top of page


‘’በትግራይ ገበያ የኤርትራ ናቅፋ ለግብይት እየዋለ ነው’’ በሚል ለቀረበው ወቀሳ የትግራይ ክልል ንግድ ቢሮ ምላሽ
ጥር 14 2018 ‘’በትግራይ ገበያ ውስጥ አንድ የኤርትራ ናቅፋ በኢትዮጵያ 8 ብር እየተገዛ ነው ለግብይት አገልግሎትም ውሏል’’ እየተባለ ለቀረበው ወቀሳ የትግራይ ክልል ንግድ ቢሮ "ሌላ እየተደረገ ባለበት ወቅት ይህ ቢኖር አያስገርምም፤ ግን መኖሩን አላረጋገጥንም" የሚል ምላሽ ሰጠ፡፡ የትግራይ ክልል ብዝሃነት እና ህዝቦች ግንኙነት ጽህፈት ቤት በበኩሉ ከኤርትራ ጋር ያለው የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እንጂ የንግድ አይደለም ብሏል፡፡ አዲግራትን ጨምሮ በትግራይ ክልል ለኤርትራ ቅርብ በሆኑ የክልሉ ከተሞች በናቅፋ ግብይት እየተደረገ ነው የሚል መረጃ መዘወዘወር ከጀመረ ሰነባብቷል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ይህንኑ እየተናሩ ነው፡፡ የዲሞክሪሳዊ ስምረት ትግራይ ፓርቲ የኤርትራ ገንዘብ በክልሉ ግበያ ውስጥ መሰራጨቱን ለግብያት እና ሸቀጥ ልውውጥ መዋሉን ተናግሯል፡
Jan 222 min read


የብር ኖትን በሃገር ውስጥ ማሳተም ካለው ክብደት አንፃር ወይስ ትኩረት ያለ መስጠት ችግር?
ጥር 13/2018 መንግስት እስከ ዛሬ በውጪ የሚታተመውን የኢትዮጵያ የብር ኖቶች በሃገር ውስጥ የማተም ዕቅድ እንዳለው ተናግሯል። ይህም የብር ኖቶችን በውጪ ሃገራት ለማሳተም ሀገር የምታወጣውን ወጪ ያስቀርላታል ተብሏል። ለመሆኑ የብር ኖቶችን በሃገር ውስጥ ማተም በቢሊዮን ዶላሮች የሚያስወጣውን ወጪ የሚቀንስ ከሆነ እስከ ዛሬስ በውጪ ሃገር ማሳተሙ ለምን ተመራጭ ሆኖ ቆየ? የብር ኖትን በሃገር ውስጥ ማሳተም ካለው ክብደት አንፃር ወይስ ትኩረት ያለ መስጠት ችግር? የምጣኔ ሃብት ባለሙያው አቶ ጥላሁን ግርማ ለዘርፉ ትኩረት ያለመስጠት ችግር ነው የሚል ምላሽ አላቸው። ባለሙያው መንግስታት የራሳቸው ቅድሚያ የሚሰጡአቸው ጉዳዮች ስሏሏቸው እስከ ዛሬም የብር ኖቶችን በሃገር ውስጥ ማሳተም ብዙም ትኩረት ሳይሰጡት ቆይተው ሊሆን ይችላል? የሚል ሙ
Jan 212 min read


አለም አቀፍ ገዥዎች በዋጋ ምክንያት ለኢትዮጵያ ሰሊጥ የሚያሳዩትን ፍላጎት እየቀነሱ ነው ተባለ።
ጥር 13/2018 አለም አቀፍ ገዥዎች በዋጋ ምክንያት ለኢትዮጵያ ሰሊጥ የሚያሳዩትን ፍላጎት እየቀነሱ ነው ተባለ። የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት እና ብራዚል ሰሊጥን ከኢትዮጵያ ባነሰ ዋጋ ለአለም ገበያ እያቀረቡ በመሆናቸው የገዥዎች ፍላጎት ወደ እነሱ እያደላ ስለመሆኑ ተነግሯል። ሰሊጥ ከሀገር ውስጥ አምራቾች የሚገዛበት ዋጋ ከፍ ያለ በመሆኑ በአለም አቀፍ ግብይቱ ላይ ተፅዕኖ እየፈጠረ እንደሚገኝ ተነግሯል። ከአምራቾች ከፍ ባለ ዋጋ የተገዛውን ሰሊጥ ተወዳዳሪ ሆኖ በአለም ገበያ ላይ መሸጥ እንዳልተቻለ ከኢትዮጵያ ጥራጥሬ፣ ቅባት እህሎችና ቅመማ ቅመም ላኪዎች ማህበር ሠምተናል። ብራዚልን የመሰሉ አዳዲስ ሰሊጥ አምራች ሀገራት አጋጣሚውን በሰፊው እየተጠቀሙበት እንደሚገኙ የማህበሩ ፕሬዚዳንት አቶ ኤዳኦ አብዲ ተናግረዋል። እኛ በሜትሪክ ቶን እስከ 1300 ዶላር የ
Jan 212 min read


ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋቢ ሸበሌ ሆቴልን ገዛው።
ጥር 13/2018 ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋቢ ሸበሌ ሆቴልን ገዛው። የግዢና ሽያጭ ስምምነቱን የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አሕመድና የዋቢ ሸበሌ ሆቴል አክሲዮን ማህበር የቦርድ ፀሀፊ ልዑል በዕደማርያም መኮንን ተፈራርመዋል። ሚድሮክ ዋቢ ሸበሌ ሆቴልን ዘመናዊና ቅንጡ በሆነ መልኩ የማሪዮት ደረጃን (autograph collection by Marriot ) ጠብቆ እንደሚያድሰውና ኢትዮጵያ ለምታዘጋጀው 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ እንደሚያደርሰው ተናግሯል። አቶ ጀማል አሕመድ የሆቴሉን አገልግሎት በዘርፉ አለም በደረሰበት ደረጃ በማዘመን ለእንግዶች ምቹና ጥራቱን የጠበቀ የማረፊያ ቦታ ለማድረግ እንደሚሰራ ተናግረዋል። የዋቤ ሸበሌ ሆቴል የቦርድ ፀሀፊ ልዑል በዕደማርያም መኮንን የሆቴሉን ታሪክ ጠብቆ በማዘ
Jan 211 min read


ደህንነቱ ያልተጠበ ከ13 ሺህ ኩንታል በላይ የጨው ምርት በክትትል መያዙን የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ተናገረ።
ጥር 13/2018 ደህንነቱ ያልተጠበ ከ13 ሺህ ኩንታል በላይ የጨው ምርት በክትትል መያዙን የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ተናገረ። ባለስልጣኑ ይህንን ያለው ከብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት ጋር በትብብር በመሆን በህብረተሰቡ ላይ የጤና ጉዳት የሚያስከትሉ ምርቶችን በተመለከተ የወሰደውን ርምጃ አስመልክቶ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ ላይ ነው። የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ነጋሸ ስሜ እነዚህ የተያዙ የጨው ምርቶች ለጤና ጎጂ መሆናቸው በላብላቶሪ ተረጋግጧል ብለዋል። የጨው ምርቶቹ በተለይም በአስገዳጅነት ማሟላት ያለባቸውን የአዮዲን መጠን ሳያሟሉ የቀሩ ናቸው ተብሏል። በህጉ መሰረት የጨው ምርት ለገበያ ከመቅረቡ በፊት በተመጠነ አዮዲን መበልፀጉ መረጋገጥ አለበት ተብሏል። አሁን ተያዙ የተባሉ የጨው ምርቶች
Jan 211 min read


በኢትዮጵያ ፈቃድ ያላቸው መገናኛ ብዙኃን 309 ደረሱ ተባለ።
ጥር 13/2018 በኢትዮጵያ ፈቃድ ያላቸው መገናኛ ብዙኃን 309 ደረሱ ተባለ። እነዚህ መገናኛ ብዙሀን ተመዝገበውና ፈቃድ አግኝተው በስራ ያሉ መሆናቸው ተነግፘል። በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በህጋዊ መንገድ ፈቃድና ምዝገባ አግኝተዉ የሚንቀሳቀሱ የብሮድካስት፣ የበይነ መረብ፣ የህትመት እና የዉጭ መገናኛ ብዙኃን መሆናቸውን ሰምተናል። ከ 309 ውስጥ 175 የብሮድካስት፣ 20 የህትመት፣ 35 የዉጭ ሚዲያ ክሮስፖንዳንት፣ 73 የበይነመረብ፣ አምስት የክፍያ ኢንተርኔት ብሮድካስት እና አንድ ነፃ የኢንተርኔት ብሮድካስት መገናኛ ብዙኃን በባለሥልጣኑ ምዝገባ እና ፈቃድ አግኝተው እየተንቀሳቀሱ መሆኑ ታውቋል። ከእነዚህም ውስጥ 254ቱ በስርጭት ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ 55ቱ ደግሞ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ባለስልጣኑ ተናግሯል። በባለሥልጣኑ ባለፉት ስድስት
Jan 211 min read


ለኢመደበኛ ፍለሰቱ ትልቁ ምክንያት ተደረጎ የተነሳውም ድህነት ነው፡፡
ጥር 12/2018 በአንዳንድ አካባቢዎች የሀይማኖት መሪዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች ሳይቀር ወጣቶችን ወደ ስደት መርቀው መሸኘታቸው ኢመደበኛ ፍልሰትን ከሚያስፋፉ ምክንያቶች አንዱ ሆኖ ቀጥሏል ሲል የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ፡፡ እነዚህ አካላት ይህንን የሚያደርጉትም በኢመደበኛ ስደት ወጣቶች የሚደርስባቸው አደጋ እና ስቃይ ካለለመገንዘብ ነው ብሏል፡፡ በየአካባቢው ‘’የእከሌ ልጅ እኮ ያለፈለት እና ለቤተሰቦቹም ኤፍኤስአር(FSR) መኪና የገዛው ስደት ሄዶ ነው’’ በሚሉ እና መሰል ማበረታቻዎች ወጣቶች ለኢመደበኛ ፍልሰት እየተዳረጉ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ ይህ የተነገረው የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የአካል ጉዳተኞች፣ የአረጋውያን፣ የማህበራዊ ጥበቃ መብቶች፣ ኢመደበኛ ፍልሰትን እና ቤተሰብን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ለሚዲያ
Jan 201 min read
የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡
ጥር 12/2018 የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር "ስራቸውን በአግባቡ አልሰሩም፣ ህግን አላከበሩም ፣ ኦዲት ሪፖርት ለዓመታት አላቀረቡም ፣ጠቅላላ ጉባዔም ወቅቱን ጠብቀው ማካሄድ አልቻሉም"በሚል ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡ የቀድሞ ቦርድ አባላት ስራቸወን በአግባቡ ባለመስራታቸው እና ሪፖርት ባለማቅረባቸው "ይቅርታ" ጠይቀዋል፡፡ ከ600 በላይ ንቁ በስራ ላይ ያሉ ድርጅቶች አባላት ያሉት ማህበሩ ጥቅላላ ጉባዔውን እና የምስረታ 50ኛ ዓመቱን ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ በቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ፋካሊቲ የመሰብሰብያ አዳራሽ አካሂዷል፡፡ የተከናወኑ ስራዎችን እና ዓመታዊ ሪፖርት እንዲቀርብ ወደ መድረክ ወጥተው የነበሩት የማህበሩ ፕሬዚዳንት እና የቦርድ አባላት በአግባቡ የተቀናጀ ሪፖርት አ
Jan 203 min read


የወል ትርክት እንዴት መገንባት ይቻል ይሆን?
ጥር 7/2018 በኢትዮጵያ ትርክቶች በዝተው ከአንድነት ይልቅ ልዩነት እየሰፋ መምጣቱ እንዳሳሰባቸው የሚናገሩ ብዙዎች ናቸው፡፡ ለኢትዮጵያውያን የጋራ መገለጫ የሆኑ የበዙ ሁነቶች እና ታሪኮች ባለቤት ብንሆንም በተቃራኒ ትርክቶች በዝተው ከአንድነት ይልቅ ልዩነት እየሰፋ መምጣቱ እንዳሳሰባቸው የሚናገሩ ብዙዎች ናቸው፡፡ መንግስትም የፀና ሀገረ መንግስት ለመገንባትም ጭምር የሚያለያዩ ትርክቶችን በጋራ ትርክት መተካት ያስፈልጋል በሚል እየሰራበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ለመሆኑ ለዘመናት የዘለቁ የብሔርተኝነት የልዩነት ትርክቶች ለጦርነትና ራሴን ችዬ ሀገር እሆናለሁ እስከማለት በደረሰበት በአሁኑ ወቅት የጋራ ትርክትን መገንባት ይቻላል ወይ? ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ያሬድ እንዳሻው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ….. YouTube :...
Jan 151 min read


ግብርናውን ለማዘመን የገበሬውን ህይወት ለማሻሻል እና የተሻለ ምርታማነት እውን እንዲሆን የምርምር ስራዎች ሲከወኑ ቆይቷል፡፡
ጥር 7/2018 ግብርናውን ለማዘመን የገበሬውን ህይወት ለማሻሻል እና የተሻለ ምርታማነት እውን እንዲሆን የምርምር ስራዎች ሲከወኑ ቆይቷል፡፡ ለተጠቀሰው መሰል ዓላማ ከሰራቸው 400 የምርምር ስራዎች መካከል 20 ከመቶ የሚሆኑት በስራ ላይ ሳይውሉ መቅረታቸውን የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ተናግሯል፡፡ 80 ከመቶ ወይም 320 ተቋሙ የሰራቸው የምርምር ስራዎች ደግሞ ለታለመላቸው ዓላማ በስራ ላይ መዋላቸውን ሰምተናል፡፡ ተቋሙ ይህን ያለው የ15 ዓመታት የሰራውን ስራ በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ ነው ፡፡ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሴ(ዶ/ር) ተቋማቸው ላለፉት 15 ዓመታት ከሰራቸው ጥናቶች መካከል 80 የሚሆኑት ወደ ስራ ያልገቡት እንዲጠናላቸው ያዘዙ ተቋማት ጥናቱን ለመተግበር አቅም ስላነሳቸውና
Jan 151 min read


የኒውክሊየር ኃይል ከውሃ፣ ከንፋስና ከፅሐይ የኃይል አማራጮች በተሻለ ለኢትዮጵያ ምን የተለየ ነገር ይዞላት ይመጣ ይሆን?
ጥር 6/2018 ኢትዮጵያ 13 ቢሊየን ዶላር በጀት ይጠይቃል የተባለን የኒውክሊየር ሀይል ማመንጫ ለመገንባት በዝግጅት ላይ ነች፡፡ በውሃ፣ ነፋስና ፀሐይ ላይ ጥገኛ የነበረው የኤሌክትሪክ ሀይል አማራጭ የኒውክሊየር ሀይልንም ይጠቀማል ተብሏል፡፡ የኒውክሊየር ሀይል ግንባታ ለኢትዮጵያ ምን ይዞላት ይመጣል? የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይል ኮምሽን ምክትል ኮሚሽነር ኢንጅነር አብዱልቃድር ዑመር የኒውክሊየር ኃይል ከሌሎች የአሌክትሪክ ኃይል አማራጮች በተሻለ በተለዋዋጭ የአየር ሁኔታ እና ሌሎች ተፅዕኖ ውስጥ ሆኖ እንኳን የማይወዥቅ የኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ ይችላል ይላሉ፡፡ ምክትል ኮሚሽነሩ ውሃ፣ ፀሐይ እና ንፋስ የኃይል አማራጮች የማመንጨት አስተማማኝነታቸው 50 ከመቶ በታች ሲሆን የኒውክለር ግን 92 በመቶ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ ይህም ኒውክለርን ከሌሎች የኃይል
Jan 142 min read


በሀገራዊ ምክክር የፖለቲካ ልሒቃን፣ ፖለቲከኞች መሳተፍ አለመሳተፍ በውጤቱ ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ ምንድን ነው?
ጥር 6/2018 በሀገራዊ ምክክር የፖለቲካ ልሒቃን፣ ፖለቲከኞች መሳተፍ አለመሳተፍ በውጤቱ ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ ምንድን ነው? የሁለቱን ወገን ሃሳብ ጠይቀናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ያሬድ እንዳሻው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ….. YouTube : https://url-shortener.me/2DTR Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 Facebook፡ https://url-shortener.me/2DTY WhatsApp : https://url-shortener.me/2DU0 X : https://x.com/shegerfm?s=2 Website፡ https://www.shegerfm.com/ LinkedIn : https://url-sh
Jan 141 min read


በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የግል አየር መንገዶች ለአውሮፕላኖቻቸው ጥገና በዓመት እስከ 800,000 ዶላር ያወጣሉ ተባለ፡፡
ጥር 6/2018 በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የግል አየር መንገዶች ለአውሮፕላኖቻቸው ጥገና በዓመት እስከ 800,000 ዶላር ያወጣሉ ተባለ፡፡ አየር መንገዶቹን ከዚህ ወጪ፣ የውጭ ሀገር ጉዞና እንግልት ለማዳን ያግዛል የተባለ አገልግሎት እንዲሰጥ ለኢትዮጵያ አየር ሀይል የአውሮፕላን ጥገና ፈቃድ ተሰጥቶታል፡፡ በኢትዮጵያ ያሉ የግል አየር መንገዶች በቁጥር አስራ ሁለት መድረሳቸው ተነግሯል። የነዚህ አየር መንገዶች ንብረት የሆኑ መካከለኛና አነስተኛ አውሮፕላኖች ጥገና ሲፈልጉ አገልግሎቱን የሚሰጣቸው እራሱን የቻለ የጥገና ማዕከል በሀገር ውስጥ አልነበረም ተብሏል። በዚህም ምክንያት ለጥገና አገልግሎት ወደ ኬንያና ሌሎችም ሀገሮች ለመጓዝ እንደሚገደዱ ተሰምቷል። ይህም ብዙ ወጪን የሚያስወጣቸው አቅማቸውንም የሚፈታተን መሆኑን ሰምተናል። አሁን ግን
Jan 141 min read


የኦሮሚያ ሕብረት ስራ ባንክ ከ20.5 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎች ባለው በኮፔይ ኢ - ብር እስካሁን ከ4.8 ትሪሊዮን ብር በላይ ግብይት መፈጸሙን ተናገረ።
ጥር 6/2018 የኦሮሚያ ሕብረት ስራ ባንክ ከ20.5 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎች ባለው በኮፔይ ኢ - ብር እስካሁን ከ4.8 ትሪሊዮን ብር በላይ ግብይት መፈጸሙን ተናገረ። ባንኩ ከውጭ ሀገር የሚላክላቸውን የውጭ ምንዛሬ ከባንኩ በኩል ለተቀበሉ ደንበኞቹ ባዘጋጀው የውጭ ምንዛሪ የሎተሪ እድለኞችን ሸልሟል፣ ዲጂታል ሎተሪ ሽያጭ እንደሚጀምር ተናግሯል። የተላከላቸውን የውጭ ሀገር ገንዘብ ከኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ በመቀበላቸው እድለኛ የሆኑ ደንበኞች አንድ ዘመናዊ የቤት መኪና፣ 2 የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል ፣10 ላፐቶፖች፣ 10 ቴሌቪዥኖችና 40 ስማርት ስልኮች በአጠቃላይ 63 ሸልማቶች ዕድለኞች ተበርክተዋል። የባንኩ ኦፕሬቲንግ ተጠባባቂ ቺፍ አፊሰር አቶ አብዲ ፈቀደ ባንኩ ከኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎትና ታምሶል ኮሚዩኒኬሽን ጋር በመተባበር፣ በኮፔይ ኢ-ብር
Jan 141 min read


በትግራይ ክልል ከጦርነቱ በፊት በባንክ ብድር ተገንብተው በጦርነቱ የወደሙ ፕሮጀክቶች እዳ ሙሉ በሙሉ እንዲሰረዝ የክልሉ ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክርቤት ብሔራዊ ባንክን በደብዳቤ ጠየቀ፡፡
ጥር 5/2018 በትግራይ ክልል ከጦርነቱ በፊት በባንክ ብድር ተገንብተው በጦርነቱ የወደሙ ፕሮጀክቶች እዳ ሙሉ በሙሉ እንዲሰረዝ የክልሉ ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክርቤት ብሔራዊ ባንክን በደብዳቤ ጠየቀ፡፡ የትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክርቤት የክልሉ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ብድር ከሰሜኑ ጦርነት በፊት ማለትም ከ2012 ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ ከነበረበት 32 ቢሊዮን ከነወለዱ አሁን ከ80 ቢሊዮን ብር በላይ ሆኗል ብሏል፡፡ ምክርቤቱ በክልሉ ለንግድ እና ኢንቨስትመንት የተወሰዱ የባንክ እዳዎች የንግዱ ማህበረሰብ መክፍል ስለማይችል ከፕሪቶሪው የሰላም ስምምነት በኋላ የመክፈያ ጊዜ ገደብ ለ18 ወራት ተራዝሞለት እንደነበር የምክርቤቱ ፕሬዝዳንት አቶ በሪሁ ሃፍቱ ተናግረዋል፡፡ ንጋዴዎቹም ሆኑ አልሚዎቹ በተሰጣቸው 18 ወራት ስራ
Jan 132 min read


በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ከሳምንት በኋላ በሚከበረው የጥምቀት በዓልም የተሻለ የቱሪስት ፍሰት እንደሚኖር ዝግጅት ተደርጓል፡፡
ጥር 5/2018 ከፍ ያለ የውጭ ቱሪስት ከሚገኝባቸውና የሀገር ውስጥ ቱሪዝም እንቅስቃሴም ሞቅ ከሚልባቸው ሃይማኖታዊ በዓላት መካከል የጥምቀት በዓል አንዱ ነው፡፡ በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ከሳምንት በኋላ በሚከበረው የጥምቀት በዓልም የተሻለ የቱሪስት ፍሰት እንደሚኖር ዝግጅት ተደርጓል፡፡ በቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎች ለቱሪስቶች የተሻለ የትራንስፖርት አማራጭ እንዲኖርና ለብዙዎችም ጊዜያዊ የስራ እድል እንዲፈጠር እየተሰራ ነው ተብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. በረከት አካሉ YouTube : https://url-shortener.me/2DTR Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 Facebook፡ https://url-shortener.me/2DTY WhatsApp : https://url-shortener.me/2D
Jan 131 min read


ሜታ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሆኑ የአውስትራሊያ አዳጊ ወጣቶችን ገፆቹን እንዳይጠቀሙ አደረጋቸው፡፡
ጥር 5/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #አውስትራሊያ የእነ ፌስ ቡክ እና ኢኒስታግራም የማህበራዊ ድረ ገፆች እናት ኩባንያ (ሜታ) ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሆኑ የአውስትራሊያ አዳጊ ወጣቶችን ገፆቹን እንዳይጠቀሙ አደረጋቸው፡፡ ክልከላው በአውስትራሊያ ስራ ላይ የዋለውን ህግ መሰረት ያደረገ መሆኑን ABC ፅፏል፡፡ አዲሱ የአውስትራሊያ ህግ እድሜያቸው ከ16 አመታት በታች የሆነ አዳጊ ወጣቶች በጭራሸ የማህበራዊ ትስስር ገፆችን እንዳይገለገሉ የሚከለክል ነው፡፡ አዳጊ ወጣቶች ክልከላውን ተላልፈው የማህበራዊ ትስስር ገፆቹን ሲገለገሉ ከተገኙ አገልግሎት አቅራቢያ ኩባንያዎች የገንዘብ ቅጣት እንዲቆነደዱ ያደርጋል፡፡ አዳጊ ወጣቶችን የማህበራዊ ትስስር ገፆችን እንዳይገለገሉ በማድረግ አውስትራሊያ ቀዳሚዋ አገር ሆናለች፡፡ #ሶማሊያ የሶማሊያ ፌዴራላዊ መንግስት ከተባበ
Jan 132 min read


ሠራተኞቻቸውን የጡረታ መዋጮ በጊዜው ገቢ የማያደርጉ የግል ድርጅቶች ራሳቸውን ላልተገባ ቅጣት እና ወለድ እየዳረጉ ነው ተባለ።
ጥር 5/2018 ሠራተኞቻቸውን የጡረታ መዋጮ በጊዜው ገቢ የማያደርጉ የግል ድርጅቶች ራሳቸውን ላልተገባ ቅጣት እና ወለድ እየዳረጉ ነው ተባለ። ሃብት ንብረታቸውን ሸጦ የጡረታ መዋጮው ገቢ እንዲሆን እስከ ማድረግ የሚደርስ እርምጃ ሊወስድባቸው እንደሚችልም የግል ድርጅት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር አሳስቧል። አንድ እና ከአንድ በላይ ሠው የቀጠረ ማንኛውም የግል ድርጅት ሠራተኛውን ወደ ጡረታ አቅድ የማስገባት ግዴታ እንዳለበት የግል ድርጅት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር አሳስቧል፡፡ ሠራተኛው ወደ ጡረታ ስርአቱ መግባት ያለበት ከተቀጠረ ከአርባ አምስት ቀናት በኋላ እንደሆነ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አባተ ምትኩ ተናግረዋል። አብዛኞቹ ቀጣሪ ድርጅቶች ግን ሠራተኛው ኮንትራት ነው ወይም ጊዜያዊ ነው በሚል ይህን ግዴታ ያለ ማክበር ዝንባ
Jan 131 min read


የትምባሆ ኢንዱስትሪዎች በመንግስት አካላት እና በፖሊሲ አውጪዎች ላይ ጫና በማሳደር ስለ ትንባሆ አሳሳች መልክቶችን በማሰራጨት ንግዳቸውን ለማስፋፋት እየሰሩ እንደሆነ ተነግሯል።
ጥር 5/2018 የትምባሆ ኢንዱስትሪዎች በመንግስት አካላት እና በፖሊሲ አውጪዎች ላይ ጫና በማሳደር ስለ ትንባሆ አሳሳች መልክቶችን በማሰራጨት ንግዳቸውን ለማስፋፋት እየሰሩ እንደሆነ ተነግሯል። ኢንዱስትሪዎቹ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ነን በሚል፣ የበጎ አድራጎት ስራን በማስታከክ እና በሌሎች ዘዴዎች የትምባሆ ስርጭትን ለማስፋፋት እየሰሩ ነው ተብሏል። ከዚህ በተጨማሪም በዣንጥላዎች፣ በቲሸርቶች እና በመሰል ምርቶች ላይ ማስታወቂያዎችን እየሰሩ መሆኑም ተጠቅሷል። የእነዚህን የኢንዱስትሪዎች ጫናን በመቋቋሙና ዘርፋን በመቆጣጠሩ የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን የተሻለ ስራ ሰርቻለሁ ብሏል። በዓለም ዓቀፍ ደረጃ 100 ሀገራት በተካተቱበት ጥናት፤ ኢትዮጵያ የትምባሆ ምርቶችን በመቆጣጠሩ የተሻለ አፈፃፀም አስመዝግባለች ተብሏል። በዚህ ጥናት ኢትዮጵያ የትምባሆ
Jan 131 min read


10 ቢሊዮን ዶላር ወጪ የሚጠይቀው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ተጀመረ።
ጥር 2/2018 10 ቢሊዮን ዶላር ወጪ የሚጠይቀው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ተጀመረ። ግንባታውን ያስጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ናቸው፡፡ የቢሾፍቱ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ፕሮጀክት ይሆናል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስረድተዋል። ይኽም ከኢትዮጵያ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ሪፎርም፣ የኢንደስትሪ ማስፋፊያ አጀንዳ እና የረጅም ዘመን የአቪየሽን ስትራቴጂ ጋር የተናበበ ነውም ሲሉም አክለዋል። ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድን አለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያጠናክራል። በAfCFTA ማህቀፍ የአፍሪካን የማገናኘት አቅም ይጨምራል ተብሏል። ከአዲስ አበባ ደቡብ ምስራቅ 40 ኪሎሜትር አካባቢ የምትገኘውና 1910 ሜትር ከፍታ ያላት ቢሾፍቱ ለአውሮፕላኖች ሥራ የተመቸ ከባቢ ያላት ሲሆን
Jan 101 min read


በአዲስ አበባ አንዳንድ የወረዳ አመራሮች ተገልጋዩን ያመነጫጭቃሉ፣ ለጥያቄም ምላሽ አይሰጡም የሚል ቅሬታ ቀረበባቸው።
ጥር 2/2018 በአዲስ አበባ አንዳንድ የወረዳ አመራሮች ተገልጋዩን ያመነጫጭቃሉ፣ ለጥያቄም ምላሽ አይሰጡም የሚል ቅሬታ ቀረበባቸው። የከተማ አስተዳደሩ በበኩሉ በአግባባቡ ስራቸውን መስራት ያልቻሉ ሃላፊዎች ላይ እርምጃ እንደተወሰደባቸው አንደሆነ አስረድቷል፡፡ ቅሬታው የቀረበባቸው የከተማው የሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ በስድስት ወራት የስራ ክንውን ዙሪያ ትናንት ቅዳሜ ጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ከሚመለከታቸው የከተማው ባለድርሻ አካላት ጋር ወይይት ባካሄደበት ወቅት ነው። የወይይቱ ተሳታፊዎች አገልግሎት ለማግኘት ወደ ወረዳ ሲያቀኑ በሁሉም ባይሆንም በአንዳንድ አመራሮች ማመነጫጨቅ እና ማንገላታት እንደሚያጋጥማቸው እንዲሁም ለጥያቄያቸው ምላሽ እንደሚነፍጓቸው ተናግረዋል። ወይይቱን የመሩት የአዲስ አበባ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ አማካሪ
Jan 101 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

