ኢትዮጵያ በ2018 በጀት አመት በ9 ወራት ውስጥ ከወጪ ንግድ 7 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ገቢን አግኝታለች፡፡
- 1 day ago
- 1 min read
ሐምሌ 7/2018
ኢትዮጵያ በ2018 በጀት አመት በ9 ወራት ውስጥ ከወጪ ንግድ 7 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ገቢን አግኝታለች፡፡
ከውጪ አስፈላጊ ለምትላቸው እቃዎች ግዢ 16 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ አውጥታለች፡፡
በዘጠኝ ወራቱ ኢትዮጵያ ወደ ውጪ ከላከችው እቃ ያገኘችው ገቢና ወደ ሀገር ውስጥ ላስገባችው እቃ ያወጣችው ወጪ መካከል ያለው ልዩነት የ8 ነጥብ 9 ቢሊዮን ዶላር ነው፡፡
ይህም በወቅቱ የኢትዮጵያ የንግድ ሚዛን ጉድለት መጠኑን ያሳያል፡፡
በ2017 በጀት አመት የኢትዮጵያ የንግድ ሚዛን ጉድለት 10 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የበጀት አመቱ አጠቃላይ የንግድ ሚዛን ጉዱለት ከዚህ ሊቀንስ እንደሚችል ተነግሯል፡፡
በ2018 በጀት አመት 11 ቢሊዮን ዶላር ከወጪ ንግድ ያገኘችው ኢትዮጵያ ከባለፈው አመት ጋር ሲመሳከር የ2 ነጥብ 8 ቢሊዮን ዶላር ጭማሪ ያሳያል፡፡
ታዲያ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የንግድ ሚዛን ጉድለት ምን ቢሰራ ማጥበብ ይቻላል ? በስንት ጊዜስ ? የዘርፉ ባለሙያን ጠይቀናል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ....
በረከት አካሉ





Comments