top of page


በበጀት ዓመቱ ሰባት ወራት ከ800 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናግረዋል።
ጥር 26/2018 በበጀት ዓመቱ ሰባት ወራት ከ800 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናግረዋል። የሰባት ወራቱ አፈጻጸም የዓመቱ ዕቅድ ቀድሞ እንደሚሳካ የሚያመለክት ነው ብለዋል። ያለውን አፈጻጸም ተከትሎ በፌዴራል ደረጃ የተቀመጠውን የ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ዕቅድ ወደ 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር የማሳደግ ሃሳብ እንዳለ ጠቅሰዋል። ክልሎች የሚሰበስቡትን ገቢ ደግሞ 1 ትሪሊየን ብር እንዲደርስ መታሰቡን አመልክተዋል። በዚህም በአጠቃላይ 2 ነጥብ 5 ትሪሊየን ብር በመሰብሰብ ከአጠቃላይ ጥቅል ሀገራዊ ምርት ወይም ጂ ዲ ፒ ዘጠኝ በመቶ ድርሻ የሚይዝ ገቢ እንዲኖረን እየሰራን ነው ሲሉ አክለዋል። ኢትዮጵያ እስከ አሁን የምትሰበስበው ገቢ ከአጠቃላይ ጥቅል ሀገራዊ ምርት ወይም ጂ ዲ ፒ ድርሻው ሰባት በመቶ እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒ
Feb 31 min read


በዚህ ዓመት ባንኮች ከሰጡት ብድር 90 በመቶው ለግሉ ዘርፍ የቀረበ ነው ተባለ፡፡
ጥር 26/2018 በዚህ ዓመት ባንኮች ከሰጡት ብድር 90 በመቶው ለግሉ ዘርፍ የቀረበ ነው ተባለ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ዘንድሮ ባንኮች ያቀረቡት ብድር ከአምናው 123 በመቶ ማደጉን ተናግረዋል፡፡ ብድሩ ከእጥፍ በላይ ከማደጉ ባሻገር ከዚህ ቀደም ለመንግስት የልማት ድርጅቶች በብዛት ይቀርብ የነበረው ብድር ዘንድሮ ግን 90 በመቶው ለግሉ ዘርፍ የተሰጠ ነው ብለዋል፡፡ ባንኮች እርስ በርስ ብር እና ዶላር እንዲገበያዩ መፍቀዱ የገንዘብ አቅርቦት በ10 በመቶ እንዲጨምር ምክንያት መሆኑንም ተጠቅሷል፡፡ ቁጠባም ከአምናው በ44 በመቶ እድገት መሳየቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለእንደራሴዎች በሰጡት ምላሽ ተናግረዋል፡፡ ትዕግስት ዘሪሁን የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ Y
Feb 31 min read


‘’ከጎረቤት ሃገራት አንፃር ኢትዮጵያ ነዳጅ፣ የኤሌትሪክ ሀይል እና ውሃ፤ ለዜጎቿ በርካሸ የምታቀርብ ሀገር ናት’’ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ
ጥር 26/2018 ከጎረቤት ሃገራት አንፃር ኢትዮጵያ ነዳጅ ፣ የኤሌትሪክ ሀይል እና ውሃ ለዜጎቿ በርካሸ የምታቀርብ ሀገር መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ፡፡ የኤሌክትሪክ ሀይል ከኢትዮጵያ አንፃር 500 እጥፍ የሚያስከፍሉ ጎረቤት ሃገራት መኖራቸውን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ንጹህ የመጠጥ ውሃም በርካሽ እያቀረበች መሆኗን ተናግረዋል፡፡ የነዳጅ ዋጋ በየወሩ ለምን ጭማሪ ይደረጋል? በሚል ከምክር ቤት አባላት ጥያቄ ተነስቶ ነበር፡፡ ለዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሰጡት ምላሽ እንደ አሜሪካ ባሉ ባደጉት ሃገራት የነዳጅ ዋጋ ልዩነቶች በየቀኑ በየማዲያው ይጠለፋል ብለዋል፡፡ ነዳጅ በኢትዮጵያ የሚሸጥበት ዋጋ አሁንም ከጎረቤት ሃገራት አንፃር ዝቅተኛ ነው ፤ ሲስተሙ ለዛ ስለማይመች አጭበርባሪዎችን ግን በልኩ ገና መቆጣጠር አልተቻለም ብለዋ
Feb 31 min read


‘’በየቦታው ላለው መሬትና ለሚዘራው ሰብል የሚስማማ ማዳበርያ ለማቅረብ የሚያስችል ጥናት እየተደረገ ነው’’
ጥር 26/2018 ኢትዮጵያ ውስጥ በየቦታው ላለው መሬትና ለሚዘራው ሰብል የሚስማማ ማዳበርያ ለማቅረብ የሚያስችል ጥናት እየተደረገ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተካሄደበት ወቅት ነው፡፡ ከዚህ ቀደም ለሁሉም ሰብል ዓይነትና መሬት ይቀርብ የነበረው ማዳበሪያ ተመሳሳይ ነበር ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ይህን ለመቀየር መንግስት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡ ጥናቱ ሲጠናቀቅና ወደ ስራ ሲገባ አሁን ያለው ምርት በእጥፍ እንደሚያድግም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለምክር ቤት አባላቱ ተናግረዋል፡፡ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https:/
Feb 31 min read


‘’ኢትዮጵያ ለህዳሴ ግድቡ ግንባታ፤ አንድም ብር እርዳታ፣ አንድም ብር ብድር አልወሰደችም’’ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተናገሩ።
ጥር 26/2018 ‘’ኢትዮጵያ ለህዳሴ ግድቡ ግንባታ፤ አንድም ብር እርዳታ፣ አንድም ብር ብድር አልወሰደችም’’ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ዛሬ በፓርላማ ቀርበው እንደራሴዎች ባለፉት 6 ወራት የተከናወኑ የመንግስት ስራዎችን አሰመልክተው ላነሷቸው ጥያቄዎች ምላሽ በሰጡበት ወቅት ነው። ግድቡን አንድ ብር እርዳታ ካለ አንድ ብር ብድር ያሳካ መንግስት እና ህዝብ ፕሮጀክት አይሰራም ማለት አይቻልም ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ። በጀግኖች ኢትዮጵያውያን ቁርጠኛ አቋም በአገር ውስጥም ከአገር ውጭም ያሉ ጨክነው ስለሰሩ የተጠናቀቀ ፕሮጀክት ነው ብለዋል ዐቢይ። 357 የምክር ቤት አባላት በተገኙበት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 10 መደበኛ ስብሰባውን ዛሬ በማካሄድ ላይ ነው። የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግ
Feb 31 min read


41 ፓርቲዎች በምርጫ ለመወዳደር እጩዎቻቸውን እያስመዘገቡ መሆኑ ተነግሯል፡፡
ጥር 26/2018 ዘንድሮ ይደረጋል ተብሎ በሚጠበቀው ሀገራዊ ምርጫ ተሳታፊ ይሆናሉ ተብለው ከሚጠበቁ 54 ፓርቲዎች ውስጥ 41ዱ እጩዎቻቸውን እያስመዘገቡ መሆኑ ተነግሯል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. የኔነህ ሲሳይ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx X :- https://x.com/shegerfm?s=2 LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i Tiktok : https://shorturl.at
Feb 31 min read


እስካሁን የተካሄደው ከ 1.4 ቢሊየን ዶላር በላይ ለባንኮች የቀረበበት የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ግቡን መቶ ይሆን?
ጥር 25/2018 ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ አስተዳደር ፖሊሲ ለውጥ ካደረገ በኋላ የሚያካሂዳቸው የውጭ ምንዛሬ ጨረታዎች ገበያውን የማረጋጋት የብርን የመግዛት አቅምም ይበልጥ እንዳይዳከም የማድረግ ዓላማ እንዳላቸው ይነገራል። የጥቁር ገበያውን ማዳከምም ሌላኛው ግቡ ነው፡፡ እስካሁን የተካሄደው ከ 1.4 ቢሊየን ዶላር በላይ ለባንኮች የቀረበበት የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ግቡን መቶ ይሆን? ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ያሬድ እንዳሻው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/
Feb 21 min read


የመሬት አጠቃቀም ፖሊሲ አለመኖሩና በሚኒስትር ደረጀ መሬትን የሚያስተዳድር ራሱን የቻለ ተቋም አለመኖሩ ኢትዮጵያን ብዙ እንዳሳጣት ይነገራል፡፡
ጥር 25/2018 የመሬት አጠቃቀም ፖሊሲ አለመኖሩና በሚኒስትር ደረጀ መሬትን የሚያስተዳድር ራሱን የቻለ ተቋም አለመኖሩ ኢትዮጵያን ብዙ እንዳሳጣት ይነገራል፡፡ ለምርት የሚሆን ለም መሬት ለመንገድና ለኢንዱስትሪ መገንቢያ እየሆነ ፈር የለቀቀ ስራ የሚከወነውም በዚህ ምክንያት ነው ይላሉ የዘርፉ ተመራማሪዎች ፡፡ ስለመፍትሔውም ጠይቀናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ምህረት ስዩም የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://sho
Feb 21 min read


በኢትዮጵያ ከ30 እስከ 40 በመቶ የሚሆን የሰብል ምርት በማከማቻ ችግር ምክንያት እንደሚባክን ይነገራል።
ጥር 25/2018 በኢትዮጵያ ከ30 እስከ 40 በመቶ የሚሆን የሰብል ምርት በማከማቻ ችግር ምክንያት እንደሚባክን ይነገራል። መረጃዎች እንደሚያሳዩት ኢትዮጵያ አሁን ላይ ያላት የሰብል ማከማቻ 4 ነጥብ 8 ሚሊየን ቶን መያዝ የሚችል ነው። 78 በመቶው ዘመናዊ ማከማቻ ነው የተባለ ሲሆን ቀሪው እንደ ቆርቆሮ ባሉ ቁሳቁሶች የተገነባ እንደሆነ ተጠቅሷል። ችግሩ የኢትዮጵያ የሠብል ምርት በአለም አቀፍ ገበያ ባለው ተወዳዳሪነት ላይም ተፅዕኖ እያሳደረ እንደሚገኝ ይነሳል። ወደፊት ደግሞ ምርቱ እየጨመረ መሄዱ ስለማይቀር ለማከማቸት ስለሚያስፈልገው መጋዘን ከወዲሁ ማሰብ ይገባል የሚሉ ብዙ ናቸው። በረጅም ጊዜ ብክነቱ ከአምስት በመቶ በታች እንዲሆን የሚያስችል ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ መሆን እንደጀመረ በመንግስት በኩል ተነግሯል። ችግሩ በዜጎ
Feb 22 min read


የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክን የኃይል አቅርቦት ሳይቆራረጥ እንዲያገኝ የሚያስችል የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ዝርጋታ መስራቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ፡፡
ጥር 25/2018 የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክን የኃይል አቅርቦት ሳይቆራረጥ እንዲያገኝ የሚያስችል የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ዝርጋታ መስራቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ፡፡ የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከዚህ በፊት የራሱ ብቸኛ መስመር ስላልነበረው የኃይል መቆራረጥና መዋዠቅ ያጋጥመው ነበር ተብሏል፡፡ አሁን ላይ ከአዳማ ቁጥር 3 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በቀጥታ አራት ባለ 33 ኪሎ ቮልት መካከለኛ መስመሮች ለፓርኩ መዘርጋቱን አገልግሎቱ አስረድቷል፡፡ ማከፋፋያ ጣቢያው 40 ሜጋ ዋት ኃይል ለፓርኩ በቀጥታ ማቅረብ የሚያስችል ዓቅም ያለው ሲሆን፤ አምራች ኢንዱስትሪዎቹ አሁን የሚጠቀሙትን የኃይል መጠን ያሳድገዋልም ተብሏል፡፡ አሁን ላይ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ እያደገ እና ኢንዱስትሪዎች እየሰፉ መሄዳቸውን ተከትሎ ዘላቂ እና ከፍተኛ ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ
Feb 21 min read


የገልፍ ሃገራትን ዘንግቶ የቆየው የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ መንገድ እንደ ሃገር ምን አሳጣን?
ጥር 25/2018 #ጉዳያችን በዙሪያዋ ያሉ የገልፍ ሃገራትን ዘንግቶ የቆየው የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ መንገድ እንደ ሃገር ምን አሳጣን? በቱሪዝም፣ በንግድና ኢንቨስትመንት ኢትዮጵያ በዙሪያዋ ካሉ የገልፍ ሃገራት ምን መጠቀም ትችላለች? የታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር አደም ካሚል በጉዳዩ ላይ የሰጡንን ማብራሪያ ለማድመጥ…. ቴዎድሮስ ወርቁ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx X :- https://x.co
Feb 21 min read


በሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ርቀው ቆይተዋል፡፡
ጥር 25/2018 በሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ርቀው ቆይተዋል፡፡ በኢትዮጵያ በሚሊየን የሚቆጠሩ ተማሪዎች ለተከታታይ 3 ዓመታት እና ከዚያ በላይ ለሚሆን ጊዜ ከትምህርት ገበታቸው ላይ አልነበሩም፡፡ በተለይ በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች በነበሩ አሁንም ድረስ በቀጠሉ የሰላም እጦቶች ተማሪዎች ቀያቸውን ለቀው ወጥተዋል፣ ትምህርት ቤቶች በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ወድመዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ልጆች ከእስክርቢቶ እና ደብተር እርቀው ሰንብተዋል፤ በሚሊየን የሚቆጠሩ ተማሪዎችም ከትምህርት ቤት በራፍ ሳይደርሱ ከርመዋል፡፡ ልጆች ከትምህርት ገበታ መራቃቸው ሊያገኙት የሚገባቸውን እውቀት እና ሊያውቋቸው የሚገቡ ነገሮችን ይነፈጋሉ ይህ ደግሞ በተለያየ መንገድ ተፅእኖውን ያበረታዋል ተብሏል፡፡ በሀገር አቀፍም ሆ
Feb 21 min read


ኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ ለደቡብ ሱዳን እና ሶማሊያ የኤሌክትሪክ ሀይል ለማቅረብ ዝግጅት እያደረገች ነው ተባለ፡፡
ጥር 25/2018 ለኬንያ፣ ጅቡቲ እና ታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ሀይል እያቀረበች ያለችው ኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ ለደቡብ ሱዳን እና ሶማሊያ ለማቅረብ ዝግጅት እያደረገች ነው ተባለ፡፡ በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ ያለው የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨት አቅም 9750 ሜጋ ዋት፤እየመነጨ ያለው ደግሞ 9730 ሜጋ ዋት መሆኑ ተነግሯል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ሲናገሩ እንደሰማነው በኢትዮጵያ ከስድስት አመት በፊት የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም በእጥፍ አድጓል። 4 ሺህ ሜጋ ዋት ገደማ የነበረው ከታዳሽ የሀይል ምንጭ የኤሌክትሪክ ሀይል የማመንጨት አቅም አሁን 9750 ሜጋ ዋት መድረሱን ተናግረዋል። በአሁኑ ሰዓት እየመነጨ ካለው ኃይል 9200 ሜጋ ዋቱ ከውሃ፣ 550 ሜጋ ዋት ደግሞ ከንፋስ የሃይል
Feb 21 min read


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባለፉት 6 ወራት ባካሄደው 13 የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ከ1.3 ትሪሊዮን በላይ ብር ከገበያው መሰብሰቡን ተናገረ።
ጥር 25/2018 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባለፉት 6 ወራት ባካሄደው 13 የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ከ1.3 ትሪሊዮን በላይ ብር ከገበያው መሰብሰቡን ተናገረ። ላኪዎች፣ በዶላር ቤት የሚያከራዩ፣ በህጋዊ መንገድ ዶላር የሚያገኙ ሁሉ ያለ ገደብ ዶላራቸውን በባንክ ማስቀመጥና በፈለጉ ጊዜ መጠቀም እንዲችሉ ይደረጋል ተብሏል። ባንኩ ይህን የተናገረው የራሱን እና የተጠሪ ተቋማትን የ6 ወራት የስራ ክንውን ሪፖርት ዛሬ በፓርላማው ቀርቦ ለፕላን ፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሲያቀርብ ነው። ብሔራዊ ባንክ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ከሚሰራቸው ስራዎች ውስጥ አንዱ ዶላርን ለባንኮች በጨረታ እያቀረበ ብርን ከገበያው መሰብሰብ እንደሆነ ተናግሯል፡፡ በፓርላማ ተገኝተው ሪፖርቱን በንባብ ያቀረቡት የብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር
Feb 21 min read


ሰባተኛ ሃገራዊ ምርጫ ሊካሄድ ከ6 ወር ያነሰ ጊዜ ቀርቶታል፡፡
ሰባተኛ ሃገራዊ ምርጫ ሊካሄድ ከ6 ወር ያነሰ ጊዜ ቀርቶታል፡፡ ያለው ዝግጅት ግን የፈዘዘ መሆኑን የሚናገሩ ብዙዎች ናቸው፡፡ ምርጫ ቦርድ በዘረጋው የእጩ ምዝገባ የዲጂታል ሥርዓት ላይም እክሎች መኖራቸውን የፖለቲካ ፓርቲዎች እየተናገሩ ነው፡፡ ምርጫ ቦርድ በዚህ ጉዳይ ምን ይላል? ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. የኔነህ ሲሳይ
Feb 21 min read


በትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ከግጭትና ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ጋር በተያያዘ የንጹሃን ሕይወት አደጋ ላይ መውደቁን ኢሰመኮ ተናገረ።
ጥር 23/2018 በትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ከግጭትና ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ጋር በተያያዘ የንጹሃን ሕይወት አደጋ ላይ መውደቁን ኢሰመኮ ተናገረ። ብሔራዊው የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ተቋም በግጭቱ ተሳታፊ የሆኑ ሁሉም አካላት ችግሩን ከሚያባብሱ ድርጊቶች እንዲቆጠቡ አሳስቧል ። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ከጥር 17 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች አንዳንድ አዋሳኝ አካባቢዎች ከተቀሰቀሰው ግጭት ጋር በተያያዘ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታን እየተከታተለ መሆኑን በመግለጫው ተናግሯል፡፡ በዚህም እስከ ትናንት ለሊት ድረስ በተለይም በጸለምት/ጠለምት፣ በመጋሌ እና አብአላ አካባቢዎች የተከሰቱ ግጭቶችን ተከትሎ የሰዎችን የሕይወት፣ የአካል ደኅንነት፣ ነጻነት እና ንብረት መብቶች ሥጋት ላይ የሚጥሉ
Jan 311 min read


ኤም ኤስ አይ ኢትዮጵያ ፣ፕሮግራሙ በተተገበረባቸው አካባቢዎች ያሉ የሴት ወጣቶችን ከትምህርት የማቋረጥ ምጣኔን እንዲቀንስ አስችሏል ተባለ።
ጥር 22/2018 ኤም ኤስ አይ (MSI) ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት አመታት ሲተገበረው የነበረው የወጣቶች የስነ-ተዋልዶና የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ፣ፕሮግራሙ በተተገበረባቸው አካባቢዎች ያሉ የሴት ወጣቶችን ከትምህርት የማቋረጥ ምጣኔን እንዲቀንስ አስችሏል ተባለ። ድርጅቱ በኦሮሚያ ፣በሲዳማ ፣በደቡብ ምዕራብና በደበቡ ክልሎች በካናዳ መንግስት ድጋፍ ሲተገብረው የነበረው የስነ ተዋልዶና የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ማጠናቀቂያ ፕሮገራም ተካሂዷል። በዚህ ፕሮግራም ከ1,000,000 በላይ ወጣቶች ስለ ስነ-ተዋልዶና የቤተሰብ እቅድ አገልገሎት ግንዛቤ እንደተሰጣቸው እንዲሁም ከ300,000 ሺህ በላይ የሚሆኑት ደግሞ አገልግሎት ያገኙበት መሆኑን የድርጅቱ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር አበበ ሽብሩ (ዶ/ር) ተናግረዋል። ፕሮግራሙ ተግባራዊ በተደረገባቸው አራቱ ክልልሎ
Jan 301 min read


ኢትዮጵያ ከዩሮ ቦንድ አበዳሪዎች ጋር በመርህ ደረጃ ስምምነት ላይ ደርሳበት የነበረው የብድር ሽግሽግ ሳይሳካ ቀረ፡፡
ጥር 22/2018 ኢትዮጵያ ከዩሮ ቦንድ አበዳሪዎች ጋር በመርህ ደረጃ ስምምነት ላይ ደርሳበት የነበረው የብድር ሽግሽግ ሳይሳካ ቀረ፡፡ የብድር ሽግሽጉን በተመለከተ ኢትዮጵያ አለም አቀፍ ጠበቃ ቀጥራ ከዩሮ ቦንድ አበዳሪዎች ጋር ንግግር ስታደርግ መቆየቷ ይታወሳል፡፡ ከሳምንታት በፊትም በመርህ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንም አሳውቀው ነበር፡፡ ይሁንና ስምምነታቸው ስራ ላይ ይውል ዘንድ የአለም አቀፉን የገንዘብ ድርጅት IMF እና የቡድን 20 ሃገራት የአበዳሪዎች ኮሚቴ ይሁንታ ሲጠበቅ ቆይቷል፡፡ ታዲያ የቡድን 20 ሃገራት የአበዳሪዎች ኮሚቴ እንዳለው ኢትዮጵያ ከወጭ ንግድ የምታገኘው ገቢ IMF ከተነበየው በላይ ከሆነ ከምታገኘው ገቢ 2 ነጥብ 75 በመቶ ለዩሮ ቦንድ አበዳሪዎች በተጨማሪነት እንድትከፍል የሚጠይቀው የስምምነት አካል ኢትዮጵያ ብትስማማበትም
Jan 301 min read


በኢትዮጵያ በሚሊየን የሚቆጠሩ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ላይ የሉም፡፡
ጥር 22/2018 በኢትዮጵያ በሚሊየን የሚቆጠሩ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ላይ የሉም፡፡ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በተፈጠረ ተፈጥሮአዊ እና ሰው ሰራሽ ችግሮች ምክንያት ወደ ትምህርት ቤት መሄድ ያለባቸው ተማሪዎች ሳይሄዱ ቀርተዋል፡፡ ባለፉት አመታት በነበረ አሁንም ድረስ በአንዳንድ አካባቢዎች በቀጠለ የሰላም እጦት ትምህርት ቤቶች በሙሉም ሆነ በከፊል ተጎድተዋል፤ ሰዎች ሰላምን ፍለጋ ቀያቸውን ለቀው ወጥተዋል፡፡ በነዚህ እና በሌሎች ምክንያች ልጆች ከትምህርት ገበታቸው እርቀዋል፡፡ እንደማሳያም የሰላም እጦት ከነበሩባቸው እና አሁንም ድረስ ችግሩ ከቀጠሉባቸው አካባቢዎች መካከል የሆነው አማራ ክልል የ2018 የትምህርት ዘመን ከጀመረ ወራት ማስቆጠሩ ቢታወቅም እመዘግባለው ብሎ ካቀደው ተማሪ 3 ሚሊየኑን እንዳላገኘ ተናግሯል፡፡ በኢት
Jan 301 min read


የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸው መድሃኒቶችን ሲሸጡ የተገኙ 44 የመድሃኒት መደብሮች ተቀጡ፡፡
ጥር 22/2018 የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸው መድሃኒቶችን ሲሸጡ የተገኙ 44 የመድሃኒት መደብሮች ተቀጡ፡፡ በመደሮቹ ላይ እስከ እገዳ የደረሰ እርምጃ መውሰዱን የአዲስ አበባ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን ተናግሯል፡፡ ባለስልጣኑ በመንፈቅ ጊዜ ውስጥ በመድሃኒት መሸጫ መደብሮች ከወንኩት ባለው የቁጥጥር ስራ 1275 ኪሎ ግራም የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸው መድሃኒቶች ማግኘቱንና ግምታዊ ዋጋቸውም 5.5 ሚሊዮን ብር መሆኑን የነገሩን በባለስልጣኑ የጤና ተቋማትና ባለሙያዎች ቁጥጥር ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ገልገሎ ኦልጅራ ናቸው፡፡ መድሃኒቶቹ መወገዳቸውን የተናገሩት ሃላፊው ይህንን ጊዜው ያለፈበት መድሃኒት ይዘው የተገኙ 44 የመድሃኒት ችርቻሮ መደብሮችና 2 የባህል ህክምና ባለሙያዎች ላይ ከከባድ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የሙያ ፍቃድን የማገድ እርምጃ
Jan 301 min read


ኢትዮጵያ ኬንያና ሶማሊያ በዳዋ ወንዝ ተፋሰስ ዙሪያ መምከራቸው ተሰማ፡፡
ጥር 22/2018 ድንበር ተሻጋሪ ወንዞችን በጋራ ለመጠቀም እና በድርቅ ወቅት የሚከሰቱ ችግርን ለመከላከል ይረዳል በሚል ኢትዮጵያ ኬንያና ሶማሊያ በዳዋ ወንዝ ተፋሰስ ዙሪያ መምከራቸው ተሰማ፡፡ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት ኢጋድ እንዳለው የማንዴላ ትሪያንግል በሚል ኢትዮጵያ ፣ ኬኒያ እና ሶማሊያ በሚገኙት መስመር ድርቅ ሲያጋጥም ድንበር ተሻጋሪ ወንዞችን በጋራ መጠቀም በሚያስችል ነጥብ ዙሪያ ውይይት መደረጉን ነው፡፡ የዳዋ ወንዝን ተፋሰስ በመከተል በሀገራቱ ውስጥ የልማት ስራዎችን በጋራ ለመስራት ያለመው የሚኒስትሮች ጉባኤ በኬኒያ ውይይት ማድረጋቸው ተሰምቷል፡፡ የዳዋ ወንዝ በድንበር አካባቢ ከ3 ሚሊዮን የሚበልጡ ሰዎችን በድርቅ ወቅት ተፋሰሱ ማገዝ ስለሚችል በወንዙ ላይ ግድቡ በመገንባት ከ2 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር በላይ
Jan 301 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

