top of page


ከተመን በላይ የትራንስፖርት ታሪፍ ይጨምራል፤ የሸቀጦች ዋጋም በትናንትናው ልክ ዛሬ አይገኝም።
ግንቦት 11/2018 በየጊዜው መንግስት ታሪፍ ያወጣላቸው ሸቀጦች በነጋዴዎች ፍላጎት ብቻ ዋጋቸው ይጨምራል፡፡ አንዳንዶችም እየደበቁት በከፍተኛ ዋጋ ይሸጣሉ፡፡ ከተመን በላይ የትራንስፖርት ታሪፍ ይጨምራል፤ የሸቀጦች ዋጋም በትናንትናው ልክ ዛሬ አይገኝም። ጭማሪው ምጣኔ ሐብታዊ ምክንያት የለውም፡፡ ሸማቹም ለምን ብሎ የመጠየቅ ልምድ የለውም፡፡ "ለምን" ብለው የሚጠይቁ ሲኖሩም ጭማሪውን አሜን ብለው የተቀበሉ ተደርበው ሲያዋክቡ ይታያሉ፡፡ ለነጋዴዎቹ ህገወጥነት ፍላጎት የሸማቹ ዝምታ እና የተባለውን "አሜን" ብሎ መቀበል በገበያው ላይ ምን አይነት ተፅዕኖ አለው? ስንል የጠየቅናቸዉ የምጣኔ ሀብት ባለሞያዉ ቆስጠንጢኖስ በርኸ (ዶ/ር) "በኢኮኖሚክስ ህግ ሸማቹ የገበያው ንጉስ ነው። ነገር ግን ሸማቹ 'ለምን?' ብሎ ካልጠየቀና ያለአግባብ የሚደረጉ ጭማሪዎችን በ
May 191 min read


ምግብ፣ ጤና እና አመጋገብ
ግንቦት 10/2018 #ጉዳያችን - ምግብ፣ ጤና እና አመጋገብ በዓለም አቀፉ የምግብ ምርምር ፖሊሲ ኢንስቲትዩት ተመራማሪ ሳይንቲስት የሆኑት ዶክተር ታደሰ ዘርፉ በጉዳዩ ላይ የሰጡንን ማብራሪያ ለማድመጥ…. ቴዎድሮስ ወርቁ
May 181 min read


‘’በሌሎች ሀገራት የተውሶ ዳታ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ አንችልም’’ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ
ግንቦት 10/2018 ‘’በሌሎች ሀገራት የተውሶ ዳታ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ አንችልም’’ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ። ጠ/ሚ ዐቢይ በስታትስቲክስ የዳታ ትንተና ታግዘን ያለንን አቅም ካላወቅን ለማቀድ፣ ለመስራት፣ ለመሸጥና ለመግዛትም አስቸጋሪ ይሆናል ብለዋል። ለዚህም የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት የዳታ ሉዓላዊነትን ለማስጠበቅ እየሰራ ያለውን ሥራ ቀለል አንድርገን የምናየው አይደለም ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ይህንን ያሉት የፕላንና ልማት ሚንስትር ከኢትዮጵያ ስታስትስቲክ አገልግሎት ጋር በመሆን "የዳታ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነፃነት" በሚል መሪ ቃል ባዘጋጁት የብሔራዊ ጉባኤ እና ኤግዚቢሽን የመክፈቻ መድረክ ላይ ነው። የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት በዚህ ዓመት ከ80,000 በላይ ዳታ ሰብሳቢ ሰራተኞችን ወደ 19,600
May 181 min read


በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 9 ወራት 83,000 ህፃናት ተወልደዋል፡፡
ግንቦት 10/2018 በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 9 ወራት 83,000 ህፃናት ተወልደዋል፡፡ ከሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ያገኘነው መረጃ እንደሚያሳየው ዘግይተው የተመዘገቡትን ጨምሮ በአጠቃላይ ከ324 ሺህ በላይ ህፃናት ተወልደዋል ብሏል፡፡ በሌላ በኩል ኤጀንሲው በተጠቀሰው ጊዜ በከተማዋ ከ5,000 በላይ ሰዎች መሞታቸውን መዝግቤአለው ሲል ነግሮናል፡፡ የሲቪል ምዝገባና የኗሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ምዝገባዎቹን ሲያደርግ በወቅቱ በዘገየ፣ እንዲሁም የጊዜ ገደቡ ያለፈበት፣ እያለ እንደሚመዘግብ ነግሮናል፡፡ በዚህም እነዚህ 83,000 ህፃናት በተወለዱ በሰላሳ ቀን ውስጥ የተመዘገቡ እንደሆኑ እና በወቅቱ የተመዘገቡ መሆናቸውንም ኤጀንሲው አስረድቷል፡፡ ሆኖም በአጠቃላይ በ9 ወር ውስጥ ወቅቱን ጠብቀው ከተመዘገቡት ሌላ በዘገየ እና የጊዜ ገደቡ ያ
May 181 min read


የነዳጅ እጥረት እንዲፈጠር በማድረግና በከባድ ሙስና የተጠረጠሩ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ።
ግንቦት 10/2018 የነዳጅ እጥረት እንዲፈጠር በማድረግና በከባድ ሙስና የተጠረጠሩ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ። የፌደራል ፖሊስ አፋልጉኝ ብሎ ማስታወቂያ ያወጣባቸውን 4 ተጠርጣሪዎች ፖሊስ ይዞ እንዲያቀርብ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል። የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት መዝገቡን ተቀብሎ ማየት የጀመረ ሲሆን፤ በዐቃቤ ህግ ክስ ላይ እንደተመላከተው ባለስልጣናቱ የፍቃድ አሰጣጥ መመሪያን በመጣስ ከተከሳሽ ወ/ሮ በረከት ወርቁ ጋር በመመሳጠር 466 ሺህ ሊትር ነጭ ናፍጣ ያለምንም ህጋዊ አሰራር እንድታገኝ አድርገዋል። የእነዚህ ባለስልጣናት እና የግለሰቧ ህገ-ወጥ ድርጊት በመንግስት ሀብት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ከማድረሱም በላይ በገበያው ላይ ለታየው የነዳጅ እጥረት ዋነኛ ምክንያት መሆኑን ክሱ
May 181 min read


ኢዜማ በተለያየ አካባቢ በማደርገው ዝግጅት ችግር እየገጠመኝ ነው ብሏል፡፡
ግንቦት 10/2018 ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫን ለማካሄድ ከሶስት ሳምንት ያነሰ ጊዜ ቀርቶታል፡፡ ፓርቲዎችም የምርጡኝ ቅስቅሳ እያደረጉ ነው፡፡ በሌላ በኩል በተለያየ አካባቢ ለምርጫ ቅስቀሳ ስንቀሳቀስ ችግር እየገጠመን ነው የሚሉ ፓርቲዎችም ቅሬታቸውን ሲያቀርቡ ይሰማል፡፡ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በሰጠው መግለጫም በተለያየ አካባቢ በማደርገው ዝግጅት ችግር እየገጠመኝ ነው ብሏል፡፡ ዘገባውን ለማድመጥ…. ያሬድ እንዳሻው
May 181 min read


በአብዛኞቹ አካባቢዎች ላይ ምርጫ ለማድረግ አስቻይ የፀጥታ ሁኔታ መኖሩን በቀረቡ ሪፖርቶች ተረጋግጧል ሲል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተናገረ፡፡
ግንቦት 10/2018 በአብዛኛዎቹ አካባቢዎች ላይ ምርጫ ለማድረግ አስቻይ የፀጥታ ሁኔታ መኖሩን በቀረቡ ሪፖርቶች ተረጋግጧል ሲል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተናገረ፡፡ አሁንም ግን ትኩረት የሚሹ ቦታዎች መኖራቸው ተጠቅሷል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ሥምሪት የሰጣቸው የክትትል ቡድኖች 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድባቸውን አካባቢዎች የፀጥታ ሁኔታን በተመለከተ ዝርዝር ሪፖትርት ማቅረባቸውን ባወጣው መግለጫ አስረድቷል፡፡ በአካባቢዎቹ ላይ ያለውን ተጨባጭ የፀጥታ ሁኔታና የፖለቲካ ምኅዳር ክትትል አድርጎ ሪፖርት የሚያቀርብ ቡድን ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እንዲሁም ከቦርዱ የተውጣጣ የክትትል ቡድን አዋቅሮ ሥምሪት መስጠቱን ቦርዱ አስታውሷል፡፡ የሥምሪት ቡድኑም ክትትል ሲያደርግ ቆይቶ ሪፖርቱን ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ
May 181 min read


በመጪው የክረምት ወቅት ዋነኛ የዝናብ ወቅታቸዉ በሆኑት አንዳንድ አካባበቢዎች ላይ የዝናብ እጥረት ሊከሰት እንደሚችል ተተነበየ።
ግንቦት 7/2018 በመጪው የክረምት ወቅት ዋነኛ የዝናብ ወቅታቸዉ በሆኑት አንዳንድ አካባበቢዎች ላይ የዝናብ እጥረት ሊከሰት እንደሚችል ተተነበየ። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት በበልግ ወቅት የነበረውን የአየር ጠባይ ገምግሞ በመጪው የክረምት ወቅት የሚጠበቀውን የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ ዛሬ ይፋ አድርጓል። በትንበያው መሰረትም በደቡብና ምስራቅ ትግራይ፤ ሰሜንና ደቡብ ወሎ ዞኖች፤ የአፋር ክልል ዞኖች እና ምስራቅ የሀገራችን አከባቢዎች መደበኛና ከመደበኛ በታች ዝናብ ያገኛሉ ተብሏል። የመካከለኛውና ምዕራብ ትግራይ ዞኖች እና ምዕራብ አማራ ዞኖች በብዙ ቦታዎቻው ላይ መደበኛና በጥቂት ስፍራዎቻቸው ላይ ከመደበኛ በታች እንደሚያገኙም ተጠቁሟል። የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዞኖች፤ ምዕራብ ኦሮሚያ ዞኖች፤ የጋምቤላ ክልል ዞኖች እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ
May 151 min read


ሊጠናቀቅ ጥቂት ጊዜያት በቀሩትና በመንግስት ወጥቶ ላለፉት 2 ዓመት ሲተገበር ከቆየው የኪራይ ውል ወጪ በአዲስ አበባ በቤቶች ላይ ከፍትኛ የዋጋ ጭማሪ እየተደረገ መሆኑ ተነገረ፡፡
ግንቦት 7/2018 ሊጠናቀቅ ጥቂት ጊዜያት በቀሩትና በመንግስት ወጥቶ ላለፉት 2 ዓመት ሲተገበር ከቆየው የኪራይ ውል ወጪ በአዲስ አበባ በቤቶች ላይ ከፍትኛ የዋጋ ጭማሪ እየተደረገ መሆኑ ተነገረ፡፡ በኢትዮጵያ እየታየ ያለው የዋጋ ግሽበት እና የኑሮ ውድነት በህብረተሰቡ ላይ እያሳደረ ያለውን ጫናና በመሰረታዊ ሸቀጦች ላይ በየቀኑ ሰማይ እየነካ የሄደው የዋጋ ንረት የሸማቹን የመግዛት አቅም በእጅጉ አዳክሞታል፤ ለዚህም መፍትሄ ሊሰጠው ይገባል ሲል የኢትዮጵያ ሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት ተናግሯል። በተለይም ባለፉት 2 ዓመታት የነበሩ የኪራይ ውሎች መጠናቀቅን ተከትሎ ከ50 እስከ 100 በመቶ የሚደርስ የኪራይ ጭማሪ በተከራዮች እየተደረገ ነው ይህንንም አረጋግጫለሁ ብሏል ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ፡፡ የሸማቹ የመግዛት አቅም መዳከም ደግሞ አጠቃላይ ሀገራዊ ኢኮ
May 152 min read


የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ባለፉት ዘጠኝ ወራት 3,600 የውጪ ሃገር ዜጎች በሀሰት የኢትዮጵያ ፓስፖርት ለመያዝ ሲንቀሳቀሱ ደርሼባቸዋለሁ ብሏል።
ግንቦት 6/2018 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ባለፉት ዘጠኝ ወራት 3,600 የውጪ ሃገር ዜጎች በሀሰት የኢትዮጵያ ፓስፖርት ለመያዝ ሲንቀሳቀሱ ደርሼባቸዋለሁ ብሏል። አገልግሎቱ ከ10 ሺህ በላይ ሰዎች ሀሰተኛ የልደት ሰርተፍኬት፣ መታወቂያ እና ፋይዳ በመያዝ ህጋዊ አገልግሎት ለማግኘት ሲሉ እንደተደረሰባቸው ተናግሯል። በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የፓስፖርት አገልግሎት ዳሬክተር የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ብርሃኑ ከድንበር አከባቢ የሚመጡ ኢትዮጵያውያን ከውጪ ሃገር ከሚመጡ ዜጎች ጋር የሚመሳሰል ማንነት ስላላቸው የውጪ ዜጎች ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ሃሰተኛ ሰነድ ለመያዝ ሙከራ እንደሚያደርጉ አስረድተዋል። አቶ ሙሉጌታ ረጅም ዓመታትን በኢትዮጵያ የኖሩ ኤርትራዊያን የኢትዮጵያ ዜግነት ሊያገኙ የሚችሉበትን ሁኔታም አስረድተዋል። በሪፈረንደሙ ወቅት ያልመረ
May 141 min read


ከእፅ መጠቀም፣ ከቁማር የተነሳ ለአእምሮ ህመም ተጋላጭ የሚሆኑ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ነው፡፡
ግንቦት 6/2018 ከእፅ መጠቀም፣ ከቁማር የተነሳ ለአእምሮ ህመም ተጋላጭ የሚሆኑ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ነው፡፡ በኢትዮጵያም በተቀረው ዓለምም ከጭንቀት፣ ድብርትና ሌሎችም ጉዳዮች ጋር በተገናኘ የሚከሰቱት የአእምሮ መታወኮች አሁንም ከአጠቃላዩ ችግር ድርሻው ከፍተኛ ነው። በሌላ በኩል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በኢትዮጵያ ለአዕምሮ ጤና መታወክ ምክንያት የሆኑ አዳዲስ ልማዶች እየታዩ ነው ይላሉ በየካ ኮተቤና በዶክተር ዳዊት ኦፊስ ፕራክቲስ ውስጥ የአዕምሮ ሀኪም የሆኑት ዳዊት አሰፋ(ዶ/ር)። እነዚህ በፊት የምዕራባዊያን ይባሉ የነበሩ አሁን አሁን በኢትዮጵያም መታየት ከጀመሩ ችግሮች ውስጥ አንዱ ከሰውነት አቋምና አመጋገብ ጋር የተገናኘ ነው ብለዋል። ብዙ ሰዎች ሰውነቴ ጨምሯል መክሳት አለብኝ፤ ምግብ አብዝቻለው መቀነስ ይኖርብኛል በሚል ጭንቀትና ስለራሳቸው ባ
May 141 min read


ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሁሉም ወገን ለኢትዮጵውያን ዘላቂ ሰላምንና መረጋጋትን የሚያስገኝ ሆኖ እንዲፈጸም የኢትዮጵ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አሳሰበ፡፡
ግንቦት 6/2018 ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሁሉም ወገን ለኢትዮጵውያን ዘላቂ ሰላምንና መረጋጋትን የሚያስገኝ ሆኖ እንዲፈጸም የኢትዮጵ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አሳሰበ፡፡ በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን ውስጥ በምዕመናን ላይ እየደረሰ ያለውን ችግር ከመንግስት ጋር በመነጋገር እንዲፈቱ፣ ሕዝቡን እንዲያጽናኑ፣ ሀገረ ስብከቱንም በሊቀ ጵጵስና በቋሚነት እንዲመሩ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ በቅዱስ ሲኖዶስ ተመድበዋል፡፡ በዓመት ሁለት ጊዜ የሚካሄደው የቅዱስ ሲኖዶስ የርክበ ካህናት ምልዓተ ንጉባኤ በዛሬው እለት ተጠናቋል፡፡ ላለፉት ቀናት ምክክር እያደረገ የነበረው ቅዱስ ሲኖዶስ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ማሳለፉን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆርዮስ በሰጡት መግለጫ አስረድተዋል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውሳኔ ካሳለፈባቸው
May 142 min read


በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ታድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና የልብስ ቁራጮች እንዲሁም የወርቅ አምባር ቅርሶች ከ158 ዓመታት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል፡፡
ግንቦት 6/2018 በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ታድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና የልብስ ቁራጮች እንዲሁም የወርቅ አምባር ቅርሶች ከ158 ዓመታት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል፡፡ ቅርሶቹ የተመለሱት ከእንግልዝ ሀገር ሲሆን ቅርሶቹን ያመጡት ሮቢን ጃክሴን (ዶ/ር) የእንግልዝ የንግስቲቱ ቤተሰብ ሙዚየም ኃላፊና አሉላ ፓንክረስት (ዶ/ር ) የኢትዮጵያ ቅርስ አስመላሽ ኮሚቴ አባልና ተመራማሪ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው እና የኢትዮጵያ አርበኞች ማህበር አባላት ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በመገኘት ለቅርሶቹ ደማቅ አቀባበል አድርገዋል፡፡ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው ታሪካዊ የሆኑ ቅርሶች በተለያዩ ምክንያቶች ከሀገር ውጭ የወጡትን ወደ ኢትዮጵያ የመመለስ ስራ በትልቅ ትኩረት እየተሰራ
May 141 min read


‘’በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩና በመንግስት ወደ ሀገራቸው ከተመለሱ በኋላ በድጋሜ በህገወጥ መንገድ ከሀገር የሚወጡ ሰዎች አሉ‘’
ግንቦት 6/2018 በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ኢትዮጵያዊያን በመንግስት ወደ ሀገራቸው ከተመለሱ በኋላ በድጋሜ በህገወጥ መንገድ ከሀገር የሚወጡ ሰዎች መኖራቸውን የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ። ይህንን ችግርም ለመፍታት ህገወጥ ደላሎች ላይ እየተሰራ መሆኑን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተናግሯል። ከስደት ተመላሾቹ ወደ ሀገራቸው ሲመጡ በማቋቋሚያ ሂደቱ ላይ የሚጠብቁትን ያህል ባለማግኘታቸው እና የነበሩበት ቦታ የተሻለ ገቢ ስለሚኖራቸው ተመልሰው ወደ መጡበት ሀገር በህገወጥ መንገድ መሄድን ይመርጣሉ ተብሏል። ብዙ የሚባሉ ሰዎች ባይሆኑም ወደ ሀገር ቤት ከመጡ በኋላ ግን በድጋሜ በህገወጥ መንገድ ከሀገር የሚወጡ መኖራቸውን ያነሳው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ይህንን ለማስተካከልም ህገወጥ ደላሎች ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ብሏል። በሌላ በኩል በተያዘው
May 141 min read


''የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ኅብረት ለምርጫ’’ በመራጮች ምዝገባ ሂደት ወቅት ታይተዋል ያላቸውን ህጸፆች ይፋ አደረገ።
ግንቦት 5/2018 በሰባተኛው ምርጫ ዙሪያ እየሰሩ ካሉ ጥምረቶች አንዱ የሆነው፤ ‘’የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ኅብረት ለምርጫ’’ በመራጮች ምዝገባ ሂደት ወቅት ታይተዋል ያላቸውን ህጸፆች ይፋ አደረገ። ማንነትን የሚያረጋግጡ ሰነዶችን ሳያሟሉ በመራጭነት መመዝገብና በተከለከሉ ቦታዎች የምርጫ ጣቢያዎችን ማቋቋም ጥምረቱ ታይተዋል ካላቸው እንከኖች መካከል ናቸው። በጥቂት የምዝገባ ጣቢያዎች ውስጥ እና አካባቢ በታጠቁ ኃይሎች በተመዝጋቢዎች፣ በአስፈጻሚዎችና በታዛቢዎች ላይ ጥቃት፣ ማስፈራራትና ወከባ እንተፈጸመም ጠቅሷል። በምርጫ እና ምርጫ ነክ ጉዳዮች ዙሪያ የሚሰራው የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ኅብረት ለምርጫ፤ 2011 ላይ ነው የተመሰረተው። ከ180 በላይ አባሉት እንዳሉትም ከጥምረቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ አበራ ሃይለማሪያም ሠምተናል። ከቀና
May 132 min read


በመካከለኛው መስራቅ ጦርነት ምክንያት የሆርሙዝ ወሽመጥ በመዘጋቱ የቅባት እህሎች የማጓጓዣ ዋጋ ከሶስት እጥፍ በላይ መጨመሩ ተነገረ፡፡
ግንቦት 5/2018 በመካከለኛው መስራቅ ጦርነት ምክንያት የሆርሙዝ ወሽመጥ በመዘጋቱ የቅባት እህሎች የማጓጓዣ ዋጋ ከሶስት እጥፍ በላይ መጨመሩ ተነገረ፡፡ ይህን የተናገረው የኢትዮጵያ የጥራጥሬ እና የቅባት እህል ላኪዎች ማህበር ነው፡፡ ማህበሩ በጦርነቱ ምክንያት የጥራጥሬ እና የቅባት እህል ላኪዎች ምርቶቻቸውን በሚፈለገው ደረጃ ወደ ውጭ መላክ እንዳልቻሉ እና በዚህም ምክንያት ትልልቅ ላኪ ድርጅቶች ምርቶቻቸውን ከዝነው መያዛቸውን ተናግሯል፡፡ የኢራኑ ጦርነት አሁንም መፍትሔ ባለማግኘቱ ኢትዮጵያ በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ወደ አውሮፓ እና አሜሪካ የምትልካቸው የቅባት እህሎች ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ መቀጠሉን የማህበሩ ፕሬዚዳንት አቶ ኤዳኦ አብዲ ነግረውናል፡፡ አቶ ኤዳኦ ኢትዮጵያ ነጭ ቦሎቄን፣ ሰሊጥ እና መሰል ምርቶች በሆሩሙዝ ወሽመጥ በኩል ወደ አሜሪ
May 131 min read


ኢትዮጵያ ውስጥ ለሰብል ምርት ከሚያስፈልገው ግብአት ውስጥ ገበሬው የሚቀርብለት ከ35 በመቶ እንደማይበልጥ ተነገረ፡፡
ግንቦት 4/2018 ኢትዮጵያ ውስጥ ለሰብል ምርት ከሚያስፈልገው ግብአት ውስጥ ገበሬው የሚቀርብለት ከ35 በመቶ እንደማይበልጥ ተነገረ፡፡ ይህ የተባለው በሰብል የግብርና ግብአት ላይ ትኩረት ያደረገ ሀገር አቀፍ የሰብል ጥበቃና ማዳበርያ ኤግዚቢሽን ከግንቦት 14 እስከ 16 እንደሚካሄድ ይፋ በተደረገበት መግለጫ ነው፡፡ ለግብርናው ምርታማነት የሚያሰፈልጉ ግብአቶችን በበቂ ሁኔታ መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ ይሁንና በተለያየ ምክንያት ገበሬው ግብአት እየደረሰው እንዳልሆነ ይነገራል፡፡ ለዚህ አንደኛው ምክንያት የገበያ ትስስር ችግር ነው የተባለ ሲሆን የሚሰናዳው ኤግዚቢሽንም ለተጠቀሰው ችግር መፍትሄ ይሆናል ተብሎ ተስፋ ተደርጎበታል፡፡ በኤግዚቢሽኑ ለሰብል ልማት የሚያገለግሉ የአፈር ማዳበርያ ፣ ፀረ ነፍሳት ፣ ፈንገስ ማጥፊያዎች ፣ አረም ማጥፊያ ፣ የግብርና ስራን ለ
May 132 min read


የአዲስ አበባ ስነ ስሪት (የተዋቀረችበት መንገድ) ለከተማ ልማትና ዕድገት አስቸጋሪ አድርጓታል ተብሏል።
ግንቦት 4/2018 የአዲስ አበባ ስነ ስሪት (የተዋቀረችበት መንገድ) ለከተማ ልማትና ዕድገት አስቸጋሪ አድርጓታል ተብሏል። አመሰራረቷም በተጠና የከተማ ፕላን ሳይሆን በልማዳዊ ሰፈራ መሆኑ ከነገስታቱ ጀምሮ ባለው ስርዓት ውስጥ አዲስ አበባን ለማዘመን ፈተና ሆኖ መቀጠሉም ተነግሯል። ይህ የተነገረው ናሽናል ሚዲያ አክስዮን ማህበር "አዲሲቱ አዲስ" በሚል ርዕስ የአዲስ አበባ ከተማን የማደስና የልማት ሥራዎች፣ በጎ ዕድሎችና ፈተናዎች ላይ ያተኮረ ውይይት በተካሄደበት መድረክ ላይ ነው። በመድረኩ ላይ የዳሰሳ ፅሁፍ ያቀረቡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህሩ ዳዊት በንቲ (ዶ/ር)፤ አዲስ አበባ ከሌሎች የዓለም ከተሞች በዕድሜ ትንሿ መሆኗን አንስተዋል። ከተማዋ የተቆራረጠች እና ለዋና ከተማነት የማትመች ቦታ ላይ ነች ያሉት ዳዊት(ዶ/ር)፤ ይህም በየጊዜው ከተማዋ
May 122 min read


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት 9 ወራት የስነ ምግባር ጥሰት በፈፀሙ 1,139 የአገልግሎቱ ሠራተኞች ላይ የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃዎች መውሰዱን ተናገረ፡፡
ግንቦት 4/2018 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት 9 ወራት የስነ ምግባር ጥሰት በፈፀሙ 1,139 የአገልግሎቱ ሠራተኞች ላይ የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃዎች መውሰዱን ተናገረ፡፡ እርምጃ ከተወሰደባቸው ኃላፊዎችና ሠራተኞች መካከል 16ቱ ከስራቸው ሲሰናበቱ፤ 721ዱ የደመወዝ ቅጣት እንዲሁም 402 የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ናቸው ተብሏል፡፡ አገልግሎቱ በሠራተኞች ላይ ከወሰዳቸው አስተዳደራዊ እርምጃዎች መካከል 103 ሠራተኞች ላይ በደንበኞች የቀረበን ጥቆማ በመመርመር የወሰደው መሆኑንና ቀሪ 1,036ቱ ተቋሙ በራሱ ግኝት አጣርቶ የወሰዳቸው እርምጃዎች መሆናቸውን ተናግሯል፡፡ ባለፉት 9 ወራት አገልግሎቱ በሙስና መጠቆሚያ ዘመናዊ መተግበሪያ እና በሌሎች አማራጮች ከደንበኞቹ የደረሱትን 427 ጥቆማዎችን መርምሮ በ103 ኃላፊዎችና ሠራተኞች ላይ የ
May 121 min read


የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዘገየ አስፋው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
ግንቦት 4/2018 የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዘገየ አስፋው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። አቶ ዘገየ የግብርና ሚኒስቴርን ከ1968–1970 ዓ.ም እና ከ1983 - 1984 ዓ.ም በሚኒስትርነት ማገልገላቸውን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል፡፡ አቶ ዘገየ አስፋው መሬት ለአራሹ አዋጅ እንዲታወጅ ከፍተኛ ድርሻ ነበራቸው፡፡ አቶ ዘገየ አስፋው ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ አለም ተለይተዋል ሲል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተናግሯል፡፡ ከዚህ አለም በሞት እስከተለዩ ድረስም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው እየሰሩ ነበር፡፡ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1
May 121 min read


ባለፉት ዘጠኝ ወራት ለህዳሴ ግድብ 1.2 ቢሊዮን ብር ተሰብሰቧል ተባለ።
ግንቦት 3/2018 ባለፉት 9 ወራት ለህዳሴ ግድብ 1.2 ቢሊዮን ብር ተሰብሰቧል ተባለ። ይሀም ለመሰብሰብ ከታቀደው ውስጥ ከ50 በመቶ በታች ወይም 1.2 ቢሊዮን ብር ብቻ ነው ተብሏል፡፡ ባለፉት 9 ወራት ሀገሪቱ ከኤሌክትሪክ ሀይል ሽያጭ ወደ 366 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷ ታውቋል፡፡ ይህ የተነገረው የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባለፉት 9 ወራት የሰራቸውን ስራዎች ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ባለፈው ሚያዝያ 29/2018 ዓ.ም ባቀረበበት ወቅት ነው፡፡ ጷጉሜ 4/2017 ዓ.ም የግንባታ ስራው ተጠናቅቆ ለተመረቀው ታላቁ ህዳሴ ግድብ 9 ወራት ውስጥ በህዝብ ተሳትፎ፣ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ተሳትፎ በዘጠኝ ወራት ውስጥ 2.58 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ እንደነበር ለምክር ቤቱ የቀረበው ሰነድ ያሳያል፡፡ ይሁንና የእቅዱን 50 በመቶ ገደማ
May 112 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

