top of page


ወደ አውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት የሚላክ ቡና ደን ሳይመነጠር የተመረተ እንደሆነ አረጋግጦ የመላክ ስራ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ይጀመራል ተባለ።
ጥር 22/2018 ወደ አውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት የሚላክ ቡና ደን ሳይመነጠር የተመረተ እንደሆነ አረጋግጦ የመላክ ስራ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ይጀመራል ተባለ። ህብረቱ ወደ አባል ሀገራቱ የሚላክ የግብርና ምርት ከደን ምንጣሮ ነፃ መሆን እንዳለበት የሚያስገድደውን ህግ ከአንድ ዓመት በኋላ ስራ ላይ ማዋል እንደሚጀምር ማሳወቁ ይታወሳል። የአውሮፓ ህብረት በተለይ በታዳጊ ሀገራት የተመረቱ ዘጠኝ የግብርና ምርቶች ወደ አባል ሀገራቱ መግባት የሚችሉት፤ ከደን ምንጣሮ ነፃ በሆነ መሬት ላይ ተዘርተው የበቀሉ ከሆነ እና ለዚህም ማረጋገጫ ሲያቀርቡ ብቻ እንደሚሆን በመጥቀስ ይህንኑ የተመለከተ የሚል ህግ አውጥቷል። በዚህ ክልከላ ውስጥ ከተካተቱ የግብርና ምርቶች ኢትዮጵያን የሚመለከተቱት ቡና እና አኩሪ አተር መሆናቸውን ሠምተናል። ህጉ ከባለፈው ወ
Jan 301 min read


የህብረት ስራ ማህበራት ተጠያቂነት ያለበት አሰራር እንዲከተሉ ለማድረግ በተጀመረው የሪፎርም ስራ ባክኖ የነበረ 1.6 ቢሊየን ብር ማስመለስ ተችሏል ተባለ።
ጥር 22/2018 የህብረት ስራ ማህበራት ተጠያቂነት ያለበት አሰራር እንዲከተሉ ለማድረግ በተጀመረው የሪፎርም ስራ ባክኖ የነበረ 1.6 ቢሊየን ብር ማስመለስ ተችሏል ተባለ። ሌሎችም በርካታ ውጤቶች በኀብረት ሥራ ማህበራት የሪፎርም ስራ መመዝገባቸውን የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ሺሰማ ገብረሥላሴ ተናግረዋል። ለአብነትም ማህበቱን በማዋሀድ፣ በማፍረስና ማጠናከር በተሰራው ስራ ከ120 ሺህ በላይ የነበረው የኀብረት ሥራ ማህበራት ቁጥር አሁን ላይ ወደ 89 ሺህ ዝቅ ማለቱን ጠቅሰዋል። የአመራር ስርአታቸውን ለማሻሻል በተሰራው ስራም ከ6900 መሰረታዊ ማህበራትና 57 ዩኒየኖች የአመራር ለውጥ አድርገዋል ያሉት አቶ ሺሰማ ወደ 4300 የሚሆኑ ሴቶችና ወጣቶች በአመራርነት እንዲካተቱ መደረጉንም ተናግረዋል። አዳዲስ አባላትን በ
Jan 301 min read


በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ትልልቅ ድርጅቶች ሰራተኖቻችሁን አደራጁ ተብለው ሲጠየቁ "አናደራጅም" የሚል ምላሽ እንደሚሰጡ ተነገረ።
ጥር 22 2018 ባለ ኮኮብ ሆቴሎችን ጨምሮ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ትልልቅ ድርጅቶች ሰራተኖቻችሁን አደራጁ ተብለው ሲጠየቁ "አናደራጅም" የሚል ምላሽ እንደሚሰጡ ተነገረ። የኢትዮጵያ አሰሪዎች ፌደሬሽን በበኩሉ አንዳንዶቹ ልክ እንደ ቀድሞው ዘመን ሰራተኛው ከተደራጀ ይደበድበኛል ፣ ንብረቴንም ይወርሰኛል የሚል ስጋት በአሰሪው በኩል መኖሩን አስረድቷል። ሰራተኞቹ እንዲደራጁ የሰራተኛ ማህበራት ደብዳቤ ሲልኩ የተቋማቱ ሀላፊዎች አይደራጁም የሚል ምላሽ እንደሚልኩ ተነግሯል። ይህ የተነገረው የከተማዋ ስራ እና ክህሎት ቢሮ በአሰሪው እና ሰራተኛ መካከል ጤነኛ የሆነ ግንኙት እንዲኖር ምክክር እንዲጀመር ሰራተኛው እንዲደራጅ ለማድረግ ይረዳል በሚል ባሰናደው የውይይት መድረክ ላይ ነው፡፡ የኢትዮጵያ አሰሪዎች ፌደሬሽን በበኩሉ አሰሪዎች ፤ሰራተኞች
Jan 301 min read


አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አዲስ አርማ ወይም ሎጎ ይፋ አደረገ።
ጥር 22/2018 አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አዲስ አርማ ወይም ሎጎ ይፋ አደረገ። ባንኩ ለ18 ዓመታት ሲጠቀምበት የነበረውን መለያውን ቀይሯል። የጭረት ምልክትን ይዞ የመጣው አዲሱ የባንኩ ሎጎ የሁሉም ነገር ጅማሬን የሚያመለክት እንደሆነ ተነግሮለታል። በቤሪ አድቨርታይዚንግ አማካኝነት የተሰራው የባንኩ አዲሱ መለያ ሎጎ በክብ ቢጫ ቀለም ውስጥ ጥቁር ጭረት ያሰፈረ እንደሆነ ተመልከተናል። የጭረት ምልክትን ይዞ የመጣው አዲሱ የባንኩ ሎጎ የሁሉንም ሀሳብ ጅማሬ ወይም መጀመሪያን የሚያመለክት እንደሆነ ተነግሯል። ላለፉት አመታት ሲሰራ የቆዬው አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አዲስ የብራንድ ማንነት ባንኩ ሙሉ ለሙሉ ወደ ለውጥ እየተሸጋገረ መሆኑን የሚያበስር ነው ተብሏል። እንደማሳያም ለቀጣዮቹ 3 አመታት በኢንደስትሪው ተወዳዳሪ እና ተመራጭ ትርጉም ያለው የፋይ
Jan 301 min read


ኢቲኬር የስፓይሩሊና ምግብ አጋዥ እና የውበት መጠበቂያ ምርቶችን እንዲያመርት ፍቃድ ተሰጠው።
ጥር 22/2018 ኢቲኬር የስፓይሩሊና ምግብ አጋዥ እና የውበት መጠበቂያ ምርቶችን እንዲያመርት ፍቃድ ተሰጠው። ስፓይሩሊና በያዘው ከፍተኛ ፕሮቲን እንደ አጋዥ ምግብ ወይንም ሰፕልመንት የሚመርጥ እንዲሁም ለውበት መጠበቂያነት የሚያገለግለውና በውሃ አካላት ላይ የሚገኘውን አልጌ ነው። ኢቲ ኬራ ስፓይሩሊና አልጌን ለአጋዥ ምግብነትም ፣ ለውበት መጠበቂያም አድርጎ እንዲያመርት የመጠቀሚያ ፈቃድ የሰጠው የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ነው፡፡ ይህን ስምምነትም በዛሬው እለት በኢቲኬር ፕሮዳክት መስራችና ባለቤት አቶ ማቲዮስ መባ እና የብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዮት ብርሃኑ (ዶ/ር) መካከል ተፈርሟል። ስፓይሮሊና አልጌን የመሳሰሉ የብዝሃ ሕይወቶችን ለመጠቀም ፣ ለማምረት ፍቃድ ያስፈልጋል፡፡ የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲት
Jan 301 min read


ኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነ የነዳጅ ምርት መፈተሻ ላብራቶሪ ለመክፈት መሰናዳቱን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ተናገረ፡፡
ጥር 21/2018 ኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነ የነዳጅ ምርት መፈተሻ ላብራቶሪ ለመክፈት መሰናዳቱን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ተናገረ፡፡ ከቀናት በኋላ ተመርቆ ወደ አገልግሎት ይገባል የተባለው የድርጅቱ የድሬደዋ ቅርንጫፍ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የነዳጅ ምርት መፈተሻ ላብራቶሪ የያዘ መሆኑ ተነግሮለታል፡፡ በተጨማሪም የባዮ ኬሚካል እና የኤሌክትሮ መካኒካል ፍተሻ ላብራቶሪዎችን የያዘ መሆኑ ሲነገር ሰምተናል፡፡ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የብሔራዊ የጥራት መሰረተ ልማት ከሆኑት አራት ተቋማት ውስጥ አንዱ ሲሆን የፍተሻ ስራ፣ የኢንስፔክሽን አገልግሎት እና የሰርተፍኬሽን ስራን ይከውናል፡፡ ከዚህ ቀደም ምርቶች ፍተሻ የሚደረግላቸው አዲስ አበባ ወደሚገኘው ዋናው መስሪያ ቤት በመላክ መሆኑን ያስታወሱት የድርጅቱ ዋና ዳይ
Jan 291 min read


ተማሪዎች በወርቅ ማዕድን ስራ ላይ መሰማራት ለትምህርት ማቋረጥ አንዱ ምክንያት መሆኑን የቤንሻንጉሉ ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ ተናገረ፡፡
ጥር 21/2018 ተማሪዎች በወርቅ ማዕድን ስራ ላይ መሰማራት ለትምህርት ማቋረጥ አንዱ ምክንያት መሆኑን የቤንሻንጉሉ ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ ተናገረ፡፡ ችግሩን ለመቅረፍ ከፀጥታ አካላትና ከወረዳዎች ጋር በመነጋገር እየሰራ መሆኑን አስረድቷል፡፡ የቤንሻንጉሉ ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ዘነበ በዚህ አመት 315 ሺህ ተማሪዎች ለመመዝገብ ታቅዶ 305 ሺህ የሚሆኑ ተማሪዎችን መዝግበናል ብለዋል፡፡ በክልሉ በየዓመቱ ለተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት አለመምጣትና ከትምህርት ገበታ መቅረት ዋንኛ ምክንያት የማእድን ስራ ተጠቃሽ ነው ብለዋል፡፡ አሁን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ከወረዳዎች ጋር በመነጋገር የወርቅን ቁፋሮ ስራ በሚሰራባቸው አካባቢዎች ለትምህርት የደረሰ ልጅ በትምህርት ቀን ስራ እንዳይሰራ ከፀጥታ አካላት ጋር
Jan 292 min read


በጋምቤላ ክልል ከቀናት በፊት ተከስቶ በነበረው የፀጥታ ችግር እጃቸው አለበት የተባሉ የመንግስት አመራሮች በቁጥጥር እየዋሉ ነው ተባለ፡፡
ጥር 21/2018 በጋምቤላ ክልል ከቀናት በፊት ተከስቶ በነበረው የፀጥታ ችግር እጃቸው አለበት የተባሉ የመንግስት አመራሮች በቁጥጥር እየዋሉ ነው ተባለ፡፡ የክልሉ ሠላም አሁን ላይ በአንጻራዊነት መሻሻል ማሳየቱንም የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ነግሮናል፡፡ በጋምቤላ ክልል ከተወሰኑ ሣምንታት በፊት ተከስቶ የነበረው የፀጥታ ችግር አሁን እየተፈታ ነው ተብሏል፡፡ የክልሉ መንግስት በጊዜው ባወጣው መግለጫ የመጣውን ሰላም እና ልማት ወደ ኋላ ለመመለስ እየሰሩ ያሉ እኩይ ሀይሎች ያላቸው ወገኖች ፤ በየቦታው ሰዎች በመግደል ፤ ተሽከርካሪዎች ላይ ጥቃት በማድረስ እና ህይወት እንዲጠፋ በማድረግ ጉዳት አድርሰዋል ማለቱ ይታወሳል። የፀጥታ አካላትን እና አመራርን ዒላማ በማድረግ ክልሉን ወደ ለየለት የህዝቦች እልቂት ለማስገባት የተለያዩ ሙከራዎች ሲደረጉ ተስተውለዋል
Jan 291 min read


የህፃናት ካንሰር ህክምና ለማግኘት በአማካይ እስከ 6 ሰዓት መጓዝን እንደሚጠይቅ ተነገረ።
ጥር 21/2018 የህፃናት ካንሰር አሳሳቢነት በየጊዜው እየጨመረ ቢመጣም፣ በአግልግሎት አለመስፋፋት ምክንያት ህክምናውን ለማግኘት በአማካይ እስከ 6 ሰዓት መጓዝን እንደሚጠይቅ ተነገረ። በኢትዮጵያ የህፃናት ደምና ካንሰር ህክምና ማህበር በዓመት በካንሰር ከሚጠቁ አጠቃላይ ሰዎች 10 በመቶዎቹ ህፃናት ቢሆንም ህክምና የሚያገኙት ግን 25 በመቶዎቹ ብቻ ናቸው ብሏል። ከህክምናው አለመስፋፋት በተጨማሪ፣ ህክምናው የሚጠይቀው የገንዘብ አቅምና የህብረተሰብ የጤና መድህን አለመስፋፋት ፈተና እንደሆነ መቀጠሉን የማህበሩ ዋና ፕሬዝዳንት ዶ/ር አቤል ኃይሉ ነግረውናል። በህክምና ወቅት ህፃናት ደም በማጣት ይሞታሉ ያሉት ዶ/ር አቤል፣ አሁን ያለውን የደም ዕጥረት ለማስቀረት ከአጠቃላዩ የህዝብ ቁጥር 61 በመቶው ደም መለገስ ይኖርበታል ብለውናል። ያ
Jan 291 min read


ኢትዮ ቴሌኮም በዘንድሮ በጀት ዓመት ብቻ ለምገነባቸው ግዙፍ መሰረተ ልማቶች ከአንድ ቢሊየን ዶላር በላይ እፈልጋለሁ አለ።
ጥር 21/2018 ኢትዮ ቴሌኮም በዘንድሮ በጀት ዓመት ብቻ ለምገነባቸው ግዙፍ መሰረተ ልማቶች ከአንድ ቢሊየን ዶላር በላይ እፈልጋለሁ አለ። ኩባንያው ለምገነባቸው መሰረተ ልማቶች ባንኮች የሚያቀርቡት የውጭ ምንዛሪ የ ኢትዮ ቴሌኮምን ፍላጎት የሚያሟላ ሆኖ አላገኘሁትም ብሏል። ኢትዮ ቴሌኮም ከውጭ ምንዛሪ ከፍተኛ ፍላጎት ጋር በተገናኘ ከአለም አቀፍ የፋይናንስ አቅራቢዎች ጋር እየተነጋገርኩ ነው ብሏል። ከውጭ ምንዛሪ ገበያ መለዋወጥ ጋር በተገናኘ ኩባንያው የውጭ ምንዛሪ ሎስ ወይም መዛባት ከሚያጋጥማቸው መካከል አንድ መሆኑ ተሰምቷል። ኩባንያው የውጭ ምንዛሪ ሎስ ወይም መዛባት የ ኦፕሬሽኑ ወይም የአገልግሎት አቅራቢው ችግር ሳይሆን ከ ፖሊሲ ለውጥ ጋር የመጣ ነው ብሏል። ኩባንያው ለዚህ ተጋላጭ ነው ፤ ይህም በፖሊሲ አውጭዎች የሚፈታ ነው መሆኑን ሰምተናል።
Jan 291 min read


በአሰሪ እና ሰራተኛ መካካል ያለውን “የጎሪጥ መተያያት” ማስቆም ካልተቻለ ሀገርን ወደፊት ማራመድ ይቸግራል ተባለ።
ጥር 21/2018 በአሰሪ እና ሰራተኛ መካካል ያለውን “የጎሪጥ መተያያት” ማስቆም ካልተቻለ ሀገርን ወደፊት ማራመድ ይቸግራል ተባለ። እስካሁን የቀጠለው “የጎሪጥ መተያያት” ሀገሪቱን ወደኋላ አስቀርቷል ተብሏል። ይህ የተባለው ዛሬ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ አካባቢው ሰላማዊና ምርታማ እንዲሆን ይረዳል በሚል የአሰሪና ሰራተኛ ምክክር የመደራጀት ምጣኔ ተግባር ላይ በአድዋ ሙዚየም ከባለድርሻ አካላት ጋር ወይይት ባካሄደበት ወቅት ነው። የሰራተኛን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ጥራት ያለው ምርት ለማምረት እና የተሻለ አገልገሎት ለማቅረብ ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን የውይይት የመነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት በቢሮው የአሰሪ እና ሰራተኛ ጉዳይ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አበበ ተቀባ አስረድተዋል። አሰሪዎች ከሰራተኞቻቸው ጋር ቁጭ ብለው መመካከር አለባቸው የተባለ ሲሆን ይህን
Jan 291 min read


ኢትዮጵያ በውሃ ዋና ስፖርት ከሀገር ውስጥ አልፎ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንድትሆን በቂ የውሃ ገንዳ ማዘውተሪያዎች ያስፈልጋታል ተባለ::
ጥር 20/2018 ኢትዮጵያ በውሃ ዋና ስፖርት ከሀገር ውስጥ አልፎ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንድትሆን በቂ የውሃ ገንዳ ማዘውተሪያዎች ያስፈልጋታል ተባለ:: ይህ የተባለዉ በጅማ ዩንቨርስቲ እየተካሄደ ባለው 10ኛው የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል ላይ ነው:: በውድድሩ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተወክለው የመጡ የውሃ ዋና ተወዳዳሪዎች እየተሳተፉ ነው:: ኢትዮጵያ በቂ የሆነ የውሃ ገንዳ ወይንም ማዘውተሪያዎች ቢኖራት በዘርፉ አሁን ካሉት ስፖርተኞችን የበለጠ ማፍራት ትችላለችም ተብሏል:: ይሁንና በቂ ማዘውተሪያዎች ባለመኖራቸው ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገብ እየተቻለ እንዳልሆነ የኢትዮጵያ ውሃ ስፖርቶች ፌደሬሽን ፅ/ት ኃላፊ አቶ ሽመልስ ተፈሪ ነግረዉናል:: የውሃ ዋና ስፖርተኞች በግላቸው የውሃ ገንዳ ወይም ማዘተሪያዎች ሄደው ልምምድ ለማ
Jan 281 min read


የማርበርግ ቫይረስ መከሰት ኢትዮጵያን ምን አስተማራት?
ጥር 20/2018 የማርበርግ ቨይረስ መከሰት ኢትዮጵያን ምን አስተማራት? ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ምንታምር ፀጋው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx X :- https://x.com/shegerfm?s=2 LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv Instagram: https://shorturl.at/9X4S7
Jan 281 min read


ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባወጣው የ500 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ ላይ የ92 ሚሊዮን ዶላር ክፍተት(ተጨማሪ ፍላጎት) ተፈጠረ፡፡
ጥር 19/2018 ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባወጣው የ500 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ ላይ የ92 ሚሊዮን ዶላር ክፍተት(ተጨማሪ ፍላጎት) ተፈጠረ፡፡ ይህም ባንኩ ባቀረበው የውጪ ምንዛሬ መጠንና በተፈለገው መጠን መካከል ያለውን ክፍተት ይፋ ማድረግ ከጀመረበት ጊዜ ወዲህ ከፍተኛው ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ ማዕከላዊ ባንኩ ዛሬ 500 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ ያቀረበ ሲሆን የተጫራች ባንኮች ፍላጎት ግን 592.3 ሚሊዮን ዶላር አንደሆነ የባንኩ መረጃ ያሳያል፡፡ የባንኩ ጨረታ ከባለፈው ጋር ሲነጻጸር የኢትዮጵያ ብር የመግዛት አቅም በ11 ሳንቲም ያጠናከረ ሆኗል፡፡ ጥር 12 ቀን 15 ዙር ጨረታውን አድርጎ የነበረው ብሔራዊ ባንክ 16 ዙር የውጭ ምንዛሬ ጨረታውን ዛሬ አካሂዷል፡፡ በዚህም መሰረት የቀረበው የ500 ሚሊዮን ዶላር ምንዛሬ በአማካኝ አንድ የአሜሪካን ዶላራ በአማካኝ 154.8
Jan 281 min read


በተመድ በአለም አቀፍ ደረጃ 2026 የአርብቶ አደር እና የግጦሽ መሬት ዓመት እንዲሆን በተወሰነው መሰረት አዲስ አበባ ላይ ጉባኤ መደረጉ ተሰማ
ጥር 19/2018 የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እና የአየር ጠባይ ለውጥንም ለመቋቋም ይረዳል ተብሎ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአለም አቀፍ ደረጃ 2026 የአርብቶ አደር እና የግጦሽ መሬት ዓመት እንዲሆን በተወሰነው መሰረት አዲስ አበባ ላይ ጉባኤ መደረጉ ተሰማ፡፡ ከግብርና ሚኒስቴር ፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሰላም እና ፀጥታ ኢንስቲትዩ ጋር በመተባበር የመንግስታቱ ድርጅት በወሰነው መሰረት በርዕሰ ጉዳዩ ዙሪያ ምሁራንና የአርብቶ አደሮች መወያየታቸው ተሰምቷል፡፡ በኢትዮጵያ ከ12 እስከ 15 በመቶ የሚደርሱ የማህበረሰብ አባላት አርብቶ አደር መሆናቸው የሚነገር ሲሆን ኢኮኖሚው ላይ ከፍተኛ ድርሻ አላቸውም ተብሏል፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ ከ300 ሚሊዮን በላይ አርብቶ አደሮች መኖራቸው የሚናገሩት የፓስቶራሊስት ፎረም ኢትዮጵያ ዳይሬክተር
Jan 271 min read


ጥር 19/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ፈረንሳይ ፈረንሳይ እድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ አዳጊዎችን የኢንተርኔት ማህበራዊ ትስስር ገጾች ተጠቃሚነትን ልታስቀር ነው፡፡ አዳጊዎችን እንደ ፌስ ቡክ እና ቲክ ቶክ ካሉ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ተጠቃሚነት የሚከለክል ረቂቅ ተሰናድቶ ለአገሩቱ ፓርላማ መቅረቡን ቢቢሲ ፅፏል፡፡ ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ሕጉ ከመጪው አዲስ የትምህርት ዘመን በፊት ስራ ላይ እንዲውል ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ ሕጉ አዳጊ ወጣቶችን ከተለያዩ ማህበራዊ ጠንቆች ለመጠበቅ ሁነኛ መፍትሄ እንደሚሆን ታምኖበታል ተብሏል፡፡ በብዙ አገሮችም አዳጊዎችን ከተለያዩ ማህበራዊ ትስስር ድረ ገጾች የማቅረቡ እርምጃ እያነጋገረ ነው ተብሏል፡፡ አውስትራሊያ እድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ አዳጊዎችን የማህበራዊ ትስስር ገፆች ተጠቃሚነት በመከልከል ቀዳሚዋ አገር እንደሆነች መረ
Jan 272 min read


ዘመን ባንክ አጠቃላይ ሀብቴ ከ100 ቢሊዮን ብር አለፈ አለ፡፡
ጥር 19/2018 ዘመን ባንክ አጠቃላይ ሀብቴ ከ100 ቢሊዮን ብር አለፈ አለ፡፡ የተከፈለ ካፒታሉም14 ቢሊዮን ብር መድረሱን በላከልን መግለጫ ላይ ጠቅሷል፡፡ ባንኩ በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የመጀመሪያ መንፈቅ አጠቃላይ ሀብት 106 ቢሊዮን ብር፣ ተቀማጭ ገንዘብ ደግሞ 80 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተናግሯል፡፡ ይህም ባንኩ የተረጋጋ ዕድገትና ጠንካራ የደንበኞች አመኔታ እንዳለው የሚያሳይ ነው ሲሉ የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደረጀ ዘበነ አስረድተዋል፡፡ ዘመን ባንክ በዚህ ጊዜ ውስጥ ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ ማስመዝገቡም ተጠቅሷል፡፡ ዋና ስራ አስፈጻሚው የባንኩ የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የመጀመሪያ መንፈቅ ስኬት ካለፈው ዓመት ከነበረው የሥራ አፈፃፀም ጋር ሲወዳደር የዘንድሮው የላቀና ስኬታማ የሥራ ጊዜ ያሳለፍንበት ነበር ሲሉ አስረድተዋል
Jan 271 min read


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሚሰጠው አገልግሎት ደንበኞቹ የእርካታ ደረጃ ከ80 ከመቶ መድረሱን ባካሄድኩት ጥናት አረጋግጫለሁ አለ፡፡
ጥር 19/2018 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሚሰጠው አገልግሎት ደንበኞቹ የእርካታ ደረጃ ከ80 ከመቶ መድረሱን ባካሄድኩት ጥናት አረጋግጫለሁ አለ፡፡ ባንኩ ይህን ያለው ዘሬ ማካሄድ በጀመረው የደንበኞች አገልግሎት ሳምንት የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንከ ከዚህ ቀደም በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ በጥቂቱም ቢሆን የታዩ ነበሩ ያላቸውን ከአሠራር ግልጽነት፣ ከአገልግሎት ጥራት መዋዠቅ፣ ከአገልግሎት መዘግየት፣ ከኔትወርክ መቆራረጥ፣ ከሲስተም ብልሽት፣ ከሥራ ክፍሎች ቅንጅት፡ ከሠራተኞች አመለካከት እና ከሥራ ባህል ጋር የተያያዙ ችግሮችን ለመፍታት ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረኩ ነው ብሏል፡፡ የደንበኞች አገልግሎት ሳምንት የሚከበረው በዋናነት ከደንበኞች ጋር በሚካሄዱ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና ግብረ መልስ መሰብሰቢያ ውይይቶች ሲሆን፣ እንደ
Jan 271 min read


በመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ በሰሜኑ ጦርነት ስጋት አድሮባቸው ስራ አቁመው የቆዩ ባለሃብቶች ዳግም ወደ ማምረት ለመመለስ ፍቃደኝነታቸውን እያሳዩ ነው ተባለ
ጥር 19/2018 በመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ የነበሩ እና በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ስጋት አድሮባቸው ስራ አቁመው የቆዩ ባለሃብቶች ዳግም ወደ ማምረት ለመመለስ ፍቃደኝነታቸውን እያሳዩ ነው ተባለ። መንግስትም መሰረተ ልማቶችን መልሶ ሊያሟላላቸው እና የተለያዩ ማበረታቻዎችን ሊሰጣቸው እንደተስማማ ሠምተናል። በአሁኑ ወቅት በኢነዱስሪ ፓርኩ እየሰራ ያለው አንድ ባለሃብት ብቻ ነው ተብሏል፡፡ ለሁለት ዓመት ያህል በቆየው የሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ስራ አቁሞ የቆየው የመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዳግም ወደ ማምረት እንዲመለስ ከአራት ወር በፊት ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እየሰራ እንደሚገኝ ተጠቅሷል። ግብረ ሃይሉ በፓርኩ ውስጥ ሲሰሩ የነበሩ እና በጦርነቱ ምክንያት ለቀው የሄዱ ባለሃብቶችን በኢንተርኔትና ሌሎች አማራጮች አግኝቶ ማነጋገሩን፤ የኢንዱስትሪ ፓርኮች
Jan 272 min read
ከኢትዮ ቴሌኮም እና መሰል አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ለአገልግሎት ከሚያስከትሉት እስከ 5 መቶ እንዲቆረጥ የሚያስገድድ ደንብ ወጥቷል
ጥር 19/2018 በተለያየ ምክንያት ለችግር የተጋለጡ ሰዎችን እርዳታ ከመጠበቅ ይልቅ ኢትዮጵያ በራሷ አቅም ምላሽ ለመስጠት ከኢትዮ ቴሌኮም እና መሰል አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ለአገልግሎት ከሚያስከትሉት እስከ 5 መቶ እንዲቆረጥ የሚያስገድድ ደንብ ወጥቷል፡፡ ደንቡ የቢዝነስ ሰዎች ንግድ ፈቃድ ሲያስወጡ እና ሲያድሱ ፓስፖርት ለማውጣትም አገልግሎት ሲጠይቁ በቁርጥ እስከ 200 ብር እንዲከፍሉ ያስገድዳል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ያሬድ እንዳሻው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://sh
Jan 271 min read


በፍትህ ሚኒስቴር የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ 1800 የሚሆኑ ሰዎችን በሕገ-ወጥ መንገድ አዘዋውሯል ባላቸው 28 ተከሳሾች ላይ ክስ መመስረቱን ተናገረ፡፡
ጥር 19/2018 በፍትህ ሚኒስቴር የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ 1800 የሚሆኑ ሰዎችን በሕገ-ወጥ መንገድ አዘዋውሯል ባላቸው 28 ተከሳሾች ላይ ክስ መመስረቱን ተናገረ፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በህገ ወጥ መንገድ ሲያዘዋውሯቸው ከነበሩት ሰዎች ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰባቸውን ዐቃቤ ህግ በክሱ ጠቅሷል፡፡ የዐቃቤ ሕግ ክስ እንደሚያስረዳው ክስ የመሰረተባቸው 28ቱ ግለሰቦች በሰው ልጅ ለመነገድ በማሰብ #የወንጀል_ቡድን በማደራጀት እንዲሁም የቡድኑ አመራር እና አባላት በመሆን በወንጀል ድርጊቱ ላይ ተሳተፈዋል በሚል የተጠረጠሩ ናቸው፡፡ በስራቸው ሌሎች አነስተኛ ስራ የሚሰሩ ደላሎችን በመመልመል ሰዎች በሊቢያ በኩል አድርገው ወደ አውሮፓ ከገቡ የተሻለ ኑሮ እንደሚኖሩ በማሳመን ወደ ባህርዳር እና ጎንደር ሲልኩ ቆይተዋል ብሏል፡፡ ተከሳሾቹ በባህር ዳር እና ጎንደር አካባ
Jan 272 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

