ዲጂታል ባንኪንግ ስራን ያቀለለ መሆኑ ቢነገርለትም በሌላ በኩል ለዲጂታል መጭበርበርም እያጋለጠ መሆኑ ይነገራል፡፡
- 56 minutes ago
- 1 min read
ሐምሌ 4/2018
ዲጂታል ባንኪንግ ስራን ያቀለለ መሆኑ ቢነገርለትም በሌላ በኩል ለዲጂታል መጭበርበርም እያጋለጠ መሆኑ ይነገራል፡፡
ከእነዚህም የማታለያ ስልቶች መካከል አንዱ ሃሰተኛ የድጅታል ደረሰኝ ሰርቶ ሻጮችን ማጭበርበር እየተበራከተ መጥቷል።
ስለ ጉዳዩ ያነጋገርናቸው ነጋዴዎች፣ አጭበርባሪዎች ከባንክ ሂሳባቸው ገንዘብ ተቀናሽ ሳያደርጉ ትክክለኛውን የሚመስል ሃሰተኛ ድጅታል ደረሰኝ እያሳዩአቸው ብዙ ገንዘብ እንደተጭበረበሩ ነግረውናል፡፡

አታላዮች ይህንን ሃሰተኛ ድጅታል ደረሰኝ ለመስራት ህገ ወጥ ሶፍትዌሮችን የሚጠቀሙ ሲሆን እነዚህ ሶፍትዌሮች የፈለጉትን የገንዘብ መጠን እና የደንበኛ ስም መፃፍ እንደሚያስችሏቸው ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡
በባንክ ተቋማት ውስጥ የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት እና ስትራቴጂ ባለሙያ የሆኑት አቶ ሃብተማርያም አደረ ባንኮች አሁን በሚከተሉት የዲጅታል ክፍያ አሰራር እንዲህ ዓይነቱን ሀሰተኛ ዲጅታል ደረሰኝ መከላከል አይችሉም ብለውናል።
ታድያ መፍትሔው ምንድነው?
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….
ንጋት መኮንን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7

