top of page


እስራኤል በመላዋ ኢራን በአገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤት ቢሮዎች እና ፅህፈት ቤቶች በላይ ያነጣጠረ ታላቅ ድብደባ ፈፀምኩ አለች፡፡
የካቲት 25/2018 እስራኤል በመላዋ ኢራን በአገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤት ቢሮዎች እና ፅህፈት ቤቶች በላይ ያነጣጠረ ታላቅ ድብደባ ፈፀምኩ አለች፡፡ በሊባኖስ ድብደባ እየፈፀመች መሆኑን ቢቢሲ ፅፏል፡፡ የርዕሰ ከተማዋ ቤይሩት ደቡባዊ ክፍል ነዋሪዎችም አካባቢውን ለቅቀው እንዲወጡ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች ተብሏል፡፡ እስራኤል እና አሜሪካ በጣምራ በኢራን ላይ ድብደባ መፈፀም ከጀመሩ ወዲህ የሊባኖሱ ታጣቂ ቡድን ሔዝቦላህ ወሰን አሻግሮ ወደ እስራኤል ሮኬቶችን እየተኮሰ መሆኑ ይነገራል፡፡ የሊባኖሷ ርዕሰ ከተማ ቤይሩት ደቡባዊ ክፍል የሄዝቦላህ መሪዎች መናኽሪያ ነው ይባላል፡፡ ሔዝቦላህ የኢራን የጦር እና የፖለቲካ አጋር እንደሆነች መረጃው አስታውሷል፡፡ በሌላ መረጃ ሲሪላንካ አቅራቢያ የኢራን የጦር መርከብ መስመጡ ተሰምቷል፡፡ በኔፓን የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች የ
Mar 41 min read


የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን የአየር እና የባህር ሀይሎች እንዳልነበሩ አድርገን አውድመናቸዋል አሉ፡፡
የካቲት 25/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #አሜሪካ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን የአየር እና የባህር ሀይሎች እንዳልነበሩ አድርገን አውድመናቸዋል አሉ፡፡ ትራምፕ የኢራንን የአየር እና የባህር ሀይሎች እንዳልነበሩ አድርገን ደምስሰናቸዋል ያሉት በዋይት ሐውስ ከጀርመኑ መራሄ መንግስት ፍሬድሪክ ሜርዝ ጋር ከተመካከሩ በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሆነ አልጀዚራ ፅፏል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኢራን የባህር እና የአየር ሀይል እንዳይኖራት ማድረጋቸው ትራምፕ ተናግረዋል፡፡ አሜሪካ እና እስራኤል ካለፈው ሳምንት ቅዳሜ አንስቶ በጣምራ በኢራን ላይ ከባድ ድብደባ እየፈፀሙ ነው፡፡ ቢቢሲ እንደፃፈው ትራምፕ የኢራንን የጦር አቅም አነካክቼዋለሁ ቢሉም ፋርሳዊቱ አገር በእስራኤል እና በቀጠናው በሚገኙ የአሜሪካ ተቋሞች ላይ የአፀፋ ጥ
Mar 42 min read


የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ ኢራንን ለመምታት መዘጋጀቱን ተሰማ፡፡
የካቲት 12/2018 የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ ኢራንን ለመምታት መዘጋጀቱን ተሰማ፡፡ ዋሽንግተንን ቴህራንን በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት ለመምታት ዝግጅት ማድረጓን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ሰዎች ነግረውናል ብሎ የዘገበው ሲ ኤን ኤን ነው፡፡ ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግን የመጨረሻውን ውሳኔ አለመስጠታቸው በመረጃ ተጠቅሷል፡፡ የአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ከፍተኛ ባለስልጣናት በትላንትናው እለት በዋይት ሐውስ ተገኝተው በኢራን ጉዳይ ላይ ውይይት ማድረጋቸውም ተነግሯል፡፡ ትራምፕም ከኢራን ጋር ስለተደረገው ድርድር ሁኔታ ከልዩ መልዕክተኛው ስቲቭ ዊትኮፍ እና ከአማቻቸው ጃሬድ ኩሽነር ማብራሪያ እንደተሰጣቸው በመረጃው ተነስቷል፡፡ አሜሪካና ኢራን ያደረጉት ትራምፕ ቀይ መስመር በሚላቸው ጉዳዮች ላይ አሁንም ከስምምነት አለመድረሱ ተዘግቧል፡፡
Feb 191 min read


ኢራን የሆርሙዝ ሰርጥን በጊዜያዊነት መዝጋቷ ተሰማ ።
የካቲት 11/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #ኢራን ኢራን የሆርሙዝ ሰርጥን በጊዜያዊነት መዝጋቷ ተሰማ ። ሰርጡ የተዘጋው *የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ* በአካባቢው የባህር ሃይል ልምምድ ስለሚያደርግ ነው ተብሏል። ልምምዱ አሜሪካ በአረብ ባህር አካባቢ ወታደራዊ አቅሟን እያደረጀች መምጣቷን ተከትሎ የሚካሄድ እንደሆነ ዘ ቴሌግራፍ ጽፏል። ዋሽንግተን አውሮፕላን ተሸኳሚ የጦር መርከብን ጨምሮ ወታደሮችን ከዘመን አፈራሽ የውጊያ መሳሪያዎች ጋር ወደ አካባቢው መላኳ ተነግሯል። የኢራን እርምጃ ሁለቱ ሀገራት አለመግባባታቸውን ለመፍታት በጄኔቫ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ላይ እያሉ የተሰማም ነው። ኢራን የሆርሙዝ መተላለፊያን ስትዘጋ እንደ ጎርጎርሳውያኑ አቆጣጠር ከ1980ዎቹ ወዲህ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ተብሏል። #ሩሲያ ሩሲያ በባልቲክ ሀገራት ላይ ወረራ ከፈ
Feb 181 min read


ጥር 27/2018 – የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ሱዳን የሱዳን ወታደራዊ መንግስት እና የአገሪቱ ጦር የበላይ ጄኔራል አብዱልፈታህ አል ቡርሃን የአገሪቱ ጦር የደቡብ ኮርዶፋኗን ዋና ከተማ ካዱግሊን ከተቀሩት ክፍሎች ጋር የሚያገናኘውን አውራ ጎዳና በእጁ ማስገባቱን ተናገሩ፡፡ ጦሩ የRSF ፈጥኖ ደራሽ ሀይል በካዱግሊ ፈጥሮት የነበረውን ከበባ ጥሶ እንደወጣ አል ቡርሃን መናገራቸውን አልጀዚራ ፅፏል፡፡ አብዱልፈታህ አልቡርሃን የደቡብ ኮርዳፋኗን ከተማ ከተቀሩት የአገሪቱ ክፍሎች ጋር የሚያገናኘውን አውራ ጎዳና ተቆጣጥረነዋል ያሉት በኦምዱርማን በሚገኘው የአገሪቱ ዋና የቴሌቪዥን ጣቢያ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ነው ተብሏል፡፡ ጄኔራል አል ቡርሃን ከRSF ጋር በጭራሽ የተኩስ አቁም አናደርግም ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ የአገሪቱ ወታደራዊ መሪ የተኩስ አቁም RSF መልሶ እንዲያንሰራራ ስለሚያደርገው
Feb 42 min read


የሩሲያ የውጭ የስለላ ተቋማት SVR የፈረንሳዩ ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የማይፈልጓቸውን የአፍሪካ መሪዎችን የማስገደል ሙከራ አድርገዋል ሲል ከሰሰ፡፡
ጥር 26/2018 – የውጪ ሀገራት ወሬዎች # ሩሲያ የሩሲያ የውጭ የስለላ ተቋማት SVR የፈረንሳዩ ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የማይፈልጓቸውን የአፍሪካ መሪዎችን የማስገደል ሙከራ አድርገዋል ሲል ከሰሰ፡፡ SVR ማክሮን ዘመናዊውን የእጅ አዙር ቅን አገዛዝ አሻፈረን ያሏቸውን እና በራሳቸው ለመቆም እየጣሩ ያሉ አገሮችን መሪዎች ለማስገደል ትዕዛዝ ሰጥተዋል ማለቱን አናዶሉ ጽፏል፡፡ ከወር በፊት በቡርኪናፋሶ ተደርጎ ነበር ያለውን የመንግስት ግልበጣ ሙከራ በምሳሌነት አንስቷል የውጭ የስለላ ድርጅቱ፡፡ ውስጥኑ በፀረ ቅኝ አገዛዝ አቋማቸው የሚታወቁትን የቡርኪናፋሶው መሪ ሻምበል ኢብራሂም ትራኦሬን ለማስገደል ጭምር የተዶለተ ነበር ማለቱ ተጠቅሷል፡፡ ቡርኪናፋሶ ፣ ማሊ እና ኒጀር የፈረንሳይ የጦር ትብብር አያሻንም ያሉ አገሮች ናቸው፡፡ የፈረንሳይን ወታደሮችም ከ
Feb 32 min read


ሜታ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሆኑ የአውስትራሊያ አዳጊ ወጣቶችን ገፆቹን እንዳይጠቀሙ አደረጋቸው፡፡
ጥር 5/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #አውስትራሊያ የእነ ፌስ ቡክ እና ኢኒስታግራም የማህበራዊ ድረ ገፆች እናት ኩባንያ (ሜታ) ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሆኑ የአውስትራሊያ አዳጊ ወጣቶችን ገፆቹን እንዳይጠቀሙ አደረጋቸው፡፡ ክልከላው በአውስትራሊያ ስራ ላይ የዋለውን ህግ መሰረት ያደረገ መሆኑን ABC ፅፏል፡፡ አዲሱ የአውስትራሊያ ህግ እድሜያቸው ከ16 አመታት በታች የሆነ አዳጊ ወጣቶች በጭራሸ የማህበራዊ ትስስር ገፆችን እንዳይገለገሉ የሚከለክል ነው፡፡ አዳጊ ወጣቶች ክልከላውን ተላልፈው የማህበራዊ ትስስር ገፆቹን ሲገለገሉ ከተገኙ አገልግሎት አቅራቢያ ኩባንያዎች የገንዘብ ቅጣት እንዲቆነደዱ ያደርጋል፡፡ አዳጊ ወጣቶችን የማህበራዊ ትስስር ገፆችን እንዳይገለገሉ በማድረግ አውስትራሊያ ቀዳሚዋ አገር ሆናለች፡፡ #ሶማሊያ የሶማሊያ ፌዴራላዊ መንግስት ከተባበ
Jan 132 min read


ቭላድሚር ፑቲን ዩክሬይን የሰላሙን መንገድ ብትመርጥ ይሻላታል ሲሉ በድጋሚ አስጠነቀቁ፡፡
ታህሳስ 20/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #ሩሲያ የሩሲያው ፕሬዘዳንት ቭላድሚር ፑቲን ዩክሬይን የሰላሙን መንገድ ብትመርጥ ይሻላታል ሲሉ በድጋሚ አስጠነቀቁ፡፡ የሩሲያው ታስ የወሬ ድርጅት የፑቲንን የከትናንት በስቲያ ማስጠንቀቂያ እወቁት ማለቱን የፃፈው ሬውተርስ ነው፡፡ የሩሲያ ጦር ሰሞኑን በዩክሬይን ላይ ሁለንተናዊ ጥቃቱን ማክፈቱ ይነገራል፡፡ ፑቲን የድጋሚ ማስጠንቀቂያቸው የተሰማው የሩሲያ ጦር በቅርቡ በዳኔስክ እና በዛፓሮዢያ ግዛቶች በያዛቸው ከተሞች እና አካባቢዎች ጉብኝት ያደረጉ የጦር አለቆችን ባነጋገሩበት አጋጣሚ ነው ተብሏል፡፡ የሩሲያው ፕሬዘዳንት ዩክሬይን ሰላሙን ካልመረጠች ለጦርነቱ ያስቀመጥነውን ግብ በጦር ሀይል ማሳካታችን አይቀርም ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ ጦርነቱ ያለ ሁነኛ መፍትሄ ወደ 4ኛ ዓመቱ እየታቀረበ ነው፡
Dec 29, 20252 min read


እስራኤል ለሶማሌላንድ ይፋዊ የነፃ አገርነት እውቅና መስጠቷ ሶማሊያን በእጅጉ አስቆጣት፡፡
ታህሳስ 18/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #እስራኤል እስራኤል ለሶማሌላንድ ይፋዊ የነፃ አገርነት እውቅና መስጠቷ ሶማሊያን በእጅጉ አስቆጣት፡፡ ሞቃዲሾ የእስራኤልን እርምጃ አጥብቃ ማውገዟን ዘ ኒው አረብ ፅፏል፡፡ ከሶማሊያ በተጓዳኝ ግብፅ ፣ ቱርክ እና ጂቡቲም እስራኤል ለሶማሌላንድ የነፃ አገርነት እውቅና መስጠቷን ኮንነውታል ተብሏል፡፡ አገሮቹ የሶማሊያ ሉአላዊነት እና የግዛት አንድነት እንዲከበር ድጋፋቸውን እንደሚቀጥሉ እወቁልን ብለዋል፡፡ ሶማሌላንድ ራሷን ከተቀረችው ሶማሊያ ከነጠለች 34 ዓመታት ሆኗታል፡፡ አለም አቀፋዊ እውቅና ባይኖራትም ከሶማሊያ በተሻለ የተረጋጋች እንደሆነች ይነገርላታል፡፡ በነፃ አገርነት ይፋዊ እውቅና ስታገኝ የእስራኤል የመጀመሪያው ሆኗል፡፡ ሶማሊያ እና አጋሮቿ ሌሎችም የእስራኤልን ፈለግ እንዳይከተሉ መስጋታቸው ተጠቅሷል፡፡
Dec 27, 20252 min read


ከሳምንት በፊት ከናይጄርያ ኬቢ ግዛት አዳሪ ትምህርት ቤት ታግተው የተወሰዱ ሴት ተማሪዎች በሙሉ ተለቀቁ፡፡
ህዳር 17 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #ናይጄርያ ከሳምንት በፊት ከናይጄርያ ኬቢ ግዛት አዳሪ ትምህርት ቤት ታግተው የተወሰዱ ሴት ተማሪዎች በሙሉ ተለቀቁ፡፡ በጊዜው 25 ሴት ተማሪዎች ታግተው እንደነበር ቢቢሲ አስታውሷል፡፡ አንዷ አስቀድሞ ከአጋቾቿ ማምለጧ ሲነገር ሰንብቷል፡፡ ታጋቾቹን ሴት ተማሪዎች ለማስለቀቅ የናይጀሪያ የፀጥታ ሀይሎች በፕሬዘዳንት ቦላ ቲኑቡ ትዕዛዝ በቅንጅት አሰሳ ላይ ተሰማርተው ነበር፡፡ ሴት ተማሪዎቹ ከእገታ ተለቀዋል ቢባልም በምን ዓይነት ሁኔታ እንደተለቀቁ የተብራራ ነገር የለም፡፡ ባለፈው ሳምንት አርብ ደግሞ ከኒጀር ግዛት የካቶሊክ ትምህርት ቤት ከ250 በላይ ተማሪዎች ታግተው መወሰዳቸውን መረጃው አስታውሷል፡፡ ከኒጀር ግዛት ታግተው የተወሰዱት ተማሪዎች ግን እንዳልተለቀቁ ተጠቅሷል፡፡ #ብራዚል
Nov 26, 20252 min read


ህዳር 16 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ቻይና የቻይናው ፕሬዘዳንት ሺ ጂን ፒንግ ታይዋን ከእናት አገሯ ጋር መቀላቀሏ በአሁኑ ወቅት እጅግ አስፈላጊ ጉዳይ ነው አሉ፡፡ ሺ ጂን ፒንግ ስለዚሁ ጉዳይ በስልክ ለአሜሪካው አቻቸው ዶናልድ ትራምፕ እንደነገሯቸው የቻይና መንግስታዊ መገናኛ ብዙሃን ማውራታቸው አናዶሉ ፅፏል፡፡ ታይዋን ራሴን የቻልኩ ነፃ አገር ነኝ ብትልም ቻይና ግን ታይዋንን እንዳፈነገጠች የገዛ ግዛቷ አድርጋ ትቆጥራታለች፡፡ የቻይና መንግስት እና አድራጊ ፈጣሪው የቻይና ኮሚኒስቶች የፖለቲካ ማህበር ቀደም ሲል ታይዋን በዚያም ሆነ በዚህ መልሳ የቻይና አካል መሆኗ አይቀርም ሲሉ ቆይተዋል፡፡ በአዲሱ የቻይና ፕሬዘዳንት የታይዋን አቋም የአሜሪካ ይፋዊ አስተያየት ምን እንደሆነ አልተሰማም፡፡ ቻይና ቀደም ሲል በታይዋን ዙሪያ ገባ ታላላቅ የጦር ልምምዶችን ማድረጓን መረጃው አስታውሷል፡፡ #አ
Nov 25, 20251 min read


ህዳር 15 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ናይጄርያ ከናይጄርያዋ ኒጀር ግዛት የአንድ የካቶሊክ ትምህርት ቤት ከታገቱት ከ300 በላይ ተማሪዎች መካከል ሃምሳው ከአጋቶቻቸው ማምለጣቸው ተሰምቷል፡፡ ጉዳዩን የሚከታተለው ቡድን 50ው ተማሪዎች ከአጋቾቻቸው ማምለጣቸውን አረጋግጫለሁ ማለቱን ቢቢሲ ፅፏል፡፡ ይሁንና በምን ሁኔታ እና ከየት እንዳመለጡ አላብራራም፡፡ አምላጮቹ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተቀላቅለዋል ማለቱ ተሰምቷል፡፡ የናይጀሪያ የፀጥታ ሀይሎች ታጋቾቹን ለማስለቀቅ በተቀናጀ አሰሳ ላይ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ባለፈው ሳምንት መጀመሪያም በኬቢ ግዛት ከሚገኝ አንድ አዳሪ ትምህርት ቤት 20 ተማሪዎች ታግተው መወሰዳቸውን መረጃው አስታውሷል፡፡ እገታውን በመስጋት ብዙዎቹ የናይጀሪያ ግዛቶች ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉ ማድረጋቸው በመረጃው ተጠቅሷል፡፡ #ሳውዲ_አረቢያ ሳውዲ አረቢያ በ1
Nov 24, 20252 min read


ጥቅምት 29 2018 - ጥቅምት 29 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#አሜሪካ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን በደቡብ አፍሪካ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የቡድን 20 አባል አገሮች ጉባኤ አይገኝም አሉ፡፡ የአሜሪካውፕሬዘዳንት አፍሪካ ነርስ በተሰኙት ነጭ ደቡብ አፍሪካዊያን ላይ እልቂት እና ማሳደዱ በርትቶባቸዋል የሚል ክሳቸውን እየደጋገሙት መሆኑን አናዶሉ አስታውሷል፡፡ የፕሬዘዳንት ሲሪል ራማፎሳ መንግስት በትራምፕ የሚቀርበውን ውንጀላ በተደጋጋሚ እያስተባበለ ነው፡፡ ትራምፕ ግን የደቡብ አፍሪካን መንግስት ጥምድ አድርገው እንደያዙት ነው፡፡ እንደውም ደቡብ አፍሪካ ከቡድን 20 አባል አገርነቷ ልትባረር ይገባል ያሉት ሰሞኑን ነው፡፡ የቡድን 20 አባል አገሮች ስብሰባ በደቡብ አፍሪካ ቢካሄድም ያለ አሜሪካ ተሳትፎ ይሆናል ተብሏል፡፡ #ማሊ በምዕራብ አፍሪካዊቱ ሀገር ማሊ
Nov 8, 20251 min read


ጥቅምት 28 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ካሜሮን የካሜሮኑ አረጋዊ ፕሬዘዳንት ፖል ቢያ ለ8ኛ ጊዜ ቃለ መሐላ በመፈፀም አዲሱን ሀላፊነታቸውን ተረከቡ፡፡ ፖል ቢያ ለ8ኛ ጊዜ ቃለ መሐላ በመፈፀም ሀላፊነታቸው የተረከቡት በቅርብ ጊዜው የካሜሩን ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ አሸንፈዋል ከተባለ በኋላ እንደሆነ አልጀዚራ ፅፏል፡፡ የ92 አመቱ አረጋዊ ፖል ቢያ እስካሁን ካሜሮንን ከ40 አመታት በላይ መርተዋታል፡፡ በአሁኑ ጊዜም ከአገር መሪዎቹ መካከል በእድሜ አንጋፋው እሳቸው ናቸው፡፡ ፖል ቢያ በምርጫው አሸንፈዋል የተባለው ሁነኛ ተፎካካሪዎች ከምርጫ በታገዱበት አጋጣሚ ነው ተብሏል፡፡ ተቃዋሚዎች ፖል ቢያ አሸናፊ የተደረጉበትን ምርጫ ህገ መንግስታዊ ጠለፋ ነው ሲሉ እየጠሩት መሆኑን መረጃው አስታውሷል፡፡ #ሩሲያ ሩሲያ የአሜሪካ የወረራ ስጋት ተጋርጦብኛል ለትምትለው የደቡብ አሜሪካዋ አገ
Nov 7, 20252 min read


ጥቅምት 27 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ፊሊፒንስ ፊሊፒንስን ሰሞኑን በመታት ከባድ አውሎ ነፋስ የሟቾቹ ብዛት ከ140 በላይ መድረሱ ተሰማ፡፡ አውሎ ነፋሱ በከባድ ጎርፍ እና በመሬት መንሸራተት ጭምር የታገዘ እንደነበር AFP አስታውሷል፡፡ በአደጋው ከሞቱት እና አካላዊ ጉዳት ከገጠማቸው ሌላ 127 ሰዎች ደግሞ እስካሁን የደረሱበት አልታወቀም ተብሏል፡፡ ይህም የሟቾቹ ብዛት ከተጠቀሰውም በላይ ሊጨምር ይችላል የሚል ስጋት አሳድሯል፡፡ ሴቡ የተባለችዋ ግዛት ዋነኛዋ የአደጋው ሰለባ ነች፡፡ በግዛቲቱ የደረሰው ጎርፍ እና የመሬት መንሸራተት ከዚህ ቀደም ከደረሱት ሁሉ በእጅጉ ከባድ ነበር ተብሏል፡፡ ጎርፉ መኪኖችን እና ትልልቅ ኮንቴይነሮችን ጭምር አንከብክቦ መጋለቡ ታውቋል፡፡ ለፊሊፒንሱ አውሎ ነፋስ ፣ ጎርፍ እና የመሬት መንሸራተት አደጋ የአየር ለውጡ በዋና ምክንያትነት እየቀረ
Nov 6, 20252 min read


ጥቅምት 25 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ኢራን የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አርጋቺ አገሬ ከአሜሪካ ጋር ወደ ኒኩሊየር ነኩ ንግግር ለመመለስ የሚያጣድፉት ጉዳይ የለም አሉ፡፡ አርጋቺ ከአሜሪካ ጋር በእኩልነት ደረጃ ካልሆነ በስተቀር አንዳችም ንግግር ማድረግ እንደማትሻ መናገራቸውን አልጀዚራ ፅፏል፡፡ አሜሪካ ኢራን በጭራሽ ዩራኒየም ማብላላት የለባትም የሚል አቋም አላት፡፡ አዲሱ የአሜሪካ የንግግር ሀሳብም በዚሁ ጉዳይ ላይ የሚያተኩር ነው ይባላል፡፡ ኢራን ደግሞ ይሄን በጭራሽ አልቀበልም ባይ ነች፡፡ ምዕራባዊያኑ ኃያላን ኢራን የኒኩሊየር ቦምብ የመስራት ውጥን አላት ሲሉ ይከሷታል፡፡ ቴሕራን በበኩሏ የኒኩሊዩር መርሐ ግብሬ ለኤሌክትሪክ ማመንጫ እና ለሰላማዊ አገልግሎት የታለመ ነው የሚል መሟገቻ ታቀርባለች፡፡ #ሜክሲኮ ፔሩ ከሜክሲኮ ጋር የነበራትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አቋረጠች፡፡ ፔሩ ዲ
Nov 4, 20252 min read


ኢትዮጵያ በመካከለኛ የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ዝርጋታ አቅሟን ለማሳደግ ከፈረንሳይ ተቋም ጋር ውል አሰረች፡፡
ጥቅምት 25 2018 ኢትዮጵያ በመካከለኛ የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ዝርጋታ አቅሟን ለማሳደግ ከፈረንሳይ ተቋም ጋር ውል አሰረች፡፡ የመካከለኛ የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ተጠቃሚዎች የሆኑት ኢንዱስትሪዎች መሆኑ የተነገረ ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሚያስተዳድራቸው እና ከሚመራቸው መስመሮች አንዱ መሆኑ ተነግሯል፡፡ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የመካከለኛ መስመር ዝርጋታ አቅምን ለማሳደግ የተፈራረመችው ከፈረንሣዩ 'ኤሊክቲሪሲቲ ደ ፍራንስ' (EDF) ጋር መሆኑን ሰምተናል፡፡ በሌላ በኩል አገልግሎቱ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ግብዓቶች ከሚያመርት የኬንያ ኩባንያ ጋር ውይይት ማረጉን ተናግሯል፡፡ ተቋሙ ከኩባንያው ጋር የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ግብዓቶችን በኢትዮጵያ ማምረት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መወያየቱን የሰማን ሲሆን
Nov 4, 20251 min read


ጥቅምት 19 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ብራዚል የብራዚል ፖሊስ የሬዮ ዴ ጄኒየሮ ከተማን ከተደራጁ ወሮበሎች ለማፅዳት ባካሄደው ዘመቻ በጥቂቱ 64 ሰዎች ተገደሉ ተባለ፡፡ ከተማይቱ በቅርቡ አለም አቀፋዊ የአየር ለውጥ ጉባኤን እንደምታስተናግድ ሬውተርስ ፅፏል፡፡ ፖሊስ ለዚህ ጉባኤ ቅድመ ዝግጅት ሬዮ ዴ ጄኔሮን ከወሮበሎች ለማፅዳት በዘመቻ ላይ ነው ተብሏል፡፡ በአጋጣሚው በተፈጠረው ግጭት ከተገደሉ 64 ሰዎች መካከል 4ቱ የፖሊስ መኮንኖች መሆናቸው ታውቋል፡፡ በትናንቱ ዘመቻ 2 ሺህ 500 ፖሊሶች እና ሌሎች የፀጥታ ባልደረቦች መካፈላቸው ተጠቅሷል፡፡ በግጭቱ በፀጥታ ባልደረቦቹ እና በተደራጁት ወሮበሎች መካከል የተኩስ ልውውጥ እንደነበር መረጃው አስታውሷል፡፡ ፖሊስ ከ80 በላይ የተደራጁ ወሮበሎችን አስሬያለሁ ማለቱ በመረጃው ተጠቅሷል፡፡ #ቤኒን በቤኒን የዋነኛው ተቃዋሚ
Oct 29, 20252 min read


ጥቅምት 17 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ቱርክ በቱርክ PKK የተሰኘው የኩርዶች የቀድሞ አማጺ ቡድን ታጣቂዎቹን ከቱርክ ወደ ኢራቅ ማስወጣት ጀመረ፡፡ PKK ታጣቂዎቹን ወደ ኢራቅ ማስወጣት የጀመረው ከቱርክ መንግስት ጋር በጀመረው የሰላም ሒደት መሰረት እንደሆነ አሶሼትድ ፕሬስ ፅፏል፡፡ የኩርዶቹ ታጣቂ ቡድን ከእንግዲህ የትጥቅ አመፅ እርም ይሁንብኝ ያለው ባለፈው አመት ግንቦት ወር ላይ እንደነበር መረጃው አስታውሷል፡፡ በትጥቅ መፍታት ሒደት ላይ ይገኛል ተብሏል፡፡ PKK ታጣቂነቱን ትቶ በሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ብቻ የመቀጠል ፍላጎት እንዳለው ተጠቅሷል፡፡ ቡድኑ ለወሰደው እርምጃ አስተማማኝነት የቱርክ መንግስት PKK ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ማህበርነት የሚለወጥበትን ሁኔታ እንዲያመቻችለት መጠየቁ ተሰምቷል፡፡ PKK የትጥቅ አመፅ እርም ይሁንብኝ ያለው ከ40 አመታት በኋላ እንደሆነ መረጃው አስታውሷ
Oct 27, 20252 min read


ጥቅምት 13 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ሱዳን በሱዳን የRSF ፈጥኖ ደራሽ ሀይል ከአገሪቱ ኤርፖርቶች የሚነሱ እና በኤርፖቶቹ የሚያርፉ አውሮፕላኖችን በሙሉ አወድማለሁ ሲል ዛተ፡፡ ዛቻውን ያሰሙ የፈጥኖ ደራሹ ሀይሉ አዛዥ ሌተና ጄኔራል ሞሐመድ ሐምዳን ዳጋሎ እንደሆኑ ሱዳንስ ፖስት ፅፏል፡፡ ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ትናንት ወደ አገልግሎት ተመልሷል በተባለው የካርቱም ኤርፖርት ላይ ተደጋጋሚ የድሮን ጥቃት ሰንዝሯል ተብሏል፡፡ የካርቱም ኤርፖርት ትናንት ከ2 ዓመታት በኋላ የመጀመሪያውን የሀገር ውስጥ በረራ አውሮፕላን ማስተናገዱ ታውቋል፡፡ ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ከሱዳን መንግስት ጦር ጋር ሲዋጋ ከ2 ዓመታት ከመንፈቅ በላይ ሆኖታል፡፡ ጦርነቱን ማቆሚያ አንዳችም ፍንጭ አይታይም፡፡ #አሜሪካ በአሜሪካ በሁለት የሩሲያ ታላላቅ የነዳጅ ኩባንያዎች ላይ ያነጣጠረ አዲስ ማዕቀብ ጣለች፡፡ ማዕቀቡ የተጣለባቸው ሮስ
Oct 23, 20252 min read


ጥቅምት 12 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ካሜሩን በካሜሩን ከሳምንት በፊት በተካሄደው ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ አረጋዊው የአገሪቱ መሪ ፖል ቢያ እንዳሸነፉ የቅድሚያ ውጤቱ አሳየ ተባለ፡፡ የአገሪቱ የምርጫ አከናዋኝ መስሪያ ቤት በቅድሚያ ውጤቱ ፖል ቢያ ለፕሬዘዳንታው ምርጫው ከተሰጠው ድምፅ 53 በመቶውን በማግኘት አሸንፈዋል ማለቱን አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡ የፖል ቢያ የቅርብ ተፎካካሪ ኢሳ ቺሮማ ባካሪ ያገኙት ድምፅ 35 በመቶ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ ባካሪ ከምርጫው በኋላ በተደጋጋሚ አሸንፌያለሁ ሲሉ ሰንብተዋል፡፡ ኢሣ ቺሮማ ባካሪ ውጤቱ በወጉ ይጣራልኝ ማለት መጀመራቸው ተሰምቷል፡፡ የ92 አመቱ አረጋዊ ፖል ቢያ የምርጫ ድላቸው ከፀናላቸው የ42 አመታት መሪነታቸውን በመ5 ዓመታት ይጨምርላቸዋል ተብሏል፡፡ የአገሪቱ ህገ መንግስታዊ ምክር ቤት ይፋዊ ውጤቱን ሰሞኑን እወቁት እንደሚል በመረጃው ተጠቅሷል፡፡
Oct 22, 20252 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

