/2018 በኢትዮጵያ ገለልተኛ በሆነ ተቋም የህዝብ ቆጠራ እንዲካሄድ እና የአማራ ክልል ተወላጆችም በሚኖርበት ክልል የፖለቲካ ውክልና እንዲኖራቸው ከመንግስትጋር እርቅ አድርጎ ወደ ሰላማዊ ትግል የገባው አፋሕድ አጀንዳ አድርጎ ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረከበ። የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዛሬ ከድርጅቱ አመራሮች እና ተወካይዎች ጋር ተወያይቶ አጀንዳዎችን ተረክቧል። ደርጅቱ መሳሪያ አንስቶ ወደ ጨካ ለመግባት ምክንያት ሆነውኝ ነበር ያላቸውን በ17 ከፍል የተደራጁ አጀንዳዎቹን ለምክክር ኮሚሽን ዛሬ ከሰዓት በኋላ ማስረከቡን የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አቶ ኢያሱ አባተ ነግረዉናል። አቶ እያሱ የአማራ ክልል ህዝብ መፈናቀል ፣መሰደድ ፣ወሰን አለመከበር እና የማንንት ጥያቄዎች አለመመለስ ጫካ
Feb 52 min read


በቂ የነዳጅ ምርት ቢኖርም የነዳጅ አቅራቢዎች በየቀኑ ወደ አዲስ አበባ መግባት ያለበትን መጠን እያስገቡ አይደለም ተብሏል።
ጥር 28/2018 በአሁኑ ወቅት በቂ የነዳጅ ምርት ቢኖርም የነዳጅ አቅራቢዎች በየቀኑ ወደ አዲስ አበባ መግባት ያለበትን መጠን እያስገቡ አይደለም ተብሏል። በዚህም ምክንያት ከሰሞኑ ነዳጅ ለመቅዳት በማዲያዎች የሚደረጉ ረጃጅም ሰልፎች ተስተውለዋል ያለን የዘርፉን ግብይት የሚቆጣጠረው የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ነው። በከተማዋ ባሉ 125ቱም ማደያዎች ምን ያህል ነዳጅ በየትኛው ማደያ አለ የሚለውን እለታዊ መረጃ በማሰራጨት ቁጥጥር የሚያደርገው ቢሮው በቂ ነዳጅ አለ ለማለት በቀን ከ2.8 ሚሊዮን ሊትር በላይ ናፍጣ፣ ቤንዚን 2 ሚሊዮን ሊትር መኖር አለበት፤ አሁን ያለው 2.5 ሚሊዮን ሊትር ናፍጣ ነው ፤ ለዚህ ነው በየቦታው ሰልፍ የበዛው ሲሉ በቢሮው የንግድ ኢንስፔክሽንና ሬጉላቶሪ ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ አሰፋ አስረድተዋል። የወሩ መጨረሻ ሲቃረብ ሆን ብለው
Feb 51 min read


በተያዘው በጀት ዓመት 6 ወራት በስነ ምግባርና እና ብልሹ አሰራር ምክንያት 651 የሚሆኑ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሰራተኞች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተነገረ።
ጥር 28/2018 በተያዘው በጀት ዓመት 6 ወራት በስነ ምግባርና እና ብልሹ አሰራር ምክንያት 651 የሚሆኑ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሰራተኞች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተነገረ። አስተዳደራዊ እርምጃዎች ከተወሰደባቸው 651 ሰራተኞች የተሰናበቱ 13፣ የደመወዝ ቅጣት 481 እና 157 ደግሞ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ተነግሯል። ይህ የተነገረው አገልግሎቱ የ2018 በጀት ዓመት 6 ወራት አፈፃፀሙን በተመለከተ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው። በሌላ በኩል ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት በዲጅታል የሙስና መጠቆሚያ 251፣ በሌሎች አማራጮች (በአካል፣ በኢሜል፣ በስልክ) ደግሞ 60 በድምሩ 311 ጥቆማዎች እና አቤቱታዎች የቀረቡ መሆኑን ያነሳው አገልግሎቱ 270ቹ ተጣርተዋል ብሏል። በቀረቡ ጥቆማዎች መሰረትም ተጣርቶ ጥፋተኛ መሆናቸው ከተለዩ 118
Feb 51 min read


በኢትዮጵያ ከሚወለዱ 10,000 ህፃናት ውስጥ 80 የሚሆኑት የነርቭ ዘንግ ክፍተትና የጭንቅላት ውስጥ ውሃ መቋጠር ወይም ሀይድሮሴፋለስ ችግር ያጋጥማቸዋል ተባለ፡፡
ጥር 28/2018 በኢትዮጵያ ከሚወለዱ 10,000 ህፃናት ውስጥ 80 የሚሆኑት የነርቭ ዘንግ ክፍተትና የጭንቅላት ውስጥ ውሃ መቋጠር ወይም ሀይድሮሴፋለስ ችግር ያጋጥማቸዋል ተባለ፡፡ ችግሩ በሀገሪቱ የሚገባውን ያህል ትኩረት ያልተሰጠው በመሆኑ በማህበረሰብ ላይ የሚያደርሰው ጫና ከፍተኛ ነው ተብሏል፡፡ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊንየም የህክምና ኮሌጅ የህጻናት የነርቭ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ሐኪም የሆኑት ዶክተር ሱራፌል መኮንን ስለ ህመሞቹ ይህንን ያስረዳሉ፡፡ ስፓይና ቢፊዳ ( #Spina_Bifida ) ማለት ከነርቨ ዘንግ የአፈጣጠር ችግሮች ውስጥ አንዱ ሲሆን የአከርካሪ አጥንትና የህብለሰረሰር በአግባቡ አለመዘጋት (ክፍተት) ነው። በአብዛኛው ጊዜ ስፓይና በፊዳ ያለባቸው ሕጻናት ፈሳሽ በአጎላቸው ወስጥ ስለሚከማች ሃይደሮ ሴፋለስም ያጋጥማ
Feb 52 min read


ስፖኪዮ ወይንም የጎን መስታወት የሌላቸው ፣ መብራታቸው የማይሰራና ሌሎችም በቀላሉ የሚታይ ጉድለት ያለባቸው ተሽከርካሪዎች በጎዳናው ይታያሉ፡፡
ጥር 28/2018 ስፖኪዮ ወይንም የጎን መስታወት የሌላቸው ፣ መብራታቸው የማይሰራና ሌሎችም በቀላሉ የሚታይ ጉድለት ያለባቸው ተሽከርካሪዎች በጎዳናው ይታያሉ፡፡ እንዲህ ዓይነቱና ሌሎች ጉድለቶችን ለማወቅ ደግሞ አመታዊ የቴክኒክ ምዘና ማድረግ አስገዳጅ ነው፡፡ ታዲያ በቀላሉ ጉድለታቸው የሚታዩ ተሽከርካሪዎች ይህንን ምርመራ እንዴት እያለፉት ነው በጎዳናው የሚታዩት? አሮጌ ተሽከርካሪዎች ከጎዳና እንዲወጡ ይደረጋል በሚል በከተማው የሚወራው ወሬስ ምን ያክል እውነትነት ያለው ይሆን፤የታሰበ ነገርስ ይኖር ይሆን? ሙሉ ዘግጅቱን ለማድመጥ….. ቴዎድሮስ ወርቁ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Feb 51 min read


ለሀገር ውስጥ ፍጆታ እየቀረበ ካለው መድሃኒት ከ40 በመቶ በላዩ በሃገር ቤት የተመረተ መሆኑ ተነገረ፡፡
ጥር 27/2018 ለሀገር ውስጥ ፍጆታ እየቀረበ ካለው መድሃኒት ከ40 በመቶ በላዩ በሃገር ቤት የተመረተ መሆኑ ተነገረ፡፡ በ5 ዓመታት ጊዜ ውስጥም የፍጆታውን ከ1/3ኛ ወይም ከ60 በመቶ በላዩን መድሃኒት በሃገር ቤት ማምረት እንደሚቻልም ከጤና ሚኒስቴር ሰምተናል፡፡ በኢትዮጵያ ለህክምና ግልጋሎት የሚውሉ መድሃኒቶችንና የህክምና ግብዓቶችን ከውጭ በማስገባት የሃገር ውስጡ ፍላጎት እንደሚሸፈን ይታወቃል፡፡ ለረጅም ዓመታት የሃገር ውስጥ የመድሃኒት አምራቾች ድርሻ ከ8 እስከ 10 በመቶ ሳይበልጥ እንደቆየ በጤና ሚኒስቴር የድንገተኛ ህክምና የመድሃኒቶችና ግብዓቶች አቅርቦት አማካሪ የሆኑት አቶ መሃመድ አማን ጀማል ነግረውናል፡፡ የመንግስቱን ጨምሮ በሃገር ውስጥ ያሉ 12 የግል የህክምና መሳሪያና መድኃኒት አምራች ፋብሪካዎች የኢትዮጵያን 40 በመ
Feb 41 min read


ጥር 27/2018 – የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ሱዳን የሱዳን ወታደራዊ መንግስት እና የአገሪቱ ጦር የበላይ ጄኔራል አብዱልፈታህ አል ቡርሃን የአገሪቱ ጦር የደቡብ ኮርዶፋኗን ዋና ከተማ ካዱግሊን ከተቀሩት ክፍሎች ጋር የሚያገናኘውን አውራ ጎዳና በእጁ ማስገባቱን ተናገሩ፡፡ ጦሩ የRSF ፈጥኖ ደራሽ ሀይል በካዱግሊ ፈጥሮት የነበረውን ከበባ ጥሶ እንደወጣ አል ቡርሃን መናገራቸውን አልጀዚራ ፅፏል፡፡ አብዱልፈታህ አልቡርሃን የደቡብ ኮርዳፋኗን ከተማ ከተቀሩት የአገሪቱ ክፍሎች ጋር የሚያገናኘውን አውራ ጎዳና ተቆጣጥረነዋል ያሉት በኦምዱርማን በሚገኘው የአገሪቱ ዋና የቴሌቪዥን ጣቢያ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ነው ተብሏል፡፡ ጄኔራል አል ቡርሃን ከRSF ጋር በጭራሽ የተኩስ አቁም አናደርግም ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ የአገሪቱ ወታደራዊ መሪ የተኩስ አቁም RSF መልሶ እንዲያንሰራራ ስለሚያደርገው
Feb 42 min read


የሩሲያ የውጭ የስለላ ተቋማት SVR የፈረንሳዩ ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የማይፈልጓቸውን የአፍሪካ መሪዎችን የማስገደል ሙከራ አድርገዋል ሲል ከሰሰ፡፡
ጥር 26/2018 – የውጪ ሀገራት ወሬዎች # ሩሲያ የሩሲያ የውጭ የስለላ ተቋማት SVR የፈረንሳዩ ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የማይፈልጓቸውን የአፍሪካ መሪዎችን የማስገደል ሙከራ አድርገዋል ሲል ከሰሰ፡፡ SVR ማክሮን ዘመናዊውን የእጅ አዙር ቅን አገዛዝ አሻፈረን ያሏቸውን እና በራሳቸው ለመቆም እየጣሩ ያሉ አገሮችን መሪዎች ለማስገደል ትዕዛዝ ሰጥተዋል ማለቱን አናዶሉ ጽፏል፡፡ ከወር በፊት በቡርኪናፋሶ ተደርጎ ነበር ያለውን የመንግስት ግልበጣ ሙከራ በምሳሌነት አንስቷል የውጭ የስለላ ድርጅቱ፡፡ ውስጥኑ በፀረ ቅኝ አገዛዝ አቋማቸው የሚታወቁትን የቡርኪናፋሶው መሪ ሻምበል ኢብራሂም ትራኦሬን ለማስገደል ጭምር የተዶለተ ነበር ማለቱ ተጠቅሷል፡፡ ቡርኪናፋሶ ፣ ማሊ እና ኒጀር የፈረንሳይ የጦር ትብብር አያሻንም ያሉ አገሮች ናቸው፡፡ የፈረንሳይን ወታደሮችም ከ
Feb 32 min read


ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በሰሜኑ ጦርነት የኤርትራ ሰራዊት በትግራይ ወጣቶችን መጨፍጨፍና ኢንዱስትሪዎችን መዝረፉን እንዲቆም ኢትዮጵያ መንግስት 2 ጊዜ ወደ ኤርትራ ልዑክ ልኮ እንደነበር ይፋ አደረጉ፡፡
ጥር 26/2018 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሰሜኑ ጦርነት የኤርትራ ሰራዊት በትግራይ ክልል ወጣቶችን መጨፍጨፍ እና ኢንዱስትሪዎችን መዝረፉን እንዲቆም ኢትዮጵያ መንግስት ሁለት ጊዜ ወደ ኤርትራ ልዑክ ልኮ እንደነበር ይፋ አደረጉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ይህን ይፋ ያድጉት ዛሬ በፓርላማ በነበራቸው ቆይታ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንዳንድ ሰዎች በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ችግር የተፈጠረው የኢትዮጵያ መንግስት የቀይ ባህር ጥያቄ ስላነሳ ነው ብለው ያስባሉ ፣ ይተነትናሉ ግን አይደለም ብለዋል። ጸቡ የተጀመረው የቀይ ባህር ጉዳይ ሲመጣ አይደለም ፤"በትግራይ ውጊያ ሲጀመር የመጀመሪያ ዙር ውጊያ ሽሬን ካስለቀቅን በኋላ የኤርትራ ጦር ከኋላ ኋላ ተከትሎ ሽረ ገብቶ የግለሰቦችን ቤት ማፍረስ ሲጀምር ጸብ ተጀምሯል ፣አክሱም ገብተን ስናልፍ
Feb 31 min read


ዘንድሮ በሚካሄደው ሰባተኛ ሀገራዊ ምርጫ የተፎካካሪ ፓርቲዎች የተሻለ ድምፅ በፓርላማው እንዲኖራቸው እንደሚፈልጉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ።
ጥር 26/2018 ዘንድሮ በሚካሄደው ሰባተኛ ሀገራዊ ምርጫ የተፎካካሪ ፓርቲዎች የተሻለ ድምፅ በፓርላማው እንዲኖራቸው እንደሚፈልጉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ። መንግስት ስራውን ትቶ በምርጫ ስራ ላይ አተኩሯል በሚል ለቀረበው ጥያቄ ጠቅላይ ሚንስትሩ ሲመልሱ ብልፅግና ፓርቲ ምርጫው ላይ አተኩራችሁ እየሰራችሁ አይደለም ዋና ትኩረታችን በመንግስት ስራ ላይ ነው እያሉን ነው ብለዋል። ከምርጫ ቅስቀሳ ጋር በተያያዘ ወጣቱን ለመድረስ አሁን ያሉ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም የተሻለ ነው የህዝብ መገናኛ ብዙሃን ለሁሉም እኩል ተደራሽ እንዲሆን እንሰራለን ብለዋል ጠቅላይ ሚንስትሩ። ከፀጥታ ጋር በተያያዘ ለምርጫው ስጋት ነው ተብሎ ለተነሳው ጥያቄ ሲመልሱ ባለፉት 6 ወራት በተደረጉ የአደባባይ በዓላት ምንም ችግር ሳይፈጠር ተጠናቋል ታዲያ ምርጫው ሲደረ
Feb 31 min read


በተለይ የወልቃይት ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እየተመለሱ ያልሆነው ተፈናቃይን መያዣ ያደረገ ፖለቲካ በመኖሩ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር ተናገሩ፡፡
ጥር 26/2018 በተለይ የወልቃይት ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እየተመለሱ ያልሆነው ተፈናቃይን መያዣ ያደረገ ፖለቲካ በመኖሩ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር ተናገሩ፡፡ በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ተፈናቅለው ወደ ትግራይ ሂደው የነበሩ የኤሊባቡር እና ራያ አካባቢ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው ተመልሰው በሰላም እየኖሩ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ይሁንና የወልቃይት ተፈናቃዮችን የመመለሱ ነገር አስቸጋሪ ሁኔታ እንደገጠመው ተናግረዋል፡፡ በወልቃይት ጉዳይ በትግራይና አማራ ክልል መካከል ለረዥም ጊዜ የይገባኛል ጥያቄ መኖሩን ለዚህም የፌዴራል መንግስቱ ተፈናቃዮች ተመልሰው በሪፈንደንም ራሱ ነዋሪው ውሳኔ እንዲሰጥ አቋም መያዙን አንስተዋል፡፡ ተፈናቃዮቹም ለመመለስ፣ የተፈናቀሉበት አካባቢም ለመቀበል ዝግጁ ቢሆኑም ተፈናቃይን እንደመያዣ የሚጠቀም ፣ ስቃይ ዘርቶ እገዛ ከሌ
Feb 31 min read


ከዚህ ቀደም በዶላር ተገዝቶ ወደ ሃገር ሲገባ የነበረና 3.4 ቢሊዮን ብር የሚያወጣ የኢንዱስትሪ ምርት በሃገር ውስጥ ምርት መተካቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተናገሩ፡፡
ጥር 26/2018 ከዚህ ቀደም በዶላር ተገዝቶ ወደ ሃገር ሲገባ የነበረና 3.4 ቢሊዮን ብር የሚያወጣ የኢንዱስትሪ ምርት በሃገር ውስጥ ምርት መተካቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተናገሩ፡፡ ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ሴራሚክ ሙሉ በሙሉ በሃገር ቤት ማምረት ጀምሯልም ብለዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት በፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው። ከፓርላማ አባላት ከተነሱላቸው ጥያቄዎች መካከል አንዱ 27 በመቶ የደረሰውን የሃገሪቱን ስራ የሌለው ወጣት ወደ ስራ ለማስገባት እንደ መፍትሄ ከሚቀመጡ ሃሳቦች መካከል አንዱ የሆነው የኢንዱስትሪውን ዘርፍ ማስፋት ነው፤ በርካታ ሰዎችን ሊያሰማሩ የሚችሉ አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች የሉም፤ ያሉትም አቅማ
Feb 32 min read


መሬት በኢትዮጵያ ትልቅ የገቢ ምንጭ እና የፖለቲካ ስርዓቱም ዋነኛ ትኩረት ቢሆንም እስከዛሬም ያልተፈታ አስተዳደራዊ ችግር እንዳለበት ይነገራል፡፡
ጥር 26/2018 መሬት በኢትዮጵያ ትልቅ የገቢ ምንጭ እና የፖለቲካ ስርዓቱም ዋነኛ ትኩረት ቢሆንም እስከዛሬም ያልተፈታ አስተዳደራዊ ችግር እንዳለበት ይነገራል፡፡ ይህም ሃገር ማግኘት ያለባትን ሃብት እንዳታገኝ ከማድረጉም በላይ ለሙስናና የዕርስ በዕርስ ግጭት መነሻ መሆኑን ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡ በሃዋሳ ዩንቨርሲቲ የመሬት የህግ ጉዳዮች ተመራማሪ የሆኑት ዳንኤል በኃይሉ (ዶ/ር) መሬትን የሚያህል ሃብት በሚኒስቴር መስሪቤት የሌለው መሆኑ አንዱ የአስተዳደር ስርዓት ክፍተት ነው ይላሉ፡፡ ባለሙያው ኢትዮጵያ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን ባለማስተካከሏ ብቻ በብዙ ቢሊየን ገንዘብ እንዳጣች ያነሳሉ፡፡ ለዚህም ባለሙያው የሩዋንዳን ተሞክሮ የጠቀሱ ሲሆን ከኢትዮጵያ ከ30 በመቶ በታች የመሬት ይዞታ ያላት ሩዋንዳ የአስተዳደር ስርዓቷን በማስተካከል
Feb 31 min read


ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ባንኮች ከአጠቃላይ ኢኮኖሚው ያላቸው ድርሻ ከ5 እስከ 7 በመቶ ነው ተባለ፡፡
ጥር 26/2018 ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ባንኮች ከአጠቃላይ ኢኮኖሚው ያላቸው ድርሻ ከ5 እስከ 7 በመቶ ነው ተባለ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በጎረቤት ሀገራት ባንኮች ለሀገራቸው ጠቅላላ ኢኮኖሚ ያላቸው ድርሻ ከዚህ ይበልጣል ለዚህም ምንክያቱ ባንኮቹ አቅማቸው ስለደረጀና የውጪ ባንኮች ስለገቡ ነው ብለዋል፡፡ ባለፉት 30 ዓመታት የኢትዮጵያ ባንኮች ያለውም ውድድር እንዲሰሩ ቢደረግም የታሰበውን ያህል ሀብት መፍጠር አልቻሉም ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ባንኮችም አቅማቸው ማደርጀት አለባቸው ያሉ ሲሆን የውጪ ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ መግባት አለባቸው ብለዋል፡፡ ከውጪ የሚመጡ ባንኮች አጠቃላይ መያዝ የሚችሉት 49 በመቶ ድርሻ ብቻ ነው 5 ለውጪ ባንኮች የሚሠጥ ፍቃድ በ5 አመት ውስጥ የሚካሄድ ነው ሲሉም አስረድተዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ባንኮች
Feb 31 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

