top of page


የኢራን ሹሞች አሜሪካን በሚሳየሎቻችን አትምጪብን አሏት፡፡
ሰኔ 12/2018 - #ዓለም_አቀፍ_ወሬዎች #ኢራን የኢራን ሹሞች አሜሪካን በሚሳየሎቻችን አትምጪብን አሏት፡፡ የኢራን የውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ ኢስማየል ባጋይ የኢራን የሚሳየል መርሐ ግብር አሜሪካ እና ኢራን በደረሱት የጦርነት ማቆሚያ የመግባቢያ ስምምነት አንድም ስፍራ አልተጠቀሰም ማለታቸውን ሬውተርስ ፅፏል፡፡ ቃል አቀባዩ ሚሳየላችን ለተኩስ እንጂ ለድርድር አይቀርብም ሲሉ መሳለቃቸውም ተሰምቷል፡፡ ከአሜሪካ ሹሞች በኩል የኢራን የሚሳየል መርሐ ግብር የወደፊቱ ድርድር አካል ነው የሚለው አስተያየት እየተደጋገመ ነው ተብሏል፡፡ የኢራን ሹሞች ደግሞ ምንም ቢፈጠር ሚሳየሎቻችን ለድርድር አይቀርቡም የሚል አቋም ይዘዋል፡፡ በመግባቢያ ስምምነቱ ዝርዝር ጉዳዮች ኢራን እና አሜሪካ በ60 ቀናት ውስጥ ድርድር እንደሚያደርጉ በሰነዱ ላይ መስፈሩን መረጃው አስታውሷል፡፡
5 days ago2 min read


በአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት የተሰማሩ ባለሃብቶች ለዓመታት ሲያቀርቡት የነበረው ለኢንቨስትመንት የሚውል መሬት ጥያቄ ምላሽ አግኝቷል ተባለ።
ሰኔ 5/2018 በአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት የተሰማሩ ባለሃብቶች ለዓመታት ሲያቀርቡት የነበረው የማስፋፊያ እና ለአዲስ ኢንቨስትመንት የሚውል መሬት ጥያቄ ምላሽ አግኝቷል ተባለ። በግብርና ሚኒስቴር ድጋፍ ለማስፋፊያ እና ለአዲስ ኢንቨስትመንት የሚውል ተጨማሪ 33,000 ሄክታር መሬት በተለያዩ ክልሎች መገኘቱ ተነግሯል፡፡ እስከ አሁን ልማቱ ሲካሄድ የቆየው በ12,000 ሄክታር መሬት እንደነበር ከኢትዮጵያ አበባ ፤ አትክልትና ፍራፍሬ አምራቾችና ላኪዎች ማህበር ሠምተናል። በኢትዮጵያ አሁን ላይ 120 የሚሆኑ ባለሃብቶች በአበባ ፤ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ተሰማርተው እንደሚገኙ ተነግሯል። እነዚህ ባለሃብቶች እየሰሩ ያሉት 12,000 ሄክታር መሬት ላይ እንደሆነ ከኢትዮጵያ አበባ ፤ አትክልትና ፍራፍሬ አምራቾች እና ላኪዎች ማህበር ዋና ዳይሬክተር አቶ ቴዎ
Jun 121 min read


በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የነዳጅ አቅርቦት ችግር የወርቅ ምርትን በ30 በመቶ እንዲቀንስ ምክንያት ሆኗል
ሰኔ 5/2018 የወርቅ ማዕድን ከሚመረትባቸው ክልሎች መካከል የሆነው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ የነዳጅ እጥረቱ፤ በወርቅ መገኘት የነበረበትን ገቢ እያሳጣ መሆኑን ተናገረ፡፡ ባለፉት 2 ወራት ብቻ የነዳጅ አቅርቦት ችግር የወርቅ ምርትን በ30 በመቶ እንዲቀንስ ምክንያት ሆኗል ብሏል፡፡ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ የማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ፤ የነዳጅ አቅርቦት ችግሩ ከባለፉት ወራት የተሻለ ቢሆንም አሁንም ግን ችግሩ በማዕድን ዘርፉ ላይ ጥላውን እንዳጠላበት ተናግሯል። በሌላ በኩል ክልሉ በዘንድሮው 9 ወራት 6222.5 ኪ.ግ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ማድረጉንም ሰምተናል። ባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከ47 ኩንታል በላይ ወርቅ ገቢ እንዳደረገም ተነግሯል። በዚህም አጠቃላይ በማዕድን ዘርፉ ከ83 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል ሲል ቢሮው ነግሮናል። የክልሉ የማዕድን
Jun 121 min read


የድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ድርጅት፣ በሳምንት ሁለቴ የሚሰጠውን የትራንስፖርት አገልግሎት ወደ ሶስት ማሳደጉን ተናገረ።
ሰኔ 3/2018 የድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ድርጅት፣ በሳምንት ሁለቴ የሚሰጠውን የትራንስፖርት አገልግሎት ወደ ሶስት ማሳደጉን ተናገረ። ድርጅቱ በድንገተኛ ጎርፍ ምክንያት በሀዲዱ ላይ በደረሰ ጉዳት ለሁለት ሳምንት ያህል ስራ አቁሞ እንደነበርና ጥገና በማድረግ ወደ ስራ መመለሱም ተነግሯል። ከድሬዳዋ እስከ ደወሌ የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጠው ድርጅቱ፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከሰራው ስራ ከ33 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱ ተነግሯል። ድርጅቱ 20ኛ የቦርድ መደበኛ ጉባኤውን ከትናንት በስቲያ ማክሰኞ ያደረገ ሲሆን የዘጠኝ ወራት የስራ ክንውኑን ገምግሟል። በሚኒሊክ ዘመነ መንግስት የተቋቋመው ከጅቡቲ እስከ አዲስ አበባ የሚደርሰውና 781 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የባቡር መስመር፣ ከ5 ዓመት በፊት በሚኒስትሮች ምክር ቤት በተወሰነው መሰረት ሀብትና ንብረ
Jun 111 min read


ግንቦት 20/2018 - ዓለም አቀፍ ወሬዎች
#ፍልስጤም የፍልስጤማውያኑ ታጣቂ ቡድን (ሐማስ) የወታደራዊ ክንፉ የበላይ ሞሐመድ አውዳ በእስራኤል ጥቃት መገደሉ እውነት ነው አለ፡፡ ሞሐመድ አውዳ የተገደለው እስራኤል በጋዛ ከተማ በፈፀመችው የአየር ጥቃት እንደሆነ TRT ዎርልድ ጽፏል፡፡ ከሐማሱ የወታደራዊ ክንፍ አዛዥ ጋር በጥቃቱ ባለቤቱ እና ሁለት ልጆቹ መገደላቸው ታውቋል፡፡ አውዳ ከሐማስ መስራቾች አንዱ እንደነበር በቡድኑ መግለጫ ተጠቅሷል፡፡ ሞሐመድ አውዳ በሐማስ ወታደራዊ ክንፍ የበላይነት የተሰየመው በቅርቡ እንደነበር መረጃው አስታውሷል፡፡ እስራኤል የጋዛ የጦር ዘመቻዋን ከጀመረች ወዲህ በርካታ ስመ ጥር የሐማስ ወታደራዊ አዛዦችን መግደሏን መረጃው አስታውሷል፡፡ #ጋና ምዕራብ አፍሪካዊቱ ጋና ከደቡብ አፍሪካ ዜጎቿን ማስወጣት ጀመረች፡፡ በደቡብ አፍሪካ በውጭ ተወላጅ አፍሪካውያን ላይ ያነጣጠረው
May 282 min read


የእስራኤል እና የሊባኖስ መንግስታት የ10 ቀናት የተኩስ አቁም ለማድረግ ተስማሙ ተባለ፡፡
ሚያዝያ 9/2018 - ዓለም አቀፍ ወሬዎች #የእስራኤል_እና_የሊባኖስ የእስራኤል እና የሊባኖስ መንግስታት የ10 ቀናት የተኩስ አቁም ለማድረግ ተስማሙ ተባለ፡፡ በሁለቱ አገሮች መካከል የተኩስ አቁም ለማድረግ ስምምነት መደረሱን የአሜሪካው ፕሬዘዳንት በትሩዝ ማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ፅሁፍ ማብሰራቸውን TRT ዎርልድ ፅፏል፡፡ በኢራን ላይ የአሜሪካ እና የእስራኤል የጦር ድብደባ በተጀመረ ሰሞን ወዲያው የሊባኖሱ ጦርነት መፈንዳቱ ይታወቃል፡፡ የእስራኤል የጦር ሹሞች ወደ ጦርነቱ የገነባው የሊባኖሱ ሺአ ታጣቂ ቡድን ወደ እስራኤል ሮኬቶችን በመተኮሱ ነው ባዮች ናቸው፡፡ ወደ ሊባኖስ ደቡባዊ ክፍል የዘለቀው የእስራኤል ጦር ከትናንት ምሽት 3 ሰዓት አንስቶ የተኩስ አቁም እንዲያደርግ መታዘዙ ተሰምቷል፡፡ ኢራንም በሊባኖስ ጭምር የተኩስ አቁም እንዲደ
Apr 172 min read


አሜሪካ የሆርሙዝን የባህር መተላለፊያ ወሽመጥ እና የኢራንን ወደቦች መዝጋቷን ቻይና በጥብቅ ተቃወመችው፡፡
ሚያዝያ 7/2018 - ዓለም አቀፍ ወሬዎች #አሜሪካ አሜሪካ የሆርሙዝን የባህር መተላለፊያ ወሽመጥ እና የኢራንን ወደቦች መዝጋቷን ቻይና በጥብቅ ተቃወመችው፡፡ እስያዊቱ አገር የአሜሪካን እርምጃ አደገኛ ነው እንዳለችው አናዶሉ ፅፏል፡፡ ሀላፊነት የጎደለውም ስትል ጠርታዋለች፡፡ የቻይና የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የአሜሪካ የባህር ወሽመጡን መዝጋት ውጥረቱን ይበልጥ የሚያባብስ ነው የሚል መግለጫ አውጥቷል፡፡ የቻይናው የውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ ለችግሩ መቃለል ዘላቂ እና አጠቃላይ የተኩስ አቁም የሚደረግበት መላ ቢፈለግ የተሻለ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ የሆርሙዝ ሰርጥ ጉዳይ በአለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ አቅርቦቱን ችግር እያባባሰው መምጣቱ ይነገራል፡፡ አሜሪካ የባህር መተላለፊያ ወሽመጡን ከሰኞ ቀን 8 ሰዓት አንስቶ ዘግቼዋለሁ ማለቷን መረጃው አስታውሷል፡፡ #ናይጀር
Apr 151 min read


የእግረ መንገድ ቱሪዝም ወይም (Stop Over Tourism)
ሚያዝያ 6/2018 የእግረ መንገድ ቱሪዝም ወይም ( #Stop_Over_Tourism) በመባል የሚታወቀው የቱሪዝም አይነት ተጓዦች ከአንዱ ወደ ሌላው ሃገር ለመጓዝ መሸጋገሪያ በሚያደርጉት ሃገር እግረ መንገዳቸውን የሚያደርጉት ጉብኝት ነው። ለዚህ ደግሞ በየዓመቱ ብዙ ሚሊዮኖች ለአየር በረራው መሸጋገሪያ የሚያደርጓት አዲስ አበባ ተመራጭ እየሆነች ነው ተብሏል። የቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የእግረ መንገድ ቱሪዝም "የስቶፕ ኦቨር ቱሪዝምን ለማሳደግ ያለመ የመግባቢያ ስምምነት ባለፈው ዓመት ነበር የተፈራረሙት። ከዚያስ በኋላ ምን እየተሰራ ነው ያልናቸው በዚህ ስራ ውስጥ በየደረጃው ካሉ የመንግስት ተቋማት መካከል አንዱ በሆነው የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ቢኒያም
Apr 142 min read


ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በጦርነት ጉዳይ ''ከዶናልድ ትራምፕ ጋር ንትርክ ውስጥ መግባት ባልሻም በጦርነት አውጋዥነቴ ግን እገፋበታለሁ'' አሉ፡፡
ሚያዝያ 6/2018 - ዓለም አቀፍ ወሬዎች #ካቶሊካዊት_ቤተ_ክርስቲያ የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በጦርነት ጉዳይ ከአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ንትርክ ውስጥ መግባት ባልሻም በጦርነት አውጋዥነቴ ግን እገፋበታለሁ አሉ፡፡ ቀደም ሲል ትራምፕ የካቶሊኩን ርዕሠ ጳጳስ ደካማ ሲሉ መጥራታቸውን አናዶሉ አስታውሷል፡፡ ሊዮ 14ኛ በአልጀሪ ጉብኝታቸው ወቅት ትራምፕ ያሻቸውን ቢሉም ጦርነትን በብርቱ ማውገዜን እገፋበታለሁ ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ እኔ የወንጌል ሰባኪ ነኝ በአለም ሰላም እንዲሰፍን ከመናገር ወደ ኋላ አልልም ብለዋል፡፡ ትራምፕ ቀደም ሲል ኢራን የኒኩሊር የጦር መሳሪያ ባለቤት መሆኗን የሚደግፍ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት አልፈልግም ማለታቸው መረጃው አስታውሷል፡፡ አሜሪካ እና ኢራን በጠላትነት ከተሰ
Apr 142 min read


የኢራን የደህንነት መስሪያ ቤት የበላይ መጂድ ካዴሚ በአሜሪካ እና በእስራኤል ጣምራ ጥቃት ተገደሉ ተባለ፡፡
መጋቢት 28/2018 የኢራን የደህንነት መስሪያ ቤት የበላይ መጂድ ካዴሚ በአሜሪካ እና በእስራኤል ጣምራ ጥቃት ተገደሉ ተባለ፡፡ ካዴሚ የተገደሉት አሜሪካ እና ኢራን ዛቻቸውን ከፍ ባደረጉበት አጋጣሚ እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡ የኢራን ሹሞችም ካዴሚ በአሜሪካ እና በእስራኤል ጣምራ ጥቃት መገደላቸውን አረጋግጠዋል ተብሏል፡፡ ጦርነቱ ከተጀመረ አንስቶ የቀድሞው የአገሪቱን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ ዓሊ ሐሚኒን ጨምሮ በርካታ ኢራናውያን የጦር እና የሲቪል ሹሞች ተገድለዋል፡፡ በኢራን ፣ በእስራኤል በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ እና በሳውዲ አረቢያ አዳዲስ ጥቃቶች መፈፀማቸው ተሰምቷል፡፡ ኢራን የጦርነት መቆሚያ መደራደሪያ ረቂቋን ማቅረቧ ታውቋል፡፡ ፓኪስታን በድርድሩ አስተናጋጅነት ስሟ ሲነሳ ሰምብቷል፡፡ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡.
Apr 61 min read


በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰው ጦርነት በኢትዮጵያ በዋጋ ግሽበት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚኖረው የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ተናገረ፡፡
መጋቢት 22/2018 በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰው ጦርነት በኢትዮጵያ በዋጋ ግሽበት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚኖረው የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ተናገረ፡፡ የኢራኑ ጦርነት በአለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ የአቅርቦት ሰንሰለት መቋረጥም እየፈጠረ መሆኑን ኮሚቴው ማስታወሱን ከብሔራዊ ባንክ ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡ ይህም በሃገር ውስጥ የዋጋ ግሽበት ሁኔታ ላይ ጫና እንደሚፈጥር ጠቅሶ የስጋቱ ጫና ግን መንግስት በሚወስደው የመቆጣጠሪያ እርምጃዎች እና ግጭቱ በሚቆይበት ጊዜ የሚወሰን ይሆናል ብሏል፡፡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊስ ኮሚቴው ስድስተኛ ዙር ስብሰባውን አካሄዶ የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎችን በመገምገም መግለጫ አውጥቷል፡፡ በቅርቡ ሁለት ገለልተኛና የመስኩ ባለሙያ የሆኑ አባላትን ያካተተው የገንዘብ ፖሊሲ ከታህሳስ ወር
Mar 312 min read


የታይዋኗ ርዕሠ ከተማ ታይፔ የቀድሞ ከንቲባ በጉቦ ቅሌት የ17 አመታት የእስር ቅጣት ተከናነቡ፡፡
መጋቢት 18/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #ታይዋን የታይዋኗ ርዕሠ ከተማ ታይፔ የቀድሞ ከንቲባ በጉቦ ቅሌት የ17 አመታት የእስር ቅጣት ተከናነቡ፡፡ ኮ ዌን ጄ የተባሉት የታይፔ የቀድሞ ከንቲባ ለ17 አመታት እስር ቅጣት የተዳረጉት የ532 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የምንዛሪ ግምት ያለው ገንዘብ በጉቦ መቀበላቸው ተረጋግጦባቸው እንደሆነ AFP ፅፏል፡፡ በተሰጣቸው ጉቦ ለውጥ ለሪል ስቴት አልሚዎች ከተፈቀደላቸው በላይ ሰፊ መሬት መምራታቸው ታውቋል፡፡ ግለሰቡ በጠበቆቻቸው አማካይነት ይግባኝ መጠየቃቸው ተጠቅሷል፡፡ ጉዳያቸው በይግባኝ እስኪታይም በዋስ ሆነው ውጤቱን ይጠባበቃሉ ተብሏል፡፡ #አሜሪካ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን በሰላሙ ጉዳይ ያለ አንዳች ማንገራገር ካልተስማማች ከእስካሁኑም የከፋ ከባድ ድብደባ ይጠብቃታል ሲሉ
Mar 273 min read


የእስራኤል ጦር ከኢራን ባህር ሀይል ከፍተኛ አዛዦች መካከል አንዱ የነበሩት አል ሬዛ ታንጂ ሲሪን ገደልኩት አለ፡፡
መጋቢት 17/2018 የእስራኤል ጦር ከኢራን ባህር ሀይል ከፍተኛ አዛዦች መካከል አንዱ የነበሩት አል ሬዛ ታንጂ ሲሪን ገደልኩት አለ፡፡ ታንጂ ሲሪ የተገደሉት ኢራን በከፊል ዝግ አድርገው በሰነበተችው የሆርሙዝ ሰርጥ ቅኝት ያደርጉ በነበረበት ወቅት እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡ ታንጂሲሪ ለሆርሙዝ ሰርጥ መዘጋት ከፍተኛ ድርሻ ከነበራቸው የኢራን የጦር መሪዎች መካከል አንዱ እንደነበሩ የእስራኤሉ የመከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ ተናግረዋል፡፡ ወደ ወር በተቃረበው ጦርነት በአሜሪካ እና እስራኤል ጥምር ድብደባ በርካታ የኢራን ሲቪል እና የጦር መሪዎች መገደላቸው ይነገራል፡፡ ታንጂ ሲሪ በእስራኤል የአየር ጥቃት ተገድለዋል ስለመባሉ ለጊዜው ከኢራን በኩል የተሰማ አስተያየት የለም ተብሏል፡፡ ያም ሆኖ ኢራንን በአሜሪካ እና በእስራኤል ለሚፈፀምባት ድብደባ ምላሽ ከመ
Mar 261 min read


መጋቢት 16/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ኢራን ለኢራን ጠቅላይ የደህንነት ምክር ቤት አዲስ የበላይ ተሰየሙ፡፡ የምክር ቤቱ የበላይ ሆነው የተሰየሙት ሞሐመድ ባጌር ዘልግ ሐድር እንደሆኑ ሚድል ኢስት ሞኒተር ፅፏል፡፡ የቀድሞው የምክር ቤቱ የበላይ ዓሊ ላርጃኒ ባለፈው ሳምንት በእስራኤል ጥቃት መገደላቸው ሲነገር ሰንብቷል፡፡ ላርጃኒን ተከትሎም የቀድሞው የደህንነት ሚኒስትርም ተገድለዋል፡፡ ከ3 ሳምንታት በላይ ባስቆጠረው ጦርነት የቀድሞው ጠቅላይ መሪ አሙያቶላህ ዓሊ ሐሚኒን ጨምሮ በርካታ ሹሞች መገደላቸው ይነገራል፡፡ በጦርነቱ በአገሪቱ ከ1300 በላይ ሰዎች ተገድለዋል ተብሏል፡፡ ኢራንም በእስራኤል እና የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች በሚገኙባቸው የአረብ አገሮች የአፀፋ የሚሳየል እና የድሮን ጥቃት እየሰነዘረች መሆኑን መረጃው አስታውሷል፡፡ #አሜሪካ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ በጦርነቱ ማብቂያ
Mar 252 min read


የእስራኤሉ የመከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ የኢራኑን የደህንነት ሚኒስትር ኢስማኢል ካቲብንም ገደልነው አሉ፡፡
መጋቢት 9/2018 የእስራኤሉ የመከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ የኢራኑን የደህንነት ሚኒስትር ኢስማኢል ካቲብንም ገደልነው አሉ፡፡ ቀደም ሲል እስራኤል የኢራን የደህንነት ምክር ቤት ሰብሳቢ የነበሩትን ዓሊ ላርጃኒን መግደሏን ቢቢሲ አስታውሷል፡፡ የላርጃኒን መገደል የኢራን ሹሞችም አረጋግጠዋል፡፡ ስለ ኢስማኢል ካቲብ መገደል ግን የሰጡት ማረጋገጫም ይሁን ማስተባበያ የለም፡፡ በጦርነቱ መጀመሪያ በአሜሪካ እና በእስራኤል ጣምራ ድብደባ የቀድሞው የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ ዓሊ ሐሚኒ አና ሌሎች ከፍተኛ ሃላፊዎች መገደላቸው ይታወቃል፡፡ የኢራን ባለስልጣናት በመሪዎቻችን ላይ የተፈፀመውን ግድያ እንበቀላለን እያሉ ነው፡፡ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https:/
Mar 181 min read


''የኢራኑን የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ሀላፊ ዓሊ ላርጃኒን ገድለነዋል'' እስራኤል
መጋቢት 8/2018 የእስራኤሉ የመከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ የኢራኑን የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ሀላፊ ዓሊ ላርጃኒን ገድለነዋል አሉ፡፡ ካትዝ እንደተናገሩት ላርጃኒ የተገደሉት እስራኤል ትናንት ለዛሬ አጥቢያ ኢራን ውስጥ በፈፀመችው ድብደባ ነው፡፡ ዓሊ ላርጃኒ ከሁለት ሳምንታት በፊት በአሜሪካ እና በእስራኤል ጣምራ ጥቃት የተገደሉትን የቀድሞውን ጠቅላይ መሪ አያቶላ ዓሊ ሐሚኒን ለመተካት በእጩነት ከቀረቡት አንዱ ነበሩ፡፡ አባታቸውን በመወከል በጠቅላይ መሪነት የተመረጡት ሞጅታባ ሐሚኒ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ ዓሊ ላርጃኒ በእስራኤል ጥቃት ተገድለዋል ስለመባሉ እስካሁን ከኢራን በኩል ማረጋገጫም ይሁን ማስተባበያ እንዳልተሰጠ ሬውተርስ ፅፏል፡፡
Mar 171 min read


እስራኤል በመላዋ ኢራን በአገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤት ቢሮዎች እና ፅህፈት ቤቶች በላይ ያነጣጠረ ታላቅ ድብደባ ፈፀምኩ አለች፡፡
የካቲት 25/2018 እስራኤል በመላዋ ኢራን በአገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤት ቢሮዎች እና ፅህፈት ቤቶች በላይ ያነጣጠረ ታላቅ ድብደባ ፈፀምኩ አለች፡፡ በሊባኖስ ድብደባ እየፈፀመች መሆኑን ቢቢሲ ፅፏል፡፡ የርዕሰ ከተማዋ ቤይሩት ደቡባዊ ክፍል ነዋሪዎችም አካባቢውን ለቅቀው እንዲወጡ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች ተብሏል፡፡ እስራኤል እና አሜሪካ በጣምራ በኢራን ላይ ድብደባ መፈፀም ከጀመሩ ወዲህ የሊባኖሱ ታጣቂ ቡድን ሔዝቦላህ ወሰን አሻግሮ ወደ እስራኤል ሮኬቶችን እየተኮሰ መሆኑ ይነገራል፡፡ የሊባኖሷ ርዕሰ ከተማ ቤይሩት ደቡባዊ ክፍል የሄዝቦላህ መሪዎች መናኽሪያ ነው ይባላል፡፡ ሔዝቦላህ የኢራን የጦር እና የፖለቲካ አጋር እንደሆነች መረጃው አስታውሷል፡፡ በሌላ መረጃ ሲሪላንካ አቅራቢያ የኢራን የጦር መርከብ መስመጡ ተሰምቷል፡፡ በኔፓን የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች የ
Mar 41 min read


የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን የአየር እና የባህር ሀይሎች እንዳልነበሩ አድርገን አውድመናቸዋል አሉ፡፡
የካቲት 25/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #አሜሪካ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን የአየር እና የባህር ሀይሎች እንዳልነበሩ አድርገን አውድመናቸዋል አሉ፡፡ ትራምፕ የኢራንን የአየር እና የባህር ሀይሎች እንዳልነበሩ አድርገን ደምስሰናቸዋል ያሉት በዋይት ሐውስ ከጀርመኑ መራሄ መንግስት ፍሬድሪክ ሜርዝ ጋር ከተመካከሩ በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሆነ አልጀዚራ ፅፏል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኢራን የባህር እና የአየር ሀይል እንዳይኖራት ማድረጋቸው ትራምፕ ተናግረዋል፡፡ አሜሪካ እና እስራኤል ካለፈው ሳምንት ቅዳሜ አንስቶ በጣምራ በኢራን ላይ ከባድ ድብደባ እየፈፀሙ ነው፡፡ ቢቢሲ እንደፃፈው ትራምፕ የኢራንን የጦር አቅም አነካክቼዋለሁ ቢሉም ፋርሳዊቱ አገር በእስራኤል እና በቀጠናው በሚገኙ የአሜሪካ ተቋሞች ላይ የአፀፋ ጥ
Mar 42 min read


የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ ኢራንን ለመምታት መዘጋጀቱን ተሰማ፡፡
የካቲት 12/2018 የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ ኢራንን ለመምታት መዘጋጀቱን ተሰማ፡፡ ዋሽንግተንን ቴህራንን በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት ለመምታት ዝግጅት ማድረጓን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ሰዎች ነግረውናል ብሎ የዘገበው ሲ ኤን ኤን ነው፡፡ ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግን የመጨረሻውን ውሳኔ አለመስጠታቸው በመረጃ ተጠቅሷል፡፡ የአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ከፍተኛ ባለስልጣናት በትላንትናው እለት በዋይት ሐውስ ተገኝተው በኢራን ጉዳይ ላይ ውይይት ማድረጋቸውም ተነግሯል፡፡ ትራምፕም ከኢራን ጋር ስለተደረገው ድርድር ሁኔታ ከልዩ መልዕክተኛው ስቲቭ ዊትኮፍ እና ከአማቻቸው ጃሬድ ኩሽነር ማብራሪያ እንደተሰጣቸው በመረጃው ተነስቷል፡፡ አሜሪካና ኢራን ያደረጉት ትራምፕ ቀይ መስመር በሚላቸው ጉዳዮች ላይ አሁንም ከስምምነት አለመድረሱ ተዘግቧል፡፡
Feb 191 min read


ኢራን የሆርሙዝ ሰርጥን በጊዜያዊነት መዝጋቷ ተሰማ ።
የካቲት 11/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #ኢራን ኢራን የሆርሙዝ ሰርጥን በጊዜያዊነት መዝጋቷ ተሰማ ። ሰርጡ የተዘጋው *የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ* በአካባቢው የባህር ሃይል ልምምድ ስለሚያደርግ ነው ተብሏል። ልምምዱ አሜሪካ በአረብ ባህር አካባቢ ወታደራዊ አቅሟን እያደረጀች መምጣቷን ተከትሎ የሚካሄድ እንደሆነ ዘ ቴሌግራፍ ጽፏል። ዋሽንግተን አውሮፕላን ተሸኳሚ የጦር መርከብን ጨምሮ ወታደሮችን ከዘመን አፈራሽ የውጊያ መሳሪያዎች ጋር ወደ አካባቢው መላኳ ተነግሯል። የኢራን እርምጃ ሁለቱ ሀገራት አለመግባባታቸውን ለመፍታት በጄኔቫ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ላይ እያሉ የተሰማም ነው። ኢራን የሆርሙዝ መተላለፊያን ስትዘጋ እንደ ጎርጎርሳውያኑ አቆጣጠር ከ1980ዎቹ ወዲህ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ተብሏል። #ሩሲያ ሩሲያ በባልቲክ ሀገራት ላይ ወረራ ከፈ
Feb 181 min read


ጥር 27/2018 – የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ሱዳን የሱዳን ወታደራዊ መንግስት እና የአገሪቱ ጦር የበላይ ጄኔራል አብዱልፈታህ አል ቡርሃን የአገሪቱ ጦር የደቡብ ኮርዶፋኗን ዋና ከተማ ካዱግሊን ከተቀሩት ክፍሎች ጋር የሚያገናኘውን አውራ ጎዳና በእጁ ማስገባቱን ተናገሩ፡፡ ጦሩ የRSF ፈጥኖ ደራሽ ሀይል በካዱግሊ ፈጥሮት የነበረውን ከበባ ጥሶ እንደወጣ አል ቡርሃን መናገራቸውን አልጀዚራ ፅፏል፡፡ አብዱልፈታህ አልቡርሃን የደቡብ ኮርዳፋኗን ከተማ ከተቀሩት የአገሪቱ ክፍሎች ጋር የሚያገናኘውን አውራ ጎዳና ተቆጣጥረነዋል ያሉት በኦምዱርማን በሚገኘው የአገሪቱ ዋና የቴሌቪዥን ጣቢያ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ነው ተብሏል፡፡ ጄኔራል አል ቡርሃን ከRSF ጋር በጭራሽ የተኩስ አቁም አናደርግም ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ የአገሪቱ ወታደራዊ መሪ የተኩስ አቁም RSF መልሶ እንዲያንሰራራ ስለሚያደርገው
Feb 42 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

