top of page


ከሳምንት በፊት ከናይጄርያ ኬቢ ግዛት አዳሪ ትምህርት ቤት ታግተው የተወሰዱ ሴት ተማሪዎች በሙሉ ተለቀቁ፡፡
ህዳር 17 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #ናይጄርያ ከሳምንት በፊት ከናይጄርያ ኬቢ ግዛት አዳሪ ትምህርት ቤት ታግተው የተወሰዱ ሴት ተማሪዎች በሙሉ ተለቀቁ፡፡ በጊዜው 25 ሴት ተማሪዎች ታግተው እንደነበር ቢቢሲ አስታውሷል፡፡ አንዷ አስቀድሞ ከአጋቾቿ ማምለጧ ሲነገር ሰንብቷል፡፡ ታጋቾቹን ሴት ተማሪዎች ለማስለቀቅ የናይጀሪያ የፀጥታ ሀይሎች በፕሬዘዳንት ቦላ ቲኑቡ ትዕዛዝ በቅንጅት አሰሳ ላይ ተሰማርተው ነበር፡፡ ሴት ተማሪዎቹ ከእገታ ተለቀዋል ቢባልም በምን ዓይነት ሁኔታ እንደተለቀቁ የተብራራ ነገር የለም፡፡ ባለፈው ሳምንት አርብ ደግሞ ከኒጀር ግዛት የካቶሊክ ትምህርት ቤት ከ250 በላይ ተማሪዎች ታግተው መወሰዳቸውን መረጃው አስታውሷል፡፡ ከኒጀር ግዛት ታግተው የተወሰዱት ተማሪዎች ግን እንዳልተለቀቁ ተጠቅሷል፡፡ #ብራዚል
Nov 262 min read


ህዳር 16 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ቻይና የቻይናው ፕሬዘዳንት ሺ ጂን ፒንግ ታይዋን ከእናት አገሯ ጋር መቀላቀሏ በአሁኑ ወቅት እጅግ አስፈላጊ ጉዳይ ነው አሉ፡፡ ሺ ጂን ፒንግ ስለዚሁ ጉዳይ በስልክ ለአሜሪካው አቻቸው ዶናልድ ትራምፕ እንደነገሯቸው የቻይና መንግስታዊ መገናኛ ብዙሃን ማውራታቸው አናዶሉ ፅፏል፡፡ ታይዋን ራሴን የቻልኩ ነፃ አገር ነኝ ብትልም ቻይና ግን ታይዋንን እንዳፈነገጠች የገዛ ግዛቷ አድርጋ ትቆጥራታለች፡፡ የቻይና መንግስት እና አድራጊ ፈጣሪው የቻይና ኮሚኒስቶች የፖለቲካ ማህበር ቀደም ሲል ታይዋን በዚያም ሆነ በዚህ መልሳ የቻይና አካል መሆኗ አይቀርም ሲሉ ቆይተዋል፡፡ በአዲሱ የቻይና ፕሬዘዳንት የታይዋን አቋም የአሜሪካ ይፋዊ አስተያየት ምን እንደሆነ አልተሰማም፡፡ ቻይና ቀደም ሲል በታይዋን ዙሪያ ገባ ታላላቅ የጦር ልምምዶችን ማድረጓን መረጃው አስታውሷል፡፡ #አ
Nov 251 min read


ህዳር 15 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ናይጄርያ ከናይጄርያዋ ኒጀር ግዛት የአንድ የካቶሊክ ትምህርት ቤት ከታገቱት ከ300 በላይ ተማሪዎች መካከል ሃምሳው ከአጋቶቻቸው ማምለጣቸው ተሰምቷል፡፡ ጉዳዩን የሚከታተለው ቡድን 50ው ተማሪዎች ከአጋቾቻቸው ማምለጣቸውን አረጋግጫለሁ ማለቱን ቢቢሲ ፅፏል፡፡ ይሁንና በምን ሁኔታ እና ከየት እንዳመለጡ አላብራራም፡፡ አምላጮቹ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተቀላቅለዋል ማለቱ ተሰምቷል፡፡ የናይጀሪያ የፀጥታ ሀይሎች ታጋቾቹን ለማስለቀቅ በተቀናጀ አሰሳ ላይ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ባለፈው ሳምንት መጀመሪያም በኬቢ ግዛት ከሚገኝ አንድ አዳሪ ትምህርት ቤት 20 ተማሪዎች ታግተው መወሰዳቸውን መረጃው አስታውሷል፡፡ እገታውን በመስጋት ብዙዎቹ የናይጀሪያ ግዛቶች ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉ ማድረጋቸው በመረጃው ተጠቅሷል፡፡ #ሳውዲ_አረቢያ ሳውዲ አረቢያ በ1
Nov 242 min read


ጥቅምት 29 2018 - ጥቅምት 29 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#አሜሪካ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን በደቡብ አፍሪካ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የቡድን 20 አባል አገሮች ጉባኤ አይገኝም አሉ፡፡ የአሜሪካውፕሬዘዳንት አፍሪካ ነርስ በተሰኙት ነጭ ደቡብ አፍሪካዊያን ላይ እልቂት እና ማሳደዱ በርትቶባቸዋል የሚል ክሳቸውን እየደጋገሙት መሆኑን አናዶሉ አስታውሷል፡፡ የፕሬዘዳንት ሲሪል ራማፎሳ መንግስት በትራምፕ የሚቀርበውን ውንጀላ በተደጋጋሚ እያስተባበለ ነው፡፡ ትራምፕ ግን የደቡብ አፍሪካን መንግስት ጥምድ አድርገው እንደያዙት ነው፡፡ እንደውም ደቡብ አፍሪካ ከቡድን 20 አባል አገርነቷ ልትባረር ይገባል ያሉት ሰሞኑን ነው፡፡ የቡድን 20 አባል አገሮች ስብሰባ በደቡብ አፍሪካ ቢካሄድም ያለ አሜሪካ ተሳትፎ ይሆናል ተብሏል፡፡ #ማሊ በምዕራብ አፍሪካዊቱ ሀገር ማሊ
Nov 81 min read


ጥቅምት 28 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ካሜሮን የካሜሮኑ አረጋዊ ፕሬዘዳንት ፖል ቢያ ለ8ኛ ጊዜ ቃለ መሐላ በመፈፀም አዲሱን ሀላፊነታቸውን ተረከቡ፡፡ ፖል ቢያ ለ8ኛ ጊዜ ቃለ መሐላ በመፈፀም ሀላፊነታቸው የተረከቡት በቅርብ ጊዜው የካሜሩን ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ አሸንፈዋል ከተባለ በኋላ እንደሆነ አልጀዚራ ፅፏል፡፡ የ92 አመቱ አረጋዊ ፖል ቢያ እስካሁን ካሜሮንን ከ40 አመታት በላይ መርተዋታል፡፡ በአሁኑ ጊዜም ከአገር መሪዎቹ መካከል በእድሜ አንጋፋው እሳቸው ናቸው፡፡ ፖል ቢያ በምርጫው አሸንፈዋል የተባለው ሁነኛ ተፎካካሪዎች ከምርጫ በታገዱበት አጋጣሚ ነው ተብሏል፡፡ ተቃዋሚዎች ፖል ቢያ አሸናፊ የተደረጉበትን ምርጫ ህገ መንግስታዊ ጠለፋ ነው ሲሉ እየጠሩት መሆኑን መረጃው አስታውሷል፡፡ #ሩሲያ ሩሲያ የአሜሪካ የወረራ ስጋት ተጋርጦብኛል ለትምትለው የደቡብ አሜሪካዋ አገ
Nov 72 min read


ጥቅምት 27 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ፊሊፒንስ ፊሊፒንስን ሰሞኑን በመታት ከባድ አውሎ ነፋስ የሟቾቹ ብዛት ከ140 በላይ መድረሱ ተሰማ፡፡ አውሎ ነፋሱ በከባድ ጎርፍ እና በመሬት መንሸራተት ጭምር የታገዘ እንደነበር AFP አስታውሷል፡፡ በአደጋው ከሞቱት እና አካላዊ ጉዳት ከገጠማቸው ሌላ 127 ሰዎች ደግሞ እስካሁን የደረሱበት አልታወቀም ተብሏል፡፡ ይህም የሟቾቹ ብዛት ከተጠቀሰውም በላይ ሊጨምር ይችላል የሚል ስጋት አሳድሯል፡፡ ሴቡ የተባለችዋ ግዛት ዋነኛዋ የአደጋው ሰለባ ነች፡፡ በግዛቲቱ የደረሰው ጎርፍ እና የመሬት መንሸራተት ከዚህ ቀደም ከደረሱት ሁሉ በእጅጉ ከባድ ነበር ተብሏል፡፡ ጎርፉ መኪኖችን እና ትልልቅ ኮንቴይነሮችን ጭምር አንከብክቦ መጋለቡ ታውቋል፡፡ ለፊሊፒንሱ አውሎ ነፋስ ፣ ጎርፍ እና የመሬት መንሸራተት አደጋ የአየር ለውጡ በዋና ምክንያትነት እየቀረ
Nov 62 min read


ጥቅምት 25 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ኢራን የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አርጋቺ አገሬ ከአሜሪካ ጋር ወደ ኒኩሊየር ነኩ ንግግር ለመመለስ የሚያጣድፉት ጉዳይ የለም አሉ፡፡ አርጋቺ ከአሜሪካ ጋር በእኩልነት ደረጃ ካልሆነ በስተቀር አንዳችም ንግግር ማድረግ እንደማትሻ መናገራቸውን አልጀዚራ ፅፏል፡፡ አሜሪካ ኢራን በጭራሽ ዩራኒየም ማብላላት የለባትም የሚል አቋም አላት፡፡ አዲሱ የአሜሪካ የንግግር ሀሳብም በዚሁ ጉዳይ ላይ የሚያተኩር ነው ይባላል፡፡ ኢራን ደግሞ ይሄን በጭራሽ አልቀበልም ባይ ነች፡፡ ምዕራባዊያኑ ኃያላን ኢራን የኒኩሊየር ቦምብ የመስራት ውጥን አላት ሲሉ ይከሷታል፡፡ ቴሕራን በበኩሏ የኒኩሊዩር መርሐ ግብሬ ለኤሌክትሪክ ማመንጫ እና ለሰላማዊ አገልግሎት የታለመ ነው የሚል መሟገቻ ታቀርባለች፡፡ #ሜክሲኮ ፔሩ ከሜክሲኮ ጋር የነበራትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አቋረጠች፡፡ ፔሩ ዲ
Nov 42 min read


ኢትዮጵያ በመካከለኛ የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ዝርጋታ አቅሟን ለማሳደግ ከፈረንሳይ ተቋም ጋር ውል አሰረች፡፡
ጥቅምት 25 2018 ኢትዮጵያ በመካከለኛ የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ዝርጋታ አቅሟን ለማሳደግ ከፈረንሳይ ተቋም ጋር ውል አሰረች፡፡ የመካከለኛ የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ተጠቃሚዎች የሆኑት ኢንዱስትሪዎች መሆኑ የተነገረ ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሚያስተዳድራቸው እና ከሚመራቸው መስመሮች አንዱ መሆኑ ተነግሯል፡፡ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የመካከለኛ መስመር ዝርጋታ አቅምን ለማሳደግ የተፈራረመችው ከፈረንሣዩ 'ኤሊክቲሪሲቲ ደ ፍራንስ' (EDF) ጋር መሆኑን ሰምተናል፡፡ በሌላ በኩል አገልግሎቱ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ግብዓቶች ከሚያመርት የኬንያ ኩባንያ ጋር ውይይት ማረጉን ተናግሯል፡፡ ተቋሙ ከኩባንያው ጋር የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ግብዓቶችን በኢትዮጵያ ማምረት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መወያየቱን የሰማን ሲሆን
Nov 41 min read


ጥቅምት 19 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ብራዚል የብራዚል ፖሊስ የሬዮ ዴ ጄኒየሮ ከተማን ከተደራጁ ወሮበሎች ለማፅዳት ባካሄደው ዘመቻ በጥቂቱ 64 ሰዎች ተገደሉ ተባለ፡፡ ከተማይቱ በቅርቡ አለም አቀፋዊ የአየር ለውጥ ጉባኤን እንደምታስተናግድ ሬውተርስ ፅፏል፡፡ ፖሊስ ለዚህ ጉባኤ ቅድመ ዝግጅት ሬዮ ዴ ጄኔሮን ከወሮበሎች ለማፅዳት በዘመቻ ላይ ነው ተብሏል፡፡ በአጋጣሚው በተፈጠረው ግጭት ከተገደሉ 64 ሰዎች መካከል 4ቱ የፖሊስ መኮንኖች መሆናቸው ታውቋል፡፡ በትናንቱ ዘመቻ 2 ሺህ 500 ፖሊሶች እና ሌሎች የፀጥታ ባልደረቦች መካፈላቸው ተጠቅሷል፡፡ በግጭቱ በፀጥታ ባልደረቦቹ እና በተደራጁት ወሮበሎች መካከል የተኩስ ልውውጥ እንደነበር መረጃው አስታውሷል፡፡ ፖሊስ ከ80 በላይ የተደራጁ ወሮበሎችን አስሬያለሁ ማለቱ በመረጃው ተጠቅሷል፡፡ #ቤኒን በቤኒን የዋነኛው ተቃዋሚ
Oct 292 min read


ጥቅምት 17 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ቱርክ በቱርክ PKK የተሰኘው የኩርዶች የቀድሞ አማጺ ቡድን ታጣቂዎቹን ከቱርክ ወደ ኢራቅ ማስወጣት ጀመረ፡፡ PKK ታጣቂዎቹን ወደ ኢራቅ ማስወጣት የጀመረው ከቱርክ መንግስት ጋር በጀመረው የሰላም ሒደት መሰረት እንደሆነ አሶሼትድ ፕሬስ ፅፏል፡፡ የኩርዶቹ ታጣቂ ቡድን ከእንግዲህ የትጥቅ አመፅ እርም ይሁንብኝ ያለው ባለፈው አመት ግንቦት ወር ላይ እንደነበር መረጃው አስታውሷል፡፡ በትጥቅ መፍታት ሒደት ላይ ይገኛል ተብሏል፡፡ PKK ታጣቂነቱን ትቶ በሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ብቻ የመቀጠል ፍላጎት እንዳለው ተጠቅሷል፡፡ ቡድኑ ለወሰደው እርምጃ አስተማማኝነት የቱርክ መንግስት PKK ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ማህበርነት የሚለወጥበትን ሁኔታ እንዲያመቻችለት መጠየቁ ተሰምቷል፡፡ PKK የትጥቅ አመፅ እርም ይሁንብኝ ያለው ከ40 አመታት በኋላ እንደሆነ መረጃው አስታውሷ
Oct 272 min read


ጥቅምት 13 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ሱዳን በሱዳን የRSF ፈጥኖ ደራሽ ሀይል ከአገሪቱ ኤርፖርቶች የሚነሱ እና በኤርፖቶቹ የሚያርፉ አውሮፕላኖችን በሙሉ አወድማለሁ ሲል ዛተ፡፡ ዛቻውን ያሰሙ የፈጥኖ ደራሹ ሀይሉ አዛዥ ሌተና ጄኔራል ሞሐመድ ሐምዳን ዳጋሎ እንደሆኑ ሱዳንስ ፖስት ፅፏል፡፡ ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ትናንት ወደ አገልግሎት ተመልሷል በተባለው የካርቱም ኤርፖርት ላይ ተደጋጋሚ የድሮን ጥቃት ሰንዝሯል ተብሏል፡፡ የካርቱም ኤርፖርት ትናንት ከ2 ዓመታት በኋላ የመጀመሪያውን የሀገር ውስጥ በረራ አውሮፕላን ማስተናገዱ ታውቋል፡፡ ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ከሱዳን መንግስት ጦር ጋር ሲዋጋ ከ2 ዓመታት ከመንፈቅ በላይ ሆኖታል፡፡ ጦርነቱን ማቆሚያ አንዳችም ፍንጭ አይታይም፡፡ #አሜሪካ በአሜሪካ በሁለት የሩሲያ ታላላቅ የነዳጅ ኩባንያዎች ላይ ያነጣጠረ አዲስ ማዕቀብ ጣለች፡፡ ማዕቀቡ የተጣለባቸው ሮስ
Oct 232 min read


ጥቅምት 12 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ካሜሩን በካሜሩን ከሳምንት በፊት በተካሄደው ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ አረጋዊው የአገሪቱ መሪ ፖል ቢያ እንዳሸነፉ የቅድሚያ ውጤቱ አሳየ ተባለ፡፡ የአገሪቱ የምርጫ አከናዋኝ መስሪያ ቤት በቅድሚያ ውጤቱ ፖል ቢያ ለፕሬዘዳንታው ምርጫው ከተሰጠው ድምፅ 53 በመቶውን በማግኘት አሸንፈዋል ማለቱን አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡ የፖል ቢያ የቅርብ ተፎካካሪ ኢሳ ቺሮማ ባካሪ ያገኙት ድምፅ 35 በመቶ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ ባካሪ ከምርጫው በኋላ በተደጋጋሚ አሸንፌያለሁ ሲሉ ሰንብተዋል፡፡ ኢሣ ቺሮማ ባካሪ ውጤቱ በወጉ ይጣራልኝ ማለት መጀመራቸው ተሰምቷል፡፡ የ92 አመቱ አረጋዊ ፖል ቢያ የምርጫ ድላቸው ከፀናላቸው የ42 አመታት መሪነታቸውን በመ5 ዓመታት ይጨምርላቸዋል ተብሏል፡፡ የአገሪቱ ህገ መንግስታዊ ምክር ቤት ይፋዊ ውጤቱን ሰሞኑን እወቁት እንደሚል በመረጃው ተጠቅሷል፡፡
Oct 222 min read


ጥቅምት 11 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ፈረንሳይ የፈረንሳይ ሹሞች እጅግ ውድ የአገራችንን ቅርሶች ማስጠበቅ ተስኖናል ሲሉ በፀፀት ተናገሩ፡፡ የሹሞቹ አስተያየት የተሰማው በርዕሰ ከተማዋ ፓሪስ ከሚገኘው የሉቨር ቤተ መዘክር ውድ ጌጣ ጌጦች ከተሰረቁ በኋላ እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡ ጌጣ ጌጦቹ የአገሪቱ ቅርሶችም በመሆናቸው በዋጋ እንደማይታመኑ እየተነገረ ነው፡፡ ከተዘረፉት ቅርሶች መካከል የፈረንሳዩ ንጉሰ ነገስት ናፖሊዮን በናፖርት ለባለቤቱ አበርክቶለት የነበረ በአልማዝ የተንቆጠቆጠ ሐብልም ይገኝበታል ተብሏል፡፡ ዘራፊዎቹ ላይ በፍጥነት ካልተደረሰባቸው ቅርሶቹን በማወላለቅ በትንሽ በትንሹ ወደ ውጭ አገራት ሊያሸሿቸው ይችላሉ የሚል ስጋት አሳድሯል፡፡ የፓሪሱ ዘረፋ በመሰል ቤተ መዘክሮች የደህንነት ጥበቃው በእጅጉ እንዲጠናከር የማንቂያ ደወል ሆኗል ተብሏል፡፡ የቤተ መዘክሩ የቅርሶች ዘረፋ በአገሪቱ
Oct 212 min read


ጥቅምት 10 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#እስራኤል እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ዳግም የአየር ድብደባዋን ፈፀመች ተባለ፡፡ የእስራኤል ጦር ዳግም የአየር ድብደባውን የቀጠለው በጋዛ ደቡባዊ ክፍል እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡ ለደቡባዊ ጋዛው የአየር ድብደባ እስራኤል በሐማስ ትንኮሳ ተፈፅሞብኛ የሚል ክስ ማቅረቧን ተሰምቷል፡፡ የእስራኤል ጦር በሐማስ ፀረ ታንክ ሚሳየል ተተኩሶብኛ ብሏል፡፡ የፍልስጤማውያኑ ታጣቂ ቡድን ሐማስ በፊናው አንዲትም ጥይት አልተኮስኩም ማለቱ ተሰምቷል፡፡ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለጋዛ ሰላም ባቀረቡት ባለ 20 ነጥቦች የሰላም እቅድ ተፋላሚዎቹ በተኩስ አቁም ሰንብተዋል፡፡ ይሁንና እስራኤል እና ሐማስ በተኩስ አቁም መጣስ መካሰሳቸው ተደጋግሟል፡፡ የእስራኤል ጦር ከትናንቱ የጋዛ የአየር ድብደባ በኋላ ወደ ተኩስ አቁሙ ተመልሻለሁ ማለቱ ተሰምቷል፡፡ #ኬንያ የኬንያ የቀድሞ
Oct 202 min read


ጥቅምት 7 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ሕንድ የሕንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሕንድ የሩሲያን የነዳጅ ዘይት መግዛት እንደምታቆም ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራሞዲ ማረጋገጫ ሰጥተውኛ ስለማለታቸው የምናውቀው ነገር የለም አለ፡፡ ትራምፕ ከትናንት በስቲያ ሕንድ የሩሲያን ነዳጅ መግዛት እንደምታቆም ማረጋገጫ አግኝቻቸው ሲሉ መናገራቸውን ቢቢሲ አስታውሷል፡፡ የህንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ቃል አቀባይ በትራምፕ እና በናሬንድራ ሞዲ መካከል ይህን መሰል ንግግር ስለመደረጉ አላውቅም ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ በጉዳዩ ላይ ከዚህ ቀደም ንግግረግ ቢደረግም ነዳጁ ግዢውን ስለማቆም የተደረሰ መደምደሚያ የለም ብለዋል፡፡ የህንድ መንግስት በዚህ ጉዳይ ባወጣው መግለጫ እኛ የምናስቀድመው የአገሪቱን ፍላጎት እና የኢነርጂ ዋስትና ነው ማለቱ ተጠቅሷል፡፡ ሕንድ ከቻይና በመቀ
Oct 172 min read


ጥቅምት 6 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#የአፍሪካ_ህብረት የአፍሪካ ህብረት ወታደራዊ የመንግስት ግልበጣ የተደረገባትን ማዳጋስካርን ከአባልነት አግጃለሁ ማለቱ ተሰማ፡፡ በዚያ ካፕሳት የተሰኘው ልዩ የጦር ክፍል መኮንኖች የፕሬዘዳንት አንድሬይ ራጆሊናን መንግስት ማስወገዳቸውን እወቁልን ያሉት መሰንበቻው እንደሆነ አልጀዚራ ፅፏል፡፡ የጦር መኮንኖቹ መንግስታዊ ስልጣኑን የተቆጣጠሩት አገሪቱ ከ2 ሳምንታት በላይ በተቃውሞ ስትናጥ ከሰነበተች በኋላ ነው፡፡ የአገሪቱ ህገ መንግስታዊ ፍርድ ቤት የገልባጮቹ አለቃ ኮሎኔል ሚካኤል ራንድ ኒሪያናን ጊዜያዊ ፕሬዘዳንት እንዲሆኑ ፈቅዶላቸዋል፡፡ የገልባጮቹ አለቃ በነገው እለት ቃለ መሐላ በመፈፀም ሀላፊነታቸው ይረከባሉ ተብሏል፡፡ ከዚያ አስቀድሞ ግን የአፍሪካ ህብረት ማዳጋስካርን ከአፍሪካ ህብረት አባልነትዋ አግጃለሁ ማለቱ ተሰምቷል፡፡ #ቬኒዙዌላ የቬኒዙዌላው ፕሬ
Oct 163 min read


ጥቅምት 3 2018 - የባህር ማዶ ወሬዎች
#ማሊ ምዕራብ አፍሪካዊቱ አገር ማሊ አሜሪካውያንም ወደኛ ለመምጣት ለቪዛ ሲያመለክቱ እስከ 10 ሺህ ዶላር የሚደርስ የዋስትና ገንዘብ እንዲያሲዙ ልጠይቅ ነው አለች፡፡ ቀደም ሲል አሜሪካ ከተለያዩ የአፍሪካ አገሮች ቪዛ የሚጠይቁ ከ5 እስከ 10 ሺህ ዶላር የዋስትና ገንዘብ እንዲያሲዙ የሚጠይቅ አሰራር ተግባራዊ እንደምታደርግ እወቁልኝ ካለች መሰንበቷን አናዶሉ አስታውሳል፡፡ አዲሱ አሰራሯን ከ10 ቀናት ባልበለጠ ጊዜ ተግባራዊ ማድረግ እንደምትጀምር ታውቋል፡፡ የማሊ መንግስት መግለጫም ለአዲሱ የአሜሪካ የቪዛ መመሪያ ምላሽ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ የማላዊ እና የዛምቢያ መንገደኞች የአሜሪካ ቪዛ ለማግኘት ለቃለ መጠይቅ ከመቅረባቸው አስቀድሞ ከ5 እስከ 15 ሺህ የአሜሪካ ዶላር በዋስትና ማስያዝ እንደሚጠበቅባቸው መረጃው አስታውሷል፡፡ #ካሜሮን ካሜሩናውያን ቀጣይ ፕሬዘ
Oct 132 min read


መስከረም 28 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ፈረንሳይ ፖለቲካዊ ቀውሷ እየተባባሰ የመጣው የፈረንሳይ ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ስልጣን እንዲለቁ እና አጣዳፊ ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ ሊጠሩ ይገባል ተባለ፡፡ ሀሳቡን ያቀረቡት በአስተዳደራቸው የመጀመሪያው ጠቅላይ...
Oct 82 min read


መስከረም 26 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ሶማሊያ የሶማሊያው ፅንፈኛ ቡድን /አልሸባብ/ በርዕሰ ከተማዋ ሞቃዲሾ በሚገኝ እስር ቤት ላይ ጥቃት መፈፀሙ ተሰማ፡፡ በአልሸባብ ታጣቂዎች ጥቃት ደርሶበታል የተባለው የእስር ማዕከል በአገሪቱ ቤተ መንግስት አቅራቢያ...
Oct 62 min read


መስከረም 23 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ደቡብ_አፍሪካ የደቡብ አፍሪካው ፕሬዘዳንት ሲሪል ራማፎሣ ለጋዛ ፍልስጤማውያን ሰብአዊ እርዳታ ለማቅረብ በጀልባ ሲያመሩ በእስራኤል ጦር ተይዘው የታሰሩት በጎ ፈቃደኞች እንዲለቀቁ ጠየቁ፡፡ ከታሰሩት የብዙ አገሮች ዜጎች...
Oct 32 min read


መስከረም 23 2018 - ወጋገን ባንክ በስዊፍት የሚላክን ዓለም አቀፍ ክፍያ ወጋገን ሞባይል መተግበሪያን በመጠቀም በኦንላይን መከታተል የሚያስችላቸውን አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ተናገረ
ወጋገን ባንክ በስዊፍት የሚላክን ዓለም አቀፍ ክፍያ ወጋገን ሞባይል መተግበሪያን በመጠቀም በኦንላይን መከታተል የሚያስችላቸውን አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ተናገረ፡፡ አገልግሎቱ በተለይም በገቢ እና ወጪ ንግድ ዘርፍ...
Oct 31 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page








