top of page
የመንግስት ግዥ አገልግሎት በዘንድሮው በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት በሽያጭ ከተወገዱ ተሽከርካሪዎች እና ሌሎች ንብረቶች የተገኘ ወደ 323 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ለመንግስት ገቢ አድርጌያለሁ አለ፡፡
ግንቦት 17/2018 የመንግስት ግዥ አገልግሎት በዘንድሮው በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት በሽያጭ ከተወገዱ ተሽከርካሪዎች እና ሌሎች ንብረቶች የተገኘ ወደ 323 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ለመንግስት ገቢ አድርጌያለሁ አለ፡፡ አገልግሎቱ ይህን ያህል ገንዘብ ዘጠኝ ወራት ውስጥ ለመንግስት ገቢ ሲያደርግ በታሪኩ የአሁኑ የጀመሪያው እንደሆነ ነግሮናል፡፡ የመንግስት ግዥ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት በሽያጭ ከተወገዱ ተሽከርካሪዎች እና ሌሎች ንብረቶች ከ322 ሚሊየን ብር በላይ ለመንግስት ገቢ ማድረጉን ተናገረ፡፡ አገልግሎቱ የ90 መስሪያ ቤቶችን 271 ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን እና ልዩ ልዩ ንብረቶችን በሽያጭ በማስወገድ ለመንግስት ገቢ የሆነ ገንዘብ እንደሆነ ተጠቅሷ ። በሽያጭ ከተወገዱ ተሽከርካሪዎች እና ሌ
May 251 min read


ከአንድ ሚሊየን በላይ ኢትዮጵያዊያን በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት በተለያዩ ስራዎች ተሰማርተው እንደሚገኙ ይነገራል።
ግንቦት 17/2018 የእቃ አስተላላፊነት ዘርፍን ለውጪ ባለሀብቶች ሙሉ በሙሉ ክፍት አንዲሆን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ ወሰነ፡፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ ዛሬ ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ የእቃ አስተላላፊነት ዘርፍን ለውጭ ባለሃብቶች ተሳትፎ ክፍት ለማድረግ ውሳኔ ማሳለፉ ተሰምቷል፡፡ ቀደም ሲል የውጭ ባለሀብቶች የዕቃ አስተላላፊነት የኢንቨስትመንት ተሳትፎ ለአገር ውስጥና ለውጭ ባለሃብቶች የቅንጅት ኢንቨስትመንት የተከለለ ሲሆን የውጭ ባለሃብቶች የካፒታል የሽርክና ተሳትፎም በ49 በመቶ ተገድቦ መቆየቱ ተነስቷል። ከዚህም የተነሳ በዘርፉ የሚፈለገውን አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፍሰት ላይ ክፍተት ፈጥሮ የቆየ ሲሆን የቦርዱ ውሳኔም ይህን እና መሰል ችግሮችን የሚቀርፍ እንደሚሆን ይጠበቃል ተብሏል፡፡ በዘርፉ የተሰማሩ ነባር ባለሃብ
May 251 min read


ከአንድ ሚሊየን በላይ ኢትዮጵያዊያን በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት በተለያዩ ስራዎች ተሰማርተው እንደሚገኙ ይነገራል።
ግንቦት 17/2018 ከአንድ ሚሊየን በላይ ኢትዮጵያዊያን በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት በተለያዩ ስራዎች ተሰማርተው እንደሚገኙ ይነገራል። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውን እና ትውልደ ኢትዮጵያውን ወደ ሀገር ቤት ከሚልኩት የውጭ ምንዛሪም 40 በመቶው የእነሱ ድርሻ መሆኑ ይጠቀሳል። አሜሪካና እስራኤል ከኢራን ጋር የገቡትን ጦርነት ተከትሎ በተቀየረው የአካባቢው የሠላም ሁኔታ ምክንያት ግን እነዚህ ኢትዮጵያውን ወደ ሀገር ቤት የሚልኩት የውጭ ምንዛሪ ተፅዕኖ አርፎበታል ተብሏል። የሠላም ችግሩ ስራቸውን እንዲያጡ ያደረጋቸው ኢትዮጵያውን ብዙ መሆናቸውንም ሠምተናል። ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ምንታምር ፀጋው
May 251 min read
የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን የገንዘብ ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል፡፡
ግንቦት 17/2018 የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን የገንዘብ ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል፡፡ ከመካከሉ ከ33 ቢሊዮን ዶላር በላዩ የውጭ እዳ ሲሆን 18.3 ቢሊዮን ዶላሩ ደግሞ ከሃገር ውስጥ የተወሰደ ብድር ነው፡፡ ለመሆኑ የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር ከሌሎች አገራት አንፃር ሲታይ ከፍተኛ ፣ መካከለኛ ወይስ ዝቅተኛ ? ሀገሪቱ አሁን ያለችበት የኢኮኖሚ አቅምስ ያለባትን እዳ ለመክፈል የሚያስችላት ይሆን? የምጣኔ ሃብት በለሞያ የሆኑት አቶ ክቡር ገና የኢትዮጵያ እዳ ከሌሎች አገራት ጋር ሲተያይ ከፍተኛ የሚባል እንዳልሆነ ጠቅሰው የመክፈል አቅሟ ግን "በጣም ደካማ ስለሆነ ጫናው በጣም ከፍ ብሎ ይታያል፣ ለመክፈልም አስቸጋሪ ነው ይላሉ፡፡ የአገር ውስጥ እዳው በኢትዮጵያ ብር ሲመለስ ወደ 3 ትሪሊዮን እንደሚሆን እንዲሁም የውጭ ብድሩ ደግሞ
May 251 min read


ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ስደተኞችን ኑሮ ለማሻሻል እና ተቀባይ ማህበረሰብን ይጠቅማል የተባለ የግብርና መስኖ ፕሮጀክት
ግንቦት 14/2018 ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ስደተኞችን ኑሮ ለማሻሻል እና ተቀባይ ማህበረሰብን ይጠቅማል የተባለ የግብርና መስኖ ፕሮጀክት ለማስጀመር ኢትዮጵያ በአለም አቀፍ ደረጃ ቃል ገብታ ነበር፡፡ ይሁንና ከአለም አቀፍ ረጂ ድርጅቶች የሚቀርበው ድጋፍ በመቀዛቀዙ ለማልማት ከታሰበው 10000 ሄክታር መሬት አሁን ላይ 1200 ሄክታር መሬት ብቻ እንደለማ ሰምተናል፡፡ በስደተኞችና ተመላሽ አገልግሎት የስደተኞች ስራ ፈጠራና የኑሮ ማሻሻያ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ አንተነህ መካሻ በአለም አቀፍ የስደተኞች ፎረም ላይ ከ3 አመት በፊት መንግስት የገባውን ቃል ለመፈፀም በማሰብ 2ሺ 500 ሀኬታር መሬት በመስኖ የሚለማ አዘጋጅቶ ነበር ይላሉ፡፡ አሁን ላይ 1200 ሄክታር የሚሆነው የተዘጋጀው መሬት ብቻ ነው እስካሁን የለማው ከዚህ በላይ እንዳይሄድ አለም አቀፍ የሚቀ
May 221 min read


ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰናዳ ነው የተባለ ሀገር አቀፍ የሰብል ጥበቃና የአፈር የማዳበሪያ ኤክስፖ በኤግዚቢሽን ማዕከል ተከፈተ።
ግንቦት 14/2018 ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰናዳ ነው የተባለ ሀገር አቀፍ የሰብል ጥበቃና የአፈር የማዳበሪያ ኤክስፖ በኤግዚቢሽን ማዕከል ተከፈተ። ኤክስፖው አስመጭዎችን፣ አከፋፋዮችን፣ ተጠቃሚዎችን በቀጥታ የሚያገናኝ እና የገበያ ትስስርን የሚፈጥር ይሆናል ተብሎ ታምኖበታል። የኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሰብል በሽታ፣ ተባይ፣ የአፈር ለምነት ችግር፣ የቴክኖሎጂ እጥረቶች እና ሌሎች ችግሮችን እያስተናገደ መሆኑ ተነግሯል። ይህንን ችግር ለመቋቋም የሚያስችል እና ዘርፉ ያሉበትን ችግሮችን ለመፍታት ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት የሚቆየው ኤክስፖ የራሱ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሎ ታምኖበታል። ዝግጅቱን ዊ ሊንክ የተባለ ድርጅት ከግብርና ሚኒስቴር እና ከሌሎች የመንግስት እና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በመተባበር እንዳሰናዳው ተነግሯል። የሰብል በሽታ
May 221 min read


የኤም ኤስ አይ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ቁጥር የነበረውን የእናቶችና ጨቅላ ህፃናት ሞት እንዲቀንስ ከፍተኛ አስተዋፆ ማድረጉን ተናገረ፡፡
ግንቦት 14/2018 በኢትዮጵያ ከ35 ዓመታት በፊት ጀምሮ የስነ ተዋለዶ፣የ እናቶችና ህጻናት ጤና አግልጎሎቶችን ሲሰጥ የቆየው የኤም ኤስ አይ ኢትዮጵያ (MSI) ከፍተኛ ቁጥር የነበረውን የእናቶችና ጨቅላ ህፃናት ሞት እንዲቀንስ ከፍተኛ አስተዋፆ ማድረጉን ተናገረ፡፡ ድርጅቱ ባለፉት 10 ዓመታት በተለይ በዓመት በአማካይ ለ2,000 ሰዎች አገልግሎቱን ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሷል፡፡ በሰጣቸው የስነ ተዋለዶ፣ የእናቶችና ህጻናት ጤና አገልግሎቶች የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር አንዲያድግ አንዲሁም የእናቶችና የጨቅላ ህጻናት ሞት አንዲቀንስ ከፍተኛ አስተዋጾ ማበርከቱን የኤም ኤስ አይ ኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተሩ አበበ ሽብሩ (ዶ/ር) ነግረውናል፡፡ በዚህም ለምሳሌ ባለፈው ዓመት ብቻ ከወሊድ ጋር በተያያዘ 1000 እናቶችን ከሞት ታድገናል ብለዋል፡፡ 30
May 222 min read


የደቡብ አፍሪካ መንግስት በኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰውን ጉዳት መርምሮ ውጤቱን በቅርብ ይፋ እንደሚደረግ ቃል መግባቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ።
ግንቦት 13/2018 የደቡብ አፍሪካ መንግስት በኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰውን ጉዳት መርምሮ ውጤቱን በቅርብ ይፋ እንደሚደረግ ቃል መግባቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ። ለተፈጠረው ችግር መፍትሄ የሚያፈላልግ ልዑክ ወደ ስፍራው በቅርብ እንደሚያቀና ሚኒስቴሩ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ተናግሯል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው በሳምንቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን አካቷል፡፡ መግለጫውን የሰጡት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ናቸው። ቃል አቀባዩ በቅርቡ የተከናወኑ ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ እንቅስቃሴን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በቅርቡ በህንድ በተካሄደው የብሪክስ አባላት የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ በደቡብ አፍሪካ ጥቃት ስለደረሰባቸው ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ ከአቻችው ጋር መወያ
May 211 min read


የፖለቲካ ፓርቲዎች የህዝቡን ሰላም ከሚያውኩ ቅስቀሳዎች እንዲርቁ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አሳሰበ።
ግንቦት 13/2018 የፖለቲካ ፓርቲዎች የህዝቡን ሰላም ከሚያውኩ ቅስቀሳዎች እንዲርቁ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አሳሰበ። ከ10 ቀናት በኋላ የሚካሄደው ሃገር አቀፍ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ሃገራዊ ሰላምን ለማፅናት በሚል የፊታችን እሁድ የአደባባይ የፀሎት እንደሚደረግ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ተናግሯል። የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ጠባቂ አባቶች በወሰኑት መሰረት የፊታችን እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ፒያሳ አካባቢ በሚገኘው አራዳ ፓርክ ሃገር አቀፍ የፀሎት መርሃ ግብር መሰናዳቱን የጉባኤው ጠቅላይ ፀሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ በጉዳዩ ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ዛሬ በሰጡት መግለጫ ጠቅሰዋል። ቀሲስ ታጋይ የፀሎት መርሃ ግብሩን አላማዎች ሲጠቅሱም በሃገር ውስጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ለማገዝ ምዕመናን ሃላፊነ
May 211 min read


አቢሲንያ ባንክ የ5ተኛ ዙር የ“እችላለሁ” እና የ“ይጀምሩ፣ ያድሱ፣ ይደጉ-2” የሽያጭ ዘመቻ የሽልማትና መዝጊያ ሥነ-ሥርዓት አከናወነ።
ግንቦት 13/2018 አቢሲንያ ባንክ የ5ተኛ ዙር የ“እችላለሁ” እና የ“ይጀምሩ፣ ያድሱ፣ ይደጉ-2” የሽያጭ ዘመቻ የሽልማትና መዝጊያ ሥነ-ሥርዓት አከናወነ። ባንኩ አዘጋጅቶ የነበረው የሽያጭ ዘመቻ አዳዲስ ደንበኞች ከባንኩ ጋር ሥራ እንዲጀምሩ እና ነባር አነስተኛ ተቀማጭ ያላቸውና በንቃት የማያንቀሳቀሱ ደንበኞች ግንኙነታቸውን እንዲያድሱ እንዲሁም ሁሉም ደንበኞች ከባንኩ ጋር አብረው ይደጉ በሚል መሪ ቃል ለሁለተኛ ጊዜ ያካሄድኩት ነው ብሏል። በዚህም አንድ ዕድለኛን የመኪና ባለቤት ያደረገ ሲሆን በየሁለት ሳምንቱ ደግሞ ሌሎች በርካታ የሽልማት ዓይነቶችን በመሸለም አጠናቋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8)ን በማስመልከት ባንኩ ለ5ኛ ጊዜ “እችላለሁ" በሚል ከመጋቢት 8 እስከ ሚያዝያ 23 ቀን 2026 ዓ/ም የቆየ ልዩ ሴቶችን የሚያበረታታ መ
May 211 min read


በኤልኒኖ ምክንያት ሊከሰት ይችላል የተባለውን የድርቅ ስጋት
ግንቦት 13/2018 መጪው ክረምት በኤልኒኖ ምክንያት ሊከሰት ይችላል የተባለውን የድርቅ ስጋት የሚመለከታቸው ተቋማት ለገበሬው እና ሌላም ጉዳዩ ለሚያገባቸው መረጃውን እንዲያደርሱ ማሳሰቢያ ተሰጥቷቸዋል፡፡ መረጃውን ከማድረስ ባሻገር አስፈላጊው ቅድመ ጥንቃቄ ሳያደርጉ ቀርተው ጉዳት ከተከሰተ ተጠያቂ የሚሆኑበት አሰራር መዘርጋቱን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (IGAD) ተናግሯል፡፡ የዘንድሮው የክረምት ዝናብ ጥሩ አጀማመር ቢኖረውም በነሃሴ እና መስከረም ወራቶች ግን ደረቅ ሰሞናት ሊበዙ ፤ የዝናብ መዋዠቅ እና መቆራረጥም ሊታይ እንደሚችል የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሊጂ ኢንስቲትዩት ከሠሞኑ ይፋ ባደረገው ትንበያው ማሳወቁ ይታወሳል። ይኖራል ተብሎ የተተነበየው ደከም ያለ የኤልኒኖ ክስተት በነሃሴ እና መስከረም ወራቶች ደረቅ ሰሞናት እንዲበዙ ፤ ብሎም የዝ
May 211 min read


ባህላዊው ህክምና በሚፈለገው ልክ ከዘመናዊው ጋር ተስማምቶ መቀጠል የማይችለው ለምንድን ነው?
ግንቦት 13/2018 እንደነ ቻይና እና ህንድ ባሉት ሀገሮች ፈዋሽነት ያላቸው እፅዋትን በመድሃኒትነት መጠቀም የተለመደ ነው፡፡ በኢትዮጵያ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተለያዩ እፅዋትን በመድሃኒትነት ፈጭታችሁ አፍልታችሁ ተጠቀሙ የሚሉ መልክቶች በተለይ በማህበራዊ ሚዲያ በስፋት ይታያል፡፡ ግን አወሳሰድን የጎንዮሽ ጉዳትና ሌላውንም እንዴት ማወቅ ይቻላል? ጠቃሚውን ከጎጂው መለየት የሚቻለውስ እንዴት ነው? ባህላዊው ህክምና በሚፈለገው ልክ ከዘመናዊው ጋር ተስማምቶ መቀጠል የማይችለው ለምንድን ነው? ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ፍቅሩ አምባቸው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68a
May 211 min read
ፋሽስት ኢጣሊያ ፣ በደብረ ሊባኖስ ገዳም የሚገኙ 300 መነኮሳትና ዲያቆናት በመደዳ በጥይት ያስደበደባቸው፣ በ1929 ዓ.ም በዛሬው ቀን ነበር፡፡
#ታሪክን_የኋሊት ፋሽስት ኢጣሊያ ፣ በደብረ ሊባኖስ ገዳም የሚገኙ 300 መነኮሳትና ዲያቆናት በመደዳ በጥይት ያስደበደባቸው፣ በ1929 ዓ.ም በዛሬው ቀን ነበር፡፡ መነኮሳቱና ዲያቆናቱ እንዲገደሉ ትዕዛዝ የሰጠው ጀኔራል ሮዶልፎ ግራዚያኒ ነበር፡፡ ጀኔራል ግራዚያኒ የኢጣሊያ የምስራቅ ዕዝ አዛዥና በኋላም የኢትዮጵያ የቅኝ ግዛት ገዥ በነበረበት ጊዜ ሁሉ፣ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና መነኮሳት ላይ የተለየ ጥላቻ ነበረው፡፡ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናት፣ ኢትዮጵያ እንዳትገዛልን የሚያወግዙ፣ ስለነፃነት የሚሰብኩ፣ አርበኞችን የሚደግፉ ናቸው ፤ የሚል እምነት ስለነበረው ቤተ ክርስቲያኗን ለመበተን ይመኝ ነበር፡፡ የካቲት 12፣ አብርሃም ደቦጭ በቦምብ ካቆሰለው በኋላ ፣ሚስቱን ደብረ ሊባኖስ ገዳም መደበቁን ሰማ፡፡ ይኽም በካህናት መ
May 202 min read


በምርጫ ወቅት "በታንዛኒያ እና በዩጋንዳ "ላይ የተስተዋለው የኢንተርኔት ገደብ ወይም እቀባ በኢትዮጵያ እንዳይኖር የአፍሪካ ህብረትን ጨምሮ ሌሎች ተቋማት ምክረ ሃሳብ ማቅረባቸውን ተናገሩ።
ግንቦት 12/2018 በምርጫ ወቅት "በታንዛኒያ እና በዩጋንዳ "ላይ የተስተዋለው የኢንተርኔት ገደብ ወይም እቀባ በኢትዮጵያ እንዳይኖር የአፍሪካ ህብረትን ጨምሮ ሌሎች ተቋማት ምክረ ሃሳብ ማቅረባቸውን ተናገሩ። የአፍሪካ ህብረት ምርጫውን ለመታዘብ በቂ ዝግጅት ማድረጉን እና የምርጮ ቦርድ ውሳኔን በመጠበቅ ላይ እንደሚገኝ አስረድቷል። ይህ የተነገረው ግንቦት 10 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ህብረት ፓራዳይም ኢንሼቲቭ ከተሰኘ መንግስታዊ ካለሆነ ተቋም ጋር በመሆን በዲጂታል መብት ላይ ባሰናዳው ወይይት ላይ ነው። በራዲሰን ብሉ (Radison blue) ሆቴል በተካሄደው ውይይቱ ላይ የአፍሪካ ህብረት፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት የሳይንስ የባህል ተቋም ዩኔስኮ ፣ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ፣ የኢትዮ ቴሌኮም
May 202 min read


በኢትዮጵያ በተደረገ የዳሰሳ ጥናት ከአጠላቃይ ህዝቡ 17.3 በመቶው በደም ግፊት ህመም ተጠቂ ሆኖ መገኘቱን የጤና ሚኒስቴር ተናገረ፡፡
ግንቦት 12/2018 በኢትዮጵያ በተደረገ የዳሰሳ ጥናት ከአጠላቃይ ህዝቡ 17.3 በመቶው በደም ግፊት ህመም ተጠቂ ሆኖ መገኘቱን የጤና ሚኒስቴር ተናገረ፡፡ በዳሰሳው የማህበረሰቡ የጨው አጠቃቀም ከፍ ብሎ ታይቷል፤ ከእንቅስቃሴ የተገደበ አኗኗር እየተለመደ መምጣቱ ችግሩን እንዳያባብሰው ስጋት ፈጥሯል መባሉንም ሰምተናል፡፡ በኢትዮጵያ ከሰው ወደ ሰው የማይተላለፉ በሽታዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ ማህበረሰቡን የማትቃት መጠናቸው እየጨመረ መጥቶ 50 በመቶ የሞት መንስኤዎች መሆናቸውን የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡ በሚኒስቴሩ የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ዶክተር ህይወት ሰለሞን ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መግቢያ በር ነው የሚባለው የደም ግፊት ህመም ቁጥሩ እየጨመረ መምጣቱን በቅርቡ ያደረግነው የዳሰሳ ጥናት አሳይቶናል ብለውናል፡፡ በዚህም ዳሰ
May 202 min read


የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት (ካውንስል) ኢትዮጵያዊያን ላይ ጥሎት የነበረውን የቪዛ ገደብ ማንሳቱን ተናገረ፡፡
ግንቦት 12/2018 ከሁለት ዓመት በፊት የቪዛ ገደብ የተጣለው የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ ወደ አውሮፓ ህብረት ሀገራት ውስጥ የገቡ ዜጎቹን መልሶ የመቀበል ትብብሩንን እንዲያሻሽል ግፊት ለማድረግ ነበር፡፡ በክልከላው የዲፕሎማት እና አገልግሎት ፓስፖርት ያላቸው ኢትዮጵያዊያን ያለ ክፍያ #ቪዛ እንዲሰጣቸው አይደረግም፣ ኢትዮጵያዊያን ቪዛ ለማግኘት የሚጠብቁት ጊዜ ከ15 የሥራ ቀናት ወደ 45 የሥራ ቀናት ከፍ እንዲል ያደረገ ነበር፡፡ የህብረቱ ኮሚሽን አደረኩት ባለው አዲስ ግምገማ መሠረት የኢትዮጵያ መንግሥት በህገ ወጥ መንገድ ወደ ህብረቱ አባል ሀገራት የሚገቡ ዜጎችን ለመቀበል በለተለይ ደግሞ የአደጋ ጊዜ የጉዞ ሰነዶችን መስጠት በኩል በከፍተኛ ሁኔታ መሻሻሎች መኖራቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡ በዚህም በኢትዮጵያዊያን ላይ ጥሎት የነበረውን የቪ
May 201 min read


በታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ከፍተኛ ትችት ከባለሞያዎች ቀረበበት።
ግንቦት 12/2018 በታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ግብር ከፋይዮች አንዴ የተወሰነባቸውን ግብር መጠን ተገቢ እንዳልሆነ የሚያስረዳ አዲስ ማስረጃ እንዳያቀርቡ መከልከሉ ከፍተኛ ትችት ከባለሞያዎች ቀረበበት። የገንዘብ ሚኒስቴር በበኩሉ አዲስ ማስረጃ ማቅረብ ሙሉ በሙሉ አልተከለከልም፣ የሚፈቀድብት ሁኔታ አለ ብሏል፡፡ ረቂቁ በአንድ ግብር ዘመን ከሁለት ጊዜ በላይ ቅጣት የተጣለበት የግብር ከፋይ ድርጅት ስራ አስኪያጅ፣ የፋይናንስ ሀላፊ ጨምሮ ሌሎች ተሳታፊዎችን በወንጀል ህግ እንዲጠየቁ የሚያደርግ ነው። በረቂቅ አዋጁ ላይ ትችቱ የቀረበው የገንዘብ ሚኒስቴር ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም በዋና መስሪያ ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ ባካሄደው የባለድርሻ አካላት ወይይት ላይ ነው። በውይይቱ ላይ የተቋማት የስራ ሃላፊዎች፣ የድርጅት ተወካዮች፣ የግብር የህ
May 202 min read


የትምህርት ዘርፉን ለማሻሻል ታስቦ ከተከናወኑ ስራዎች መካከል የትምህርት ስርዓቱን ማሻሻያ አንዱ ቢሆንም እስካሁን ግን መፀሀፍቱን አሳትሞ ለተማሪዎች ማዳረስ አልተቻለም ተባለ።
ግንቦት 11/2018 የትምህርት ዘርፉን ለማሻሻል ታስቦ ከተከናወኑ ስራዎች መካከል የትምህርት ስርዓቱን ማሻሻያ አንዱ ቢሆንም እስካሁን ግን መፀሀፍቱን አሳትሞ ለተማሪዎች ማዳረስ አልተቻለም ተባለ። አንደኛ ደረጃ መፀሀፍትን ክልሎች በራሳቸው በጀት እንደሚያሳትሙ የተነገረ ሲሆን ለሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የሚያስፈልገውን መፀሀፍ የሚያቀርበው ደግሞ ትምህርት ሚኒስቴር ነው ብለዋል። ብዙዎቹ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች መማሪያ መፀሀፍት አንድ ለአንድ በሚባል ደረጃ መዳረሱን የተናገሩት የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ የመፅሀፍ ስርጭት እጥረቱ የሚስተዋለው በአንደኛ ደረጃ ላይ ነው ብለዋል፡፡ በዚህም የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች በአማካይ አንድ መፀሀፍ ለሶስት እና ለአራት ሆነው እንዲጠቀሙ እያደረገ እንደሆነም ነግሮናል፡፡ ከ200ሚሊየን ብር በላይ ወጭ አውጥቶ አዲሱን ሥርዓ
May 191 min read


አንዳንድ የግል ድርጅቶች የሠራተኞቻቸውን ትክክለኛው የጡረታ መዋጮ እንዳይሰበሰብ ደመወዝ አሳንሰው ያሳውቃሉ ተባለ።
ግንቦት 11/2018 አንዳንድ የግል ድርጅቶች የሠራተኞቻቸውን ትክክለኛው የጡረታ መዋጮ እንዳይሰበሰብ ደመወዝ አሳንሰው ያሳውቃሉ ተባለ። ድርጅቶቹ እስከ ሶስት ወር ሳይከፍሉ ከቆዩ ከሒሳብ ደብተራቸው ላይ እቀንሳለሁ ብሏል፡፡ ባለፉት ስድስት ወራትም ከ39 ቢልዮን ብር በላይ ከግል ድርጅት ሰራተኞች ተሰብስቧል ያለው ተቋሙ ከስምንት ዓመት በፊት ከነበረው ገቢው የ34 ቢልዮን ብር ብልጫ አለው ብሏል፡፡ አንድ እና ከአንድ በላይ ሠው የቀጠረ ማንኛውም የግል ድርጅት ሠራተኛውን ወደ ጡረታ አቅድ የማስገባት ግዴታ እንዳለበት የግል ድርጅት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር አስታውሷል፡፡ የጡረታ መዋጮ ከሠራተኛውም ፤ ከቀጣሪውም ድርጅት ተቀንሶ በጊዜው ገቢ መሆን እንዳለበት ነው የአስተዳደሩ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ስራ አስፈጻሚ አቶ መሠረት ዘለቀ የተናገሩት።
May 192 min read


ብሔራዊ ባንክ ካቀረበው የውጪ ምንዛሪ ከእጥፍ በላይ ፍላጎት እንደቀረበለት ተናገረ፡፡
ግንቦት 11/2018 ብሔራዊ ባንክ ካቀረበው የውጪ ምንዛሪ ከእጥፍ በላይ ፍላጎት እንደቀረበለት ተናገረ፡፡ ባንኩ 5 መቶ ሚሊዮን ዶላር የውጪ ምንዛሪ ለጨረታ አቅርቦ የነበረ ሲሆን የባንኮች ፍላጎት ደግሞ 1 ቢሊዮን ልስሳ ሚሊዮን ዶላር ሆኖ መመዝገቡን ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል፡፡ በዚህ ወቅት አንድ ዶላር 159 ብር ከ98 ሳንቲም የተሸጠ ሲሆን 30 ባንኮች በጨረታው ተሳትፈዋል፣14 ባንኮች ደግሞ በጨረታው አሸንፈው ዶላር ወስደዋል ተብሏል፡፡ ከዚህ ውስጥ 14 ባንኮች ብቻ የውጪ ምንዛሪ ማግኘታቸውን ብሄራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ የጠቀሰው፡፡ ለአንድ ዶላር በጨረታው የቀረበው ከፍተኛ ዋጋ 160.90 ብር ሲሆን አነስተኛው ደግሞ 157.30 ብር ሆኖ መመዝገቡንም ብሔራዊ ባንክ ካወጣው መግለጫ ላይ ተመልክተናል፡፡ ብሄራዊ ባንክ ለመጨረሻ ጊዜ የውጪ ምንዛሪ ጨረታ ያ
May 191 min read


ከተመን በላይ የትራንስፖርት ታሪፍ ይጨምራል፤ የሸቀጦች ዋጋም በትናንትናው ልክ ዛሬ አይገኝም።
ግንቦት 11/2018 በየጊዜው መንግስት ታሪፍ ያወጣላቸው ሸቀጦች በነጋዴዎች ፍላጎት ብቻ ዋጋቸው ይጨምራል፡፡ አንዳንዶችም እየደበቁት በከፍተኛ ዋጋ ይሸጣሉ፡፡ ከተመን በላይ የትራንስፖርት ታሪፍ ይጨምራል፤ የሸቀጦች ዋጋም በትናንትናው ልክ ዛሬ አይገኝም። ጭማሪው ምጣኔ ሐብታዊ ምክንያት የለውም፡፡ ሸማቹም ለምን ብሎ የመጠየቅ ልምድ የለውም፡፡ "ለምን" ብለው የሚጠይቁ ሲኖሩም ጭማሪውን አሜን ብለው የተቀበሉ ተደርበው ሲያዋክቡ ይታያሉ፡፡ ለነጋዴዎቹ ህገወጥነት ፍላጎት የሸማቹ ዝምታ እና የተባለውን "አሜን" ብሎ መቀበል በገበያው ላይ ምን አይነት ተፅዕኖ አለው? ስንል የጠየቅናቸዉ የምጣኔ ሀብት ባለሞያዉ ቆስጠንጢኖስ በርኸ (ዶ/ር) "በኢኮኖሚክስ ህግ ሸማቹ የገበያው ንጉስ ነው። ነገር ግን ሸማቹ 'ለምን?' ብሎ ካልጠየቀና ያለአግባብ የሚደረጉ ጭማሪዎችን በ
May 191 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

