top of page
በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች በ500,000 እና 400,000 ብር ዋስ እንዲፈቱ ተወሰነ።
ግንቦት 3/2018 በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች በ500,000 እና 400,000 ብር ዋስ እንዲፈቱ ተወሰነ። መንሱር ጀማል የተባለው ተከሳሽ ግን አቃቢ ህግ መቃወሚያ ስላቀረበበት ዛሬ ከሰዓት ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ከድርጅቱ ጋር በተያያዘ በ1.9 ቢሊዮን ብር የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ ታዋቂ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች፣ የዋስትና መብታቸው ተከብሮ በውጭ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት ፈቅዷል። ባለፈው ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ከ5 ተከሳሽ መንሱር ጀማል ውጭ ባሉ ተጠርጣሪዎች ከሀገር እንዳይወጡ እና ከፍ ያለ ዋስትና አስይዘው የዋስትና መብታቸው ተከብሮ ከውጭ ሆነው ጉዳያቸውን ቢከታተሉ እንደማይቃ
May 111 min read


በአዲስ አበባ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ጉቦ እና የእጅ መንሻ፤ አካውንት ቁጥር እስከ መስጠት መድረሱ ተነገረ፡፡
ሚያዝያ 30/2018 በአዲስ አበባ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ጉቦ እና የእጅ መንሻ፤ አካውንት ቁጥር እስከ መስጠት መድረሱ ተነገረ፡፡ በአዲስ አበባ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ለአገልግሎት የሚመጡ ሰዎችን ጉቦ የሚጠይቁ እንዳሉ የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል ነው የተናገሩት፡፡ ጉቦ እና እጅ መንሻ መጠየቅ፤ አገልግሎት መስጠት ላይ እንቅፋት ሆኖ መቀጠሉም ከምክር ቤት አባል ተነስቷል፡፡ #ጉቦ ጠይቀው የተገኙት ላይም የሚወሰድባቸው እርምጃ እና የሚወሰኑ ውሳኔዎች ቀለል ያሉ ናቸው ተብሏል፡፡ ይህ መሆኑ ጉቦ ጠያቂዎቹ የበለጠ እየተደፋፈሩ እንደሆነና ቅጣቱ ሌሎችን ሊያስተምር እንዳልቻለ ተጠቅሷል፡፡ ይህ የተነገረው ዛሬ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ ነው፡፡ ይህንን ተግባር ለማስቆም ምን እየተሰራ እንደሆነም ጥያቄ ቀ
May 81 min read


የሚያዝያ ወር የዋጋ ግሽበት ምጣኔ ከ11 በመቶ መሻገሩን መንግስት ተናገረ።
ሚያዝያ 30/2018 የሚያዝያ ወር የዋጋ ግሽበት ምጣኔ ከ11 በመቶ መሻገሩን መንግስት ተናገረ። አምና በዚህ ወቅት የዋጋ ግሽበቱ 14.4 በመቶ እንደነበር ያስታወሰው የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት ሲሆን ዘንድሮ በመጠኑ ቅናሽ አሳይቷል ብሏል። የዘንድሮ የሚያዝያ ወር የግሽበት ምጣኔ 11.7 በመቶ ነው። ከባለፈው ወር ደግሞ 2.2 በመቶ ያህል ጨምሯል። በተለይ ምግብ ነክ የሆኑና አልኮል የሌላቸው መጠጦች ደግሞ ከፍተኛ ሆኖ የዋጋ ግሽበት ምጣኔአቸው 13.5 በመቶ ደርሷል። ለአብነትም አትክልት፣ ስጋ፣ የወተት ተዋፅዖዎች፣ እንቁላል፣ ፍራፍሬ፣ ዘይት እና ስኳር የመሳሰሉት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ጨምሯል ብሏል አገልግሎቱ ባወጣው መረጃ። ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት 9.1 በመቶ የደረሰ ሲሆን የትራንስፖርት ዋጋ በ13 በመቶ ከፍ ብሏል። በምግብ ቤቶች እና ሆ
May 81 min read


በአጭር ጊዜ ለግንባታ የሚጠይቀውን በጀት አግኝተው ግንባታን ይከውኑት ይሆን?
የሚያዝያ 29/2018 የትምህርት ሚኒስቴር በቀሪዎቹ 4 ወራት 1,452 የቅድመ መደበኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሁሉም ክልሎች ለመገንባት በቅብሩ ከክልሎች ጋር ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ እነዚህ ትምህርት ቤቶች የሚገነቡት ግማሹ በትምህርት ሚኒስቴር ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ በክልሎቹ በራሳቸው ወጪ ነው፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር ለሚያስገነባቸው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 40 ሚሊዮን ዶላር ፈንድ ከአጋር አካላት በእርዳታ ማግኘቱን ተነግሯል፡፡ ታዲያ ክልሎች በአጭር ጊዜ ለግንባታ የሚጠይቀውን በጀት አግኝተው ግንባታን ይከውኑት ይሆን? የተለያዩ ክልሎችን ጠይቀናል፡፡ የደቡብ ኢትዮጵ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዮት ደምሴ በክልሉ የሚገነባው 70 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ እነዚህ ትምህርት ቤቶች ሲገነቡ በክልሉ ውስጥ
May 82 min read


ትንባሆ በሚጨስባቸው የግል ትምህርት ቤቶች አካባቢ ብርቱ ቁጥጥር እያደረግሁ ነው ሲል የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ተናገረ፡፡
የሚያዝያ 29/2018 ትንባሆ በሚጨስባቸው የግል ትምህርት ቤቶች አካባቢ ብርቱ ቁጥጥር እያደረግሁ ነው ሲል የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ተናገረ፡፡ በትምህርት ቤቶቹ አካባቢ ትንባሆ ሲያጨሱ ተገኝተው እርምጃ የተወሰደባቸውም እንዳሉ ተጠቁሟል፡፡ ይህንን ያደረግሁትም ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር ነው ብሏል ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ፡፡ ትንባሆን በማንኛውም አይነት ሁኔታ መጠቀም የበዙ የጤና ችግሮች እንዳሉት ወጣቶች እንዲያወቁት የግንዛቤ ስራ እየሰራ መሆኑንም ተናግሯል፡፡ በተጨማሪም በህጉ መሰረት ሲጋራን በነጠላ መሸጥ በህግ ቢከለከልም አሁንም በነጠላ የሚሸጡ እና የሚገዙ በየቦታው እንደሚታዩም ተነስቷል፡፡ እንዲህ በሚያደርጉት ላይ የማስተማርና እርምጃ የመውሰድ ስራ እየተሰራ መሆኑን እና መልካም የሚባል መሻሻል መገኘቱን የተናገሩት ደግሞ በኢትዮ
May 71 min read


‘’በአዲስ አበባ በ9 ወራት ከ37,000 በላይ እግረኞች ተቀጥተዋል’’
የሚያዝያ 29/2018 ማዳመጫ ጆሯቸው ላይ አድርገው የአስፋልት መንገድ የተሸገሩ እና ሌሎች የመንገድ አጠቃቀም የደንብ መተላለፍ የፈፀሙ ከ37,000 በላይ እግረኞች ተቀጥዋል ተባለ፡፡ ባለፉት 9 ወራት ቅጣቱ ከተላለፉባቸው ከነዚህ እግረኞች መካከል የገንዘብ ቅጣቱን መክፈል ያልቻሉት 16,000 ያህሉ ማህበራዊ አገልግሎት ሰጥተዋል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ፋሲካ ሙሉወርቅ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx X :-..
May 71 min read


የመክፈል አቅም ለሌላቸው፤ ጠበቆች የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን እንዲሰጡ ተጠይቀዋል፡፡
የሚያዝያ 29/2018 ፍትህ ለሁሉም ተደራሽ ይሆን ዘንድ የመክፈል አቅም ለሌላቸው ነፃ የህግ ድጋፍ እንዲያገኙ መንግስት ህግ ቢያወጣም አሁንም ግን ብዙ ሰዎች ተጠቃሚ እየሆኑ አይደለም፡፡ የፍትህ ሚኒስቴርም ይህንን ያምናል፡፡ ከህጉ ባሻገር ጠበቆችም በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱን እንዲሰጡ ተጠይቀዋል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ምንታምር ፀጋው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx X :- https://x.com/shegerfm?s
May 71 min read
የኢኮኖሚ እድገት ለማምጣት መንግስት ምርትን የሚያሳድጉ ለሰዎች የስራ እድልን የሚያበዙ ስራዎች ላይ እንዲያተኩር ተመክሯል፡፡
የሚያዝያ 29/2018 አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ትንበያ መሰረት በ2026 የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት ከአፍሪካ ከቀዳሚዎቹ መካከል ከምስራቅ አፍሪካ ደግሞ ግንባር ቀደም ያደርጋታል፡፡ 9.2 በመቶ እድገት ታስመዘግባለች ተብሏል፡፡ በሌላ በኩል ኢኮኖሚው አደገ ቢባልም የሰው የኑሮ ደረጃ ግን ለውጥ ያለው አይመስልም፡፡ በመሆኑም በዋጋ ውድነት የሚፈተነውን ነዋሪ ለማገዝ የሚያስችል የኢኮኖሚ እድገት ለማምጣት መንግስት ምርትን የሚያሳድጉ ለሰዎች የስራ እድልን የሚያበዙ ስራዎች ላይ እንዲያተኩር ተመክሯል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ትዕግስት ዘሪሁን ያሰናዳችውን በንጋት መኮንን የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/
May 71 min read


የኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ብድር ጭማሪ ማሳየቱን የገንዘብ ሚኒስቴር ተናገረ።
ሚያዝያ 29/2018 የኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ብድር ጭማሪ ማሳየቱን የገንዘብ ሚኒስቴር ተናገረ። የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል። ኢትዮጵያ በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ የ1 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ የምታገኝበትን ስምምነት ሁለቱ አገራት መፈራረማቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለፓርላማ ተናግሯል። የገንዘብ ሚኒስቴር ይህን የተናገረው ከሰሞኑ የዘጠኝ ወር የስራ ክንውን ሪፖርቱን በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ነው። የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን የስራ ክንውን ሪፖርት በንባብ ያቀረቡት ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል ብለዋል። ከዚህ ውስጥ 33.5 ቢሊዮን ዶላር የውጪ ብድር እዳ እን
May 72 min read


70 በመቶ የሚሆኑ የጤና ባለሞያዎች በአግባቡና በትክክል እጃቸውን እንደማይታጠቡ በጥናት ስለመረጋገጡ ተነግሯል።
ሚያዝያ 28/2018 70 በመቶ የሚሆኑ የጤና ባለሞያዎች በአግባቡና በትክክል እጃቸውን እንደማይታጠቡ በጥናት ስለመረጋገጡ ተነግሯል። ይህም የተላላፊ በሽታዎችን ተጋላጭነት በእጥፍ ይጨምረዋል ተብሏል። ይህ የተባለው ዓለም አቀፍ የእጅ መታጠብ ቀንን አስመልክቶ የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ባሰናዳው መድረክ ላይ ነው። በኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የበሽታ መከላከልና ጤና ማበልፀግ ባለሙያ የሆኑት ዶ/ር ሄርጎ አበራ እጅን በአግባቡ መታጠብ በተላላፊ በሽታ የመሞትን ምጣኔ ከ18 በመቶ ወደ 2 በመቶ ይቀንሰዋል ብለዋል። በኢትዮጵያ እጃቸውን በአግባቡ እና ሳይንሱን ተከትለው የሚታጠቡ የጤና ባለሙያዎች ቁጥር 30 በመቶ ብቻ መሆኑን ዶ/ር ሄርጎ አስረድተዋል። ከታማሚዎች ፈሳሽ እና መሰል ነገሮች ጋር ንክኪ ያላቸው የጤና ባለሙያዎች ለተላላፊ በሽታዎች የመጋለጥ ዕድላቸው 75 በመቶ
May 61 min read
በፊንቴክ የማጭበርበር ወንጀል ዛሬ በአቃቤ ሕግ ክስ የተመሰረተባቸው አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ተወነሰ፡፡
ሚያዝያ 28/2018 በፊንቴክ የማጭበርበር ወንጀል ዛሬ በአቃቤ ሕግ ክስ የተመሰረተባቸው አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ተወነሰ፡፡ በተጠርጣሪዎቹ ላይ በአቃቤ ህግ ዛሬ የመሰረተባቸውን የክስ ዝርዝሩን ያደመጠው የከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ከአምስተኛ ተከሳሽ መንሱር ጀማል በስተቀር ሌሎቹ በዋስ እንዲፈቱ ወስኗል፡፡ አቃቤ ህግ መንሱር ጀማልን በዋስትና እንዳይፈታ በመቃወሙ፣ መቃወሚያውን በፅሁፍ እንዲያስረዳ ችሎቱ ለመጪው ሰኞ ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ በዋስ እንዲለቀቁ ለተወሰነላቸው ተከሳሾችም በዋስትና የሚለቀቁበትን የገንዘብ መጠን ለመወሰን ፍርድ ቤቱ ለመጪው ሰኞ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ተከሳሾች የ 1.9 ቢሊን ብር የማጭበርበር ጉዳት አድርሰዋል ያለው አቃቤ ሕግ ከደረሰው ጉዳት አንፃር የዋስትና
May 61 min read


ኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የቀዳማይ ልጅነት ጉባኤ ልታሰናዳ ነው፡፡
ሚያዝያ 28/2018 ኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የቀዳማይ ልጅነት ጉባኤ ልታሰናዳ ነው፡፡ ጉባኤው ለተማሪዎች ምገባ እና የትምህርት ቁስ ድጋፍ ለሚከነው ስራ የሚታዩ የፋይናንስ ችግሮችን ለመፍታት ያግዛል ተብሏል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተቋቋመው የቀዳማይ ልጅነት ማዕከል የልጆችን የተሟላ የጤና እንክብካቤ፣ የተመጣጠነ ምግብ እና ጥራት ያለው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት መከታተል ዋና አላማው እንደሆነም ሰምተናል። በዚህም 241 የመንግስት ትምህርት ቤቶች እና በ935 የቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤቶች ላይ የምገባ ፕሮግራም፣ የትምህርት ቁሳቁስ በማቅረብ እና የተማሪዎች ዩኒፎርም በነፃ በማቅረብ አገልግሎት እየሰጠ እንደሆነም እና ከ330,000 በላይ ተማሪዎች የዚሁ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸው የቀዳማይ ልጅነት ልማት ማዕከል ዋና ስራ አስፈፃሚ ከበደ
May 61 min read


ኢዮብ ተስፋ ለሕጻናትና ለወጣቶች በጎ አድራጎት ድርጅት፤ ለ3 የህክምና ተቋሞች የህክምና ቁሳቁሶችን አስረከበ።
ሚያዝያ 28/2018 ኢዮብ ተስፋ ለሕጻናትና ለወጣቶች በጎ አድራጎት ድርጅት፤ ለ3 የህክምና ተቋሞች 180 ሺህ ዶላር ወይም ከ27 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የህክምና ቁሳቁሶችን አስረከበ። ድርጅቱ ለልብ ህክምና አገልግሎት የሚውሉትን የህክምና ቁሳቁሶቹ ያስረከበው ለጥቁር አንበሣ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፣ ለቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም የህክምና ኮሌጅ እና ለኢትዮጵያ ልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማዕከል ነው። ኢዮብ ተስፋ ለሕጻናትና ለወጣቶች በጎ አድራጎት ድርጅት ከደጋፊዎቹ ባገኘነው ደጋፍና ትብብር የገዛናቸውንና አብረውት ከሚሰሩ የልብ ሐኪሞች ትብብር ከሜድትሮኒክ ኩባንያ ያገኘናቸውን በጠቅላይ 180,000 ዶላር ወይም ከ27 ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ ብር በላይ የሚያወጡ የሕከምና ቁሳቁሶችና መሳሪያዎችን ለሶስቱ ተቋሞች አስረክቧል። ኢዮብ ተስፋ ለሕጻ
May 61 min read


የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የግብርና ምርቶች በእሴት ጭመራ እና የማምረቻ ዋጋ መቀነስ ካልተቻለ ተወዳዳሪ እንዳንሆን ሊያደርገን ይችላል ሲሉ አግሮ ኢኮኖሚስት አስጠነቀቁ፡፡
ሚያዝያ 28/2018 የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የግብርና ምርቶች በእሴት ጭመራ እና የማምረቻ ዋጋ መቀነስ ካልተቻለ ተወዳዳሪ እንዳንሆን ሊያደርገን ይችላል ሲሉ አግሮ ኢኮኖሚስት አስጠነቀቁ፡፡ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የገቢያ አቅሙ በባለሙያዎች ሲመዘን 1.4 ቢሊዮን ህዝብን ታሳቢ ያደረገ ሲሆን 3 ትሪሊዮን ዶላር በአህጉሪቱ ውስጥ እንዲዘዋወር ያደርጋል፡፡ አፍሪካዊያን በንግዱ ስርዓታቸው እሴት መጨመር ላይ ትኩረት አድርገው የማይሰሩ ከሆነ ዋንኛው የዚህ ነፃ ንግድ ቀጠናው ፈታኝ ችግር ይህ ሊሆን ይችላል ተብሏል፡፡ ታደለ ማሞ(ዶ/ር) አግሮ ኢኮኖሚስት ሲሆኑ በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የግብርና ኢኮኖሚ ምርምር ዳይሬክተር ናቸው፡፡ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ለኢትዮጵያ ግብርና እድልም ስጋትም ይዞ ይመጣል ይላሉ፡፡ ምርቶችን በትክክል ካመረት
May 62 min read


በአንደኛ ደረጃ እና በመካከለኛ ደረጃ ባሉ ትምህርት ቤቶች ላይ የመፅሐፍት እጥረት
ሚያዝያ 28/2018 ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመፅሐፍት እጥረቱ በአንደኛ ደረጃ እና በመካከለኛ ደረጃ ባሉ ትምህርት ቤቶች ላይ ከፍተኛ መሆኑን በተለያዩ ጊዜያት መነገሩ ይታወሳል፡፡ የትምህርት ሚኒስቴርም ይህንን ችግር ለመፍታት በዚህ ዓመት 23 ሚሊዮን የአንደኛ እና የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት መማሪያ መፅሐፍት ማሳተሙና ማከፋፈሉን ተነግሯል። በ2019 የትምህርት ዘመን ይደርሳል የተባለ ደግሞ 36 ሚሊዮን የአንደኛ እና የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት መማሪያ መፅሐፍትን ለማሳተም የመጨረሻ ደረጃ ላይ መድረሱን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ(ፕ/ር) አስረድተዋል። ታዲያ በዚህ ስራ ክልሎች ምን እየሰሩ ነው? የመፅሀፍት እጥረቱስ በምን ሁኔታ እየተወጡት ይሆን ስንል ጠይቀናል፡፡ የአፋር ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሳ አደም (ዶ/ር) በዚህ ዓመት ትምህር
May 62 min read


በ2018 በጀት ዓመት 9 ወራት 103 አዲስ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ፡፡
ሚያዝያ 26/2018 በ2018 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት 103 አዲስ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ፡፡ አገልግሎቱ ከዋናው ግሪድና ከግሪድ የራቁ በርካታ አዳዲስ አካባቢዎችን ተጠቃሚ ማድረጉን እና ከጤናና ማህበራዊ ተቋማት በተጨማሪ ከ31 ሺህ በላይ አባዎራዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግሯል፡፡ በዚህም 82ቱ ከዋናው የኤሌክትሪክ መረብ (ግሪድ) እንዲሁም 21 የገጠር ከተሞችና መንደሮችን ደግሞ በፀሃይ ኃይል አማራጭ (ኦፍግሪድ) የተገናኙ መሆናቸውን ሰምተናል፡፡ በተጨማሪም 423,200 አዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ያለ ሲሆን ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ18 ነጥብ 6 በመቶ ብልጫ አለው ተብሏል፡፡ ኃይል
May 41 min read


የኦሞ ኩራዝ ቁጥር ሁለት ስኳር ፋብሪካ ያሉበት ውስብስበ ችግሮች ካልተፈቱለት ለግንባታ የፈጀውን የ341.1 ሚሊዮን ዶላር ብድርን ለመከፍል እንደሚቸገር ፓርላማው አሳሰበ፡፡
ሚያዝያ 26/2018 የኦሞ ኩራዝ ቁጥር ሁለት ስኳር ፋብሪካ ያሉበት ውስብስበ ችግሮች ካልተፈቱለት ለግንባታ የፈጀውን የ341.1 ሚሊዮን ዶላር ብድርን ለመከፍል እንደሚቸገር ፓርላማው አሳሰበ፡፡ በህዝብ ተወካይዎች ምክር ቤት የመንግስት ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ2018 በጀት ዓመት የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 1፣ 2 እና 3 የስኳር ፋብሪካዎች እና የኦሞ ኩራዝ 5 ፋብሪካ ግንባታ ፕሮጀክትን ተመልክቶ የግብረ መልስ ሪፖርት አሰናድቷል፡፡ በሪፖርቱ መሰረት የኦሞ ኩራዝ ቁጥር ሁለት ስኳር ፋብሪካ የተገነባው በብድር በተወሰደ የ341.1ሚልዮን ዶላር ሲሆን በቀን ፋብሪካው የሚፈጨው የአገዳ መጠን 12 ሺህ ቶን ነው፡፡ ይሁንና ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች በመኖሪያ ቤት፣ በውሃ፣ በባንክና በኢንተርኔት አገልግሎት እጥረት እና በጥቅማጥቅምና በደመወዝ ማነስ ምክንያት ፋብሪካው
May 42 min read


ዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ሸሪክ ከደንበኞቼ በአደራ መልክ የሰበሰብኩትን 16.9 ሚሊየን ብር ለግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ድጋፍ አደረግሁ አለ።
ሚያዝያ 24/2018 ዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ሸሪክ ከደንበኞቼ በአደራ መልክ የሰበሰብኩትን 16.9 ሚሊየን ብር ለግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ድጋፍ አደረግሁ አለ። 30ኛ ዓመቱን ምክንያት በማድረግ ባንኩ ባዘጋጀው ዳሸን ኤክስፖ የማጠናቀቂያ መርሐ ግብር፤ የዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ሸሪክ የ8 ዓመት የስኬት ጉዞን አስመልክቶ ማብራሪያ ተሰጥቷል። በመርሐ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት በዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ቺፍ ኦፊሰር አቶ አምዱ ሰማን ባንኩ ጠንካራ የሸሪዓ አማካሪ ኮሚቴ በማቋቋም የማህበረሰቡን ዕሴቶች ያከበሩና ሸሪዓውን የጠበቁ አገልግሎቶች መስጠቱን አጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። የዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት 'ሸሪክ' ከሚሰጣቸው ዘመናዊና አካታች የባንክ አገልግሎቶች ባሻገር ማህበራዊ ሐላፊ
May 21 min read


ዘንድሮ 34 የመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቅቆ እንደሚመረቁ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ተናገረ፡፡
ሚያዝያ 24/2018 ዘንድሮ 34 የመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቅቆ እንደሚመረቁ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ተናገረ፡፡ ከ500 በላይ የመንገድ ፕሮጀክሮችን እየሰራ መሆኑን የሚጠቅሰው አስተዳደሩ ከግማሽ በላዩ እየተሰሩ ያለው በሃገር ውስጥ ስራ ተቋራጮች ነው ብሎናል፡፡ አንዱና አካባቢ ከሌላው ገጠሩን ከከተማው የሚያገኛኙ የመንገድ ግንባታዎች፣ ጥገናዎችና የዲዛይን ስራዎች እየተሰራባቸው ያሉ ከ500 በላይ ፕሮጀክቶች እንዳሉ የነገሩን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር መሃመድ አብዱራህማን፣ ከእነዚህ መካከል የፈጣን መንገዶችን፣ ክልሎችን እርስ በስርስ የሚያገናኙ፣ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ተነስተው በ5 አቅጣጫ የሚወጡ ፕሮጀክቶች ናቸው ብለውናል፡፡ ለመሆኑ የኢትዮጵያ የመንገድ ሽፋን ምን ያህል ደርሷል?ያልናቸው ሃላፊው ከ24ዓ
May 21 min read


ስራ ፈጣሪዎች የሚያግዝ ፕሮግራም ይዞ መምጣቱን ክሪኤቲቭ ኪንግደም ተናገረ።
ሚያዝያ 24/2018 በየዘርፉ የስራ ፈጠራ ኖሯቸው የፈጠሩትን ስራ ወደ ተግባር የሚለውጡበት ያጡ ስራ ፈጣሪዎች የሚያግዝ ፕሮግራም ይዞ መምጣቱን ክሪኤቲቭ ኪንግደም ተናገረ። የራሳቸው መሆኑ ታውቆላቸው በአእምሮአዊ ንብረት ያስመዘገቡ ስራ ፈጣሪዎች ጭምር ፈጠራቸውን በገንዘብ፣ በሀሳብ፣ በመስሪያ ቦታ በመሳሰሉት የሚደግፋቸው ያጡ ሰዎች በየቦታው አሉ። ይህንን ችግር ለመፍታት፣ ስራ ፈጣሪዎች የሚታገዙበት ክሬቲቭ ኪንግደም የተባለ ፕሮግራሙን ስራ መጀመሩን ሰምተናል። ፕሮግራሙ ስራ ፈጣሪዎች ፈጠራቸውን ወደ ተግባር እንዲለብጡ፣ ህብረተሰቡም ለስራ ፈጣሪዎቹ ዋጋ እንዲሰጥ ያስችላል ሲሉ የክሪኤቲብ ኪንግደም ዋና ስራ አስፈጻሚ ታደሰ ኃይሉ ነግረውናል። ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ማርታ በቀለ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡...
May 21 min read


በኢትዮጵያ የአሉሚኒየም ምርቶች ላይ የተሰማራው ''ቴክሃፍ አሉሚኒየም'' አለም አቀፍ የጥራት መስፈርቶችን በማሟላት እውቅና ማግኘቱ ተነገረ
ሚያዝያ 22/2018 በኢትዮጵያ ለአውሮፕላን ማረፊያዎች፣ የሃይል ማመንጫዎች፣ኢንደስትሪ ፓርኮችና ሌሎችም ግዙፍ የግንባታ ስራዎች የሚውሉ የአሉሚኒየም ምርቶች ላይ የተሰማራው ቴክሃፍ አሉሚኒየም የተባለ ተቋም አለም አቀፍ የጥራት መስፈርቶችን በማሟላት እውቅና ማግኘቱ ተነገረ፡፡ ተቋሙ በቅርቡ ወደ አለም አቀፍ ገበያ እንደሚቀላቀለም ጠቅሷል፡፡ ቴክሃፍ አሉሚኒየም አራት ዓለም አቀፍ የጥራት ምስክር ወረቀቶችን ማግኘቱ የተነገረ ሲሆን እውቅናዎቹ በኢትዮጵያ የተሰሩ ምርቶች በዓለማቀፍ ገበያ ገብተው እንዲወዳደሩ ለማድረግ በር የሚከፍት ነው ተብሏል፡፡ በዓለም ላይ የአሉሚኒም ምርቱ ካለው የምርት እድገት አንጻር የኢትዮጵያ ዝቅተኛ መሆኑን የሚያነሱት የቴክሃፍ አሉሚኒየም የሽያጭ ክፍል ሃላፊ የሆኑት አቶ ጌታሁን ጥላሁን ተቋማቸው ይህንን ክፍተት ለማጥበብና የኢትዮጵያ
Apr 301 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

