top of page


ለመጪው ሀገራዊ ምርጫ ለመራጭነት ካርድ የወሰዱ አካል ጉዳተኞች ከእቅዱ 3 በመቶ ብቻ መሆናቸውን የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ተናገረ፡፡
ሚያዝያ 22/2018 ለመጪው ሀገራዊ ምርጫ ለመራጭነት ካርድ የወሰዱ አካል ጉዳተኞች ከእቅዱ 3 በመቶ ብቻ መሆናቸውን የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ተናገረ፡፡ አካል ጉዳተኞች አጠቃላይ ከማህበረሰቡ ከ17 በመቶ በላይ መሆናቸው ይነገራል፡፡ ከመካከላቸው 5 ሚሊየኑ የምርጫ ካርድ ይወስዳሉ ተብሎ ቢጠበቅም የወሰዱት ግን 167,000 ብቻ ናቸው ሲል ፌዴሬሽኑ ነግሮናል። የምርጫ ካርድ የወሰዱ አካል ጉዳተኞች ቁጥር ዝቅተኛ የሆነበት የመረጃ ክፍተት ምክንያት አንዱ እንደሆነም ተነግሯል። ይህን የነገሩን የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይነህ ጉጆ አብዛኛው አካል ጉዳተኛ የምርጫ ካርድ አለመውሰድ ጋር በተያያዘ ቅሬታችንን ለምርጫ ቦርድ አቅርበናል፤ እንደ ሃሳብ ያቀረብነውም የመራጮች ምዝገባ እንዲራዘም የሚል ነበር
Apr 301 min read
አቢሲንያ ባንክ ˝እችላለሁ˝ 5ኛ ዙር የ2025 BYD Seagull ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪና የሎተሪ እድለኛን ለመለየት የእጣ ማውጠት ስነ ስርዓት አከናወነ፡፡
ሚያዝያ 22/2018 አቢሲንያ ባንክ ˝እችላለሁ˝ 5ኛ ዙር የ2025 BYD Seagull ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪና የሎተሪ እድለኛን ለመለየት የእጣ ማውጠት ስነ ስርዓት አከናወነ፡፡ ዛሬ በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት መድረክ ከ2.3 ሚሊዮን በላይ የኩፖን ቁጥሮችን መሠረት በማድረግ የ2025 BYD Seagull ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪና ዕድለኛን ለመለየት የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል፡፡ አቢሲኒያ ባንክ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን (March 8) በማስመልከት፣ “እችላለሁ ” በሚል መሪ ቃል ለ5ኛ ጊዜ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ አቅም የሚያጎለብት መርሐ-ግብር ማካሄዱ ይታወሳል፡፡ ባንኩ ባሰናዳው መርሀ ግብር ላይም በደም እጥረት ምክንያት የሚከሰተውን የእናቶች ሞት ለመቀነስ፣ ሀገር አቀፍ የደም ልገሳ ዘመቻ ያከናወነ ሲሆን በዚህም 3,012 ዩኒት ደም መሰብሰብ
Apr 301 min read


የፌድራል መንግስት በመንፈቅ ዓመቱ 93.3 ቢሊዮን ብር የበጀት ጉድለት እንደገጠመው የገንዘብ ሚኒስቴር ያውጣው የግማሽ ዓመት ሪፖርት አሳየ፡፡
ሚያዝያ 22/2018 የፌድራል መንግስት በመንፈቅ ዓመቱ 93.3 ቢሊዮን ብር የበጀት ጉድለት እንደገጠመው የገንዘብ ሚኒስቴር ያውጣው የግማሽ ዓመት ሪፖርት አሳየ፡፡ በሌላ በኩል የዘንድሮ የንግድ ሚዛን ልዩነት 6.2 ቢሊዮን ዶላር መሆኑም ተጠቅሷል፡፡ የገንዘብ ሚኒስቴር ባወጣው ዘርዘር ያለና የበጀት አጠቃቀምን በሚያሳየው ሪፖርቱ ባለፉት 6 ወራት ከታክስና ታክስ ካልሆኑ ምንጮች የተሰበሰበው ገቢ እንዲሁም አጋር ከተባሉ አካላት የተገኘውን ጨምሮ አጠቃላይ ገቢው 704.7 ቢሊዮን ብር መሆኑን ይጠቅሳል፡፡ ይሁንና በዚሁ ጊዜ ለመደበኛ፣ ለካፒታል ወጪዎችና ለክልሎች የተሰጠው የበጀት ድጎማ ተዳምሮ ወጪውን 798.2 ቢሊዮን ብር አድርሶታል፡፡ በዚህም ወጪውና ገቢው ባለመመጣጠኑ የ93.3 ቢሊዮን ብር የበጀት ጉድለት እንደገጠመ በሪፖርቱ ተጠቅሷል፡፡ የገጠመው የበጀት
Apr 302 min read
በ"ፊንቴክ ኢንቨስትመንት" ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ ዓቃቢ ህግ ክስ እንዲመሰርት 7 ቀናት ተፈቀደለት፡፡
ሚያዝያ 21/2018 በ"ፊንቴክ ኢንቨስትመንት" ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ ዓቃቢ ህግ ክስ እንዲመሰርት 7 ቀናት ተፈቀደለት፡፡ በፊንቴክ ኢንቨስትመንትሽፋን በተፈጸመ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮችን ጉዳይ ለመመልከት የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዛሬ ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ለ ዓቃቢ ህግ ክስ መመስረቻ 7 ቀን የፈቀደው፡፡ ፍርድ ቤቱ ለዛሬ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው ፖሊስ የምርመራ ስራዎችን አጠናቆ አንዲያቀርብ ነበር፡፡ በዛሬው ችሎትም ፖሊስ ምርመራውን መጨረሱንና ጉዳዩን ለዓቃቢ ህግ ማስተላለፉን አስረድቷል፡፡ ዓቃቢ ህግም ክስ ለመመስራት ፍርድ ቤቱን 10 ቀናት ጥይቆ 7 ቀናት ተፈቅዶለታል፡፡ በዚህም ለሚያዚያ 28/2018 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ የፊንቴ
Apr 291 min read


አዲስ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ለሚያስገቡ ደንበኞች የሁለት አመት የክፍያ ስርዓት ማመቻቸቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ።
ሚያዝያ 21/2018 አዲስ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ለሚያስገቡ ደንበኞች የሁለት አመት የክፍያ ስርዓት ማመቻቸቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ። በገንዘብ እጥረት ምክንያት ለአዲስ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ የሚያስፈልገውን ክፍያ ከፍለው አገልግሎት ማግኘት ላልቻሉ ደንበኞች የተዘረጋው ይህ አሰራር እስከ 2 ዓመት በሚደርስ የክፍያ ስርዓት እንዲከፍሉ የሚያደርግ ነው ተብሎለታል። ተቋሙ ወደ ስራ ያስገባውን አዲስ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን የሚችሉትም የነጠላ ፌዝ ቆጣሪ ተጠቃሚ ደንበኞች ናቸው የተባለ ሲሆን የመኖሪያ ቤት እና አነስተኛ ንግድ ቤቶችን ያጠቃልላል ተብሏል። ይህንን አሰራር የጀመርኩት ጥናትን መሰረት አድርጌ ነው ያለው አገልግሎቱ በርካታ ደንበኞቼ በገንዘብ እጥረት ምክንያት አዲስ ቆጣሪ ማስገባት መቸገራቸውን ጥናቱ አሳይቷል ብሏል። ደንበኛው የጊዜ ገደ
Apr 291 min read


የናፍታ ነዳጅ አቅርቦት መጠን ከመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በፊት ወደ ነበረበት እንዲመለስ መንግስት መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ተናገሩ።
ሚያዝያ 21/2018 የናፍታ ነዳጅ አቅርቦት መጠን ከመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በፊት ወደ ነበረበት እንዲመለስ መንግስት መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ተናገሩ። ሚኒስትሩ በሰጡት መግለጫ ፥ በአሁኑ ወቅት ያለውን የምርትና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ በማየት የናፍታ አቅርቦት ወደነበረበት እንዲመለስ መንግሥት ወስኗል ብለዋል። በማደያዎች ይቀርብ የነበረው የናፍታ አቅርቦት በቀን በግማሽ ቀንሶ እንደነበር ይታወሳል። በዚህም መሰረት በቀን ይቀርብ የነበረው ናፍታ 4 ነጥብ 5 ሚሊየን ሊትር እንዲሆን ተወስኖ ነበር። አሁን ላይ ግን ከጦርነቱ በፊት ይቀርብ የነበረው በቀን 9 ሚሊየን ሊትር ናፍታ እንዲገባ መንግስት ወስኗል ብለዋል። ለዚህም መንግሥት ተጨማሪ 20 ቢሊየን ብር በወር ለነዳጅ ድጎማ እንደሚያደርግ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ተናግረዋል። ናፍታው ከ
Apr 291 min read


በአለም አቀፍ ደረጃ የሚፈጠሩ ቀውሶች የመድኃኒት አቅርቦትና ግዢ ስርዓቱን እንዳያስተጓጉል አለም አቀፍ አምራቾች እና አቅራቢዎች በጋራ መስራት አለባቸው ተባለ።
ሚያዝያ 20/2018 በአለም አቀፍ ደረጃ የሚፈጠሩ ቀውሶች የመድኃኒት አቅርቦትና ግዢ ስርዓቱን እንዳያስተጓጉል አለም አቀፍ አምራቾች እና አቅራቢዎች በጋራ መስራት አለባቸው ተባለ። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት 5ኛውን ዓለም አቀፍ የመድኃኒት አቅራቢዎች ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ እያካሄደ ነው። ጦርነት ፣ ወረርሽኞች ተጽዕኖ ከሚያሳድርባቸው ዘርፎች አንዱ የመድኃኒት አቅርቦት ነው ሲሉ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተሩ አብዱልቃድር ጋልገሎ (ዶ/ር) ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በፋርማሱቲካል ኢንደስትሪ ዘርፍ ከአፍሪካ እያደገ የመጣ የገበያ ስርአት ዘርግታለች ብለዋል። የመድኃኒት አቅርቦት እና ስርጭት ለማቀላጠፍ አዳዲስና የዲጂታል አሰራሮች ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሆነም ጠቅሰዋል። ሀገሪቱ ለመድኃኒትና ህክምና
Apr 281 min read
የቤት ገዢዎችን የመግዛት አቅም ለማበርታት እንዲያግዝ ፖሊሲ የተዘጋጀለት የሞርጌጅ ባንክ እንዲቋቋም ተጠየቀ።
ሚያዝያ 20/2018 የቤት ገዢዎችን የመግዛት አቅም ለማበርታት እንዲያግዝ ፖሊሲ የተዘጋጀለት የሞርጌጅ ባንክ እንዲቋቋም ተጠየቀ። በኢትዮጵያ ያለው የግለሰቦች ቤት የመግዛት አቅም ከጊዜ ጊዜ እየቀነሰ መምጣት፣የብርየመግዛት አቅም መዳከም የግለሰቦች ቤት የመግዛት አቅም አብሮ ተዳክሟል ይላሉ የሪል እስቴት አልሚዎች። የኢትዮጵያ የሪል እስቴት አልሚዎች ማህበር የቦርድ አባላት እንደነገሩን የቤቶች ግንባታ በውጭ ምንዛሪ ላይ መሰረት ያደገ ነው፣ 55 በመቶ የግንባታ ግብዓቶች ተገዝተው የሚመጡት በውጭ ምንዛሪ ነው ብለውናል፡፡ በተዘዋዋሪ መንገድ ጥቅም ላይ የሚውሉት ግብዓቶች ሲጨመሩ የቤት ግንባታ ዘርፉ እስከ 75 በመቶ ወጪው የውጭ ምንዛሪ ላይ የተንጠለጠለ ነው፤ ለዚህ ነው የዶላር ዋጋ ሲጨምርየቤት ዋጋም የሚጨምረው ሲሉ ያስረዳሉ፡፡
Apr 282 min read


ከክልሎች ጋር በመተባበር 1 ሺህ 452 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመገንባት ማቀዱን የትምህርት ሚኒስቴር ተናገረ።
ሚያዝያ 20/2018 ከክልሎች ጋር በመተባበር 1 ሺህ 452 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመገንባት ማቀዱን የትምህርት ሚኒስቴር ተናገረ። አዲስ የሚገነቡት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በ727 ወረዳዎች ውስጥ ነው ተብሏል፡፡ 626 ትምህርት ሚኒስቴር የሚገነባ ሲሆን ቀሪው ደግሞ ክልሎች እራሳቸው እንደሚገነቡ ተነግሯል። ለዚህ ስራ የሚያስፍልገው 40 ሚሊዮን ዶላር ከአጋር ድርጅቶች እርዳታ ተገኝቷል ተብሏል። እስካሁን 460 የሚሆኑ ኮንትራክተሮች የተመረጡ ሲሆን ቀሪው ደግሞ በሚቀጥሉት ጊዜያት ለመፈለግና በዚህ አመት ግንባታው አጠናቆ በ2019 ወደ ስራ ለመግባት መታቀዱን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል። ይህ ስራ ሲጠናቀቅ 87 ሺ አዲስ ተማሪዎች ወደ ትምህርት እንዲቀላቀሉ ያደርጋል ተብሏል። በ
Apr 281 min read
በኢትዮጵያ በፋይናንስ ተቋሞች የተከፈተ የቁጠባ ሂሳብ ቁጥር ከ176 ሚሊየን በላይ ደርሷል።
ሚያዝያ 20/2018 በኢትዮጵያ በፋይናንስ ተቋሞች የተከፈተ የቁጠባ ሂሳብ ቁጥር ከ176 ሚሊየን በላይ ደርሷል። ከዚህ የባንክ ሂሳብ 97 በመቶው ግን ከ100 ሺህ ብር በታች ገንዘብ የተቀመጠበት መሆኑ ተነግሯል። በኢትዮጵያ የፋይናንስ ተቋሞች በኪሳራ ምክንያት ቢዘጉ ገንዘቡን የቆጠበው ሰው ያስቀመጠውን እንዳያጣ ለመካስ በሚል የተቋቋመው የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ስራ ከጀመረ ሶስት ዓመት ሆኖታል። ፈንዱ በዚህ ጊዜ ከባንኮችና ሌሎች የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት የሰበሰበው የአረቦን ገንዘብ ከ20 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱ ተነግሯል። ከጠቅላላ አረቦኑ አብዛኛው ወይም 10.41 ቢሊዮን ብሩ ከግል ባንኮች የተሰበሰበ እንደሆነ ፈንዱ ከላከልን መረጃ ላይ ተመልክተናል። 9.96 ቢሊዮን ብሩ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፤ ቀሪው 0
Apr 281 min read


ኢትዮጵያ እና ቻይና ባለፈው ዓመት 8.5 ቢሊዮን ዶላር የንግድ ልውውጥ አድርገዋል፡፡
ሚያዝያ 20/2018 ኢትዮጵያ እና ቻይና ባለፈው ዓመት 8.5 ቢሊዮን ዶላር የንግድ ልውውጥ አድርገዋል፡፡ ከዚህ ውስጥ 8 ቢሊዮን ዶላሩ ቻይና ወደ ኢትዮጵያ ሸቀጦቿን ልካ ያገኘቺው ገቢ ሲሆን ቀሪው 5 መቶ ሚሊዮን ዶላሩ የኢትዮጵያ ምርቶች በቻይና ገበያ ያወጡት ዋጋ ነው፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የንግድ ሚዛን ልዩነቱ እጅግ ሰፊ ነው፡፡ የሁለቱ ሀገራት የንግድ ትስስር የበለጠ እንዲጠብቅ ካደረጉ ማህበራት መካከል የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክርቤት ቀዳሚው እንደሆነ ይነገራል፡፡ የምክር ቤቱ ምክትል ዋና ፀሀፊ አቶ ካሳሁን ማሞ የሁለቱ ሀገራት የንግድ ትስስር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን ይናገራሉ፡፡ የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ቻይና ከሚገኙ የተለያዩ የንግድ ማህበራት ጋር የጋራ ስምምነት እየተዋዋለ መሆኑን የ
Apr 281 min read


የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ "ጉዞ ወደ FIFA የዓለም ዋንጫ 2026"በሚል ሲያካሂድ በነበረው የሽልማት መርሐ ግብር አሸናፊ የሆኑትን ሁለት እድለኞች ይፋ አደረገ።
ሚያዝያ 17/2018 የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ "ጉዞ ወደ FIFA የዓለም ዋንጫ 2026"በሚል ሲያካሂድ በነበረው የሽልማት መርሐ ግብር አሸናፊ የሆኑትን ሁለት እድለኞች ይፋ አደረገ። ባንኩ ከቪዛ ካርድ ጋር በመሆን የቪዛ ካርዶቹን ለሚጠቀሙ ደንበኞቹ በሰሜን አሜሪካ ለሚካሄደው የዘንድሮ የአለም ዋንጫ ሁለት ባለዕድለኞች ጉዞ ሙሉ ወጪያቸውን እንደሚሸፍን መናገሩ ይታወሳል። ሁለቱ አሸናፊዎችን ለማወቅ መርሃግብሩ ሲካሄድ የቆየው ከመጋቢት 12 እስከ ሚያዚያ 16/2018 ድረስ ነው። ዛሬ በወጣው ሽልማት ተሳታፊ ለመሆን ባንኩ በቅርቡ ወደ ሥራ ያስገባቸው ሶስት የካርድ አገልግሎቶች፣ በሀገር ውስጥ POS ማሽኖች ላይ ከብር 200 ባላይ ከፍያዎች የፈጸሙ፣ በባንኩ ATM ብር 1000 እና ከዛ በላይ ገንዘብ ያስገቡ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ከ20 ዶላር በላ
Apr 251 min read


ከወረቀት አሰራር፤ ከፊት ለፊት ተገናኝቶ ከመስራት ያልተላቀቀው የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ዘርፍ
ሚያዝያ 17/2018 ከወረቀት አሰራር፤ ከፊት ለፊት ተገናኝቶ ከመስራት ያልተላቀቀው የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ዘርፍ የሚሰጠውን አገልግሎት ወደ ዲጅታላይዜሽን አለመቀየሩ ቋሚ ተገልጋይ ደንበኞቹን እያሳጣው ነው ተባለ፡፡ ቴክኖሎጅን ታግዞ አገልግሎት መስጠት የማይችል ከሆነ ዘፉር ችግር ላይ መውደቁ እንደማይቀር የዘርፉ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ ባለሙያዎቹ ይህንን ያሉት በኢትዮጵያ የኢንሹራንስ ዘርፍ ዲጅታላይዜሽን እና የደንበኛ ታማኝነት ያላቸው ግንኙነት በሚል በቀረበ ጥናት ላይ ነው፡፡ የኢንሹራንስ ዘርፉ እስካሁን ለደንበኞቹ አገልግሎት ለመስጠትም ሆነ ሌሎች ስራዎቹን የሚከውነው ቴክኖሎጅን ተጠቅሞ ባለመሆኑ መስራት በሚገባው ልክ እንዳይሰራ እና ወደ ኋላ እንዲቀር አድርጎት ቆይቷል ተብሏል፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ እሰራችነበት ያለው የ2030 ዲጅታላይዜሽን እቅድ ዘር
Apr 251 min read


የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት 27ተኛውን አለማቀፍ አዲስ ቻምበር የንግድ ትርኢት ማካሄድ ጀመረ፡፡
ሚያዝያ 16/2018 የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት 27ተኛውን አለማቀፍ አዲስ ቻምበር የንግድ ትርኢት ማካሄድ ጀመረ፡፡ ይህ የንግድ ትርኢት የሀገር ውስጥ የንግዱ ማህበረሰብ ከሌሎች ሀገራት አቻቸው ጋር የገብያ ትስስር እንዲፈጥሩ እድል እያመቻቸ ነው ተብሏል፡፡ የአዲስ አበባ ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ዘሃራ መሃመድ ከዚህ ቀደም የተዘጋጁ የንግድ ትርኢቶች የንግዱ ማህበረሰብ ያለው የገብያ ትስስር እንዲሰፋ አድርጓል ብለዋል፡፡ የንግዱ ዘርፍ ከተማ ውስጥ እንዲሰፋ ለማድረግ ምክር ቤቱ ላለፉት 10 አመታት ዋንኛ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ነው ያሉ ሲሆን ሀገሪቱ ከአለማቀፍ ንግድ አቀላጣፊ ማህበራት ጋር ያላት ግንኙነት የተሻለ እንዲሆን የበኩሉን አስተዋፅኦ እያደረገ ነው ይላሉ፡፡ በየአመቱ በሚዘጋጀው አለማቀፍ አዲስ
Apr 241 min read


የንጹህ መጠጥ ውሃ ለማዳረስ ፈጠራ ላይ የተሰማሩ የግል ተቋማት የፋይናንስ አቅርቦት ላይ መሰራት አለበት ተባለ
ሚያዝያ 16/2018 የንጹህ መጠጥ ውሃና ከንጽህና አጠባበቅ ጋር የተያያዙ ስራዎችን በኢትዮጵያ ለማዳረስ ስራ ፈጠራ ላይ የተሰማሩ የግል ተቋማት የፋይናንስ አቅርቦት ላይ መሰራት አለበት ተባለ፡፡ የንጹህ መጠጥ ውሃና ንጽህና አጠባበቅ ወይም ሳኒቴሽን አገልግሎቶችን ማግኘት መብት ቢሆንም በኢትዮጵያ በብዙ ምክንያቶች ይህንን የሚያገኙት ካለው የህዝብ ቁጥር አኳያ ግን በቂ አይደሉም ተብሏል፡፡ በኢትዮጵያ ከ10 ዓመታት በላይ በንጹህ መጠጥ ውሃና የሳኒቴሽን አገልግሎቱን በመደገፍ ሲሰራ የቆየው አኳ ፎር ኦል የተባለ አለምዓቀፍ ተቋም በዘርፉ የፋይናንስ ድጋፍ ከሚያቀርቡ ተቋማትና በግል በስራው ላይ ከተሰማሩ ድርጅቶች ጋር ባካሄደው ምክክር ላይ ነው ይህንን የሰማነው፡፡ በግል የንጹህ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን አቅርቦት ላይ አገልግሎቱን ለመስጠት የፋይናንስ ምንጭ ማግኘ
Apr 242 min read


በኦሮሚያ ክልል የሚከሰቱ የበሽታ ወረርሽኞችን እና አጣዳፊ የምግብ እጥረት ችግሮችን ለመከላከል የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ ሆነ።
ሚያዝያ 15/2018 በኦሮሚያ ክልል የሚከሰቱ የበሽታ ወረርሽኞችን እና አጣዳፊ የምግብ እጥረት ችግሮችን ለመከላከል የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ ሆነ። ይህንን ፕሮጀክት ይፋ ያደረገው ፈያ ኢንተግሬትድ ዴቬሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን ሲሆን ፕሮጀክቱ ለ6 ወር እንደሚቆይ እና 4.5 ሚሊዮን ዶላር እንደተመደበለትም ሰምተናል። የድርጅቱ መስራች እና ዋና ዳይሬክተር አንበሱ ቶላ (ዶ/ር) እንዳሉት ይህ ባለብዙ ዘርፍ የአስቸኳይ ጊዜ ምላሽ ፕሮጀክት በጤና፣ በሥርዓተ-ምግብ እና በንፁህ መጠጥ ውሃ ዘርፎች ላይ ያተኮረ ነው ሲሉ ነግረውናል። የ4.5 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የተመደበለት ፕሮጀክቱ ለዚህም በአሜሪካ መንግሥት የሚደገፈው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ ፈንድ (EHF) ድጋፍ አድርጓል። የፕሮጀክቱ ዋና ግብ በኦሮሚያ ክልል 5 ዞኖች በተመረጡ 7 ወረዳዎች ውስጥ ለሚገኙ 295 ሺ
Apr 231 min read


የዲዛይን ችግር፣ የፀጥታ መደፍረስና የወሰን ማስከበር ላይ በሚያጋጥሙ ፈተናዎች እና የበጀት እጥረት ዘጠኝ ያህል የመስኖ ፕሮጀክቶች መስተጓጎላቸው ተነገረ፡፡
ሚያዝያ 15/2018 የዲዛይን ችግር፣ የፀጥታ መደፍረስና የወሰን ማስከበር ላይ በሚያጋጥሙ ፈተናዎች እና የበጀት እጥረት ዘጠኝ ያህል የመስኖ ፕሮጀክቶች መስተጓጎላቸው ተነገረ፡፡ የመስኖና ቆላማ ሚኒስቴር እንዳለው ከተጠቀሱት ችግሮች ባሻገር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የነዳጅ አቅርቦት ችግርም ለመስኖ ፕሮጀክቶች ፈተና ሆኗል፡፡ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የዘጠኝ ወራት የስራ ክንውን ሪፖርት እንደሚያሳየው የዲዛይን ስራቸው ሳይጠናቀቅ የተጀመሩ አንዳንድ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ስራ መጀመር ካለባቸው ጊዜ የመዘግየት ችግር አጋጥሟቸዋል፡፡ ከመካከላቸው የሎግያ ፣ ፈንታሌ ፣ ሽንሌና አንገር የመስኖ ፕሮጀክቶች ጥልቅ ጥናት ባልተደረገባቸው ዲዛይኖች የተጀመሩ ናቸው ተብሏል፡፡ በመሆኑም በአማካሪ ድርጅቶች የዲዛይን ማስተካከያ ተደርጎላቸው ወደ ስራ እስኪመለሱ የመዘግየት ችግር
Apr 232 min read


ከቀናት በፊት በተከበረው የፋሲካ በዓል ወቅት የሸማቾች ህብረት ስራ ማህበራት አንድ ኪሎ ስጋ በ650 ብር እንዲሸጡ ተወስኖ በዚሁ መሰረት ሲያቀርቡ ቆይተዋል።
ሚያዝያ 15/2018 ከቀናት በፊት በተከበረው የፋሲካ በዓል ወቅት የሸማቾች ህብረት ስራ ማህበራት አንድ ኪሎ ስጋ በ650 ብር እንዲሸጡ ተወስኖ በዚሁ መሰረት ሲያቀርቡ ቆይተዋል። ዋጋው አያዋጣንም ያሉ አንዳንድ የሸማቾች ህብረት ስራ ማህበራት ግን በሱቆቻቸው ስጋ አልነበረም። ለመሆኑ ማህበራቱ ያለ ትርፍ አንዳንዴም በኪሳራ ምርቶቹን እንዲሸጡ ማድረግ ትክክል ነው ወይ? የህብረት ስራ ማህበራት የተቋሙበት አላማ ሸማቾች ጥራት ያለው ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ፤ አምራቾችም ለምርታቸው ተገቢው ክፍያ እንዲፈጸምላቸው ማድረግ የሚል ነው። ብዙዎችም በተለይ የፍጆታ ምርቶችን በእነዚሁ ማህበራት ከተቋቋሙ ሱቁች በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት እንደቻሉ ይናገራሉ። በሌላ በኩል የሸማች ህብረት ስራ ማህበራት ምርቶችን የሚሸጡበት ዋጋ ገደብ የተቀመጠለት ስለሆነ ሊኪሳራ እየ
Apr 232 min read


''የጣሊያንና የኢትዮጵያ የንግድ ትስስር ከባለፉት ዓመታት አንፃር የ10 በመቶ እድገት አሳይቷል'' በኢትዮጰያ የኢጣሊያ ኤምባሲ
ሚያዝያ 15/2018 የጣሊያን እና የኢትዮጵያ የንግድ ትስስር ከባለፉት ዓመታት አንፃር የ10 በመቶ እድገት አሳይቷል ሲል በኢትዮጰያ የኢጣሊያ ኤምባሲ ተናገረ፡፡ የጣሊያን ኤምባሲ በኢትዮጵያ የንግድ ኮሚሽነር የሆኑት ክላውዶ ባስካሉች የሁለቱ ሃገራት የንግድ ትስስር ከዚህም በላይ የማደግ ትልቅ ዕድል አለው ብለዋል። ኮሚሽነሩ ይህንን ያሉት ከ20 በላይ የጣሊያን ኩባንያዎች የሚሳተፉበት የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ምርቶች ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንሼንሽን ሴንተር የመክፈቻ መድረክ ላይ ነው። የጣሊያን ኤምባሲ ንግድ ኮሚሽነር ክላውዶ ኤግዚቢሽኑ የጣሊያን አምራች ተቋማት በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ላይ ያበረከቱትን አስተዋፅኦ የሚያሳይ ነው ብለዋል። የጣሊያን ኩባንያዎች ኢንቨስትመንት በኢትዮጵያ 723 ሚሊየን ዩሮ መድረሱም ተጠቅሷል። የጣ
Apr 232 min read


ባለፈው ዓመት የወጣውን የሪል ስቴት አዋጅ ለማስፈፀም የሚያስችል ደምብ ዝግጅት ተጠናቅቆ ወደ ስራ ሊገባ መሆኑ ተነገረ።
ሚያዝያ 15/2018 ባለፈው ዓመት የወጣውን የሪል ስቴት አዋጅ ለማስፈፀም የሚያስችል ደምብ ዝግጅት ተጠናቅቆ ወደ ስራ ሊገባ መሆኑ ተነገረ። ይህ የተባለው በዛሬው ዕለት የመጀመሪያው የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ጉባኤና አዲስ አፍሪካ የተሰኘው የሪል ስቴት ኤግዚቢሽን በተከፈተበት ወቅት ነው። የሪል ስቴት አዋጅ ማስፈጸሚያ ደምቡን ያዘጋጀው የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር መሆኑንና በአዋጁ የተካተቱ የገዢውንም የአልሚውንም ጥቅም የሚያስጠብቁ አሰራሮችን የሚቀይስ መሆኑን በሚኒስቴር መ/ቤቱ የቤቶች ልማት ጥናት የግል ሴክተር ተሳትፎ ዴስክ ሃላፊ አቶ ታፈሰ ነጋ ነግረውናል። "አዲስ አፍሪካ" የተሰኘው ይህ የሪል ስቴት ኤግዚቢሽን መዲናዋን የአፍሪካ የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ማዕከል ለማድረግ ያለመ ነው ተብሏል። ዛሬን ጨምሮ የፊታችን ለ4 ተከታታይ ቀናት በሚቆየው
Apr 231 min read
ፖሊስ በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደለት፡፡
ሚያዝያ 14/2018 ፖሊስ በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደለት፡፡ ፖሊስ ተጨማሪ 14 ቀን ለምርመራ እንዲፈቀድለት ባለፈው አርብ በነበረው ችሎት ጠይቆ ለውሳኔ ፍርድ ቤቱ ለዛሬ ቀጥሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡ በ"ፊንቴክ"(Fintech) ኢንቨስትመንት ሽፋን በተፈጸመ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮችን ጉዳይ ፖሊስ በጠየቀው የተጨማሪ ጊዜ ላይ ለመወሰን የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዛሬ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ለፖሊስ የ7 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል። ባለፈው ሚያዚያ 9 2018 ዓ/ም በነበረው ችሎት ባለፉት ቀናት ያከናወናቸውን ተግባራት ለችሎቱ ያስረዳው ፖሊስ፣ ነገር ግን ከወንጀሉ ውስብ
Apr 221 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

