top of page

በሰባተኛው ሃገራዊ ምርጫ የተከሰቱ ችግሮች እንዳይደገሙ የህግ ማሻሻያ በማድረግ እንዲታረሙ ተጠየቀ፡፡

  • 5 hours ago
  • 1 min read

ሐምሌ 3/2018


በሰባተኛው ሃገራዊ ምርጫ የተከሰቱ ችግሮች መልሰው እንዳይደገሙ የህግ ማሻሻያ እና የአፈፃፀም ማስተካከያ በማድረግ እንዲታረሙ ተጠየቀ፡፡


ባለፈው ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም በተፈናቃይ ካምፖች በተቋቋሙ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች የተካሄደው ምርጫ የራሱ መመሪያ ወጥቶለት የተካሄደ አዲስ አሰራር ነበር፡፡


በልዩ ሁኔታ ምርጫ ስለሚካሄድባቸው ምርጫ ጣቢያዎች ማቋቋሚያ መመሪያ ወጥቶ ተፈናቃዮች የመምረጥ መብታቸውን እንዲጠቀሙ መደረጉ መልካም መሆኑ በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በገለልተኝት ምርጫውን የታዘበው የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች ህብረት ተናግሯል፡፡



ይሁንና ተፈናቃዮች የሚሰጡት ድምፅ ወደ ተፈናቀሉበት ቀዬ ሂዶ የሚቆጠር መሆኑ ለምርጫው ፍላጎት እንዲያጡ አድርጓቸዋል ብሏል፡፡


ለዚህም እንደማሳያ ከ20 ሺህ በላይ ተፈናቃዮች በነበሩበት ካምፕ 40 የማይሞሉ ሰዎች የመረጡበት አጋጣሚ መኖሩን ጠቅሷል፡፡


በመሆኑም ለመጭው ምርጫ የህግ ማሻሻያ ያስፈልገዋል ሲል ነግሮናል፡፡


በጉዳዩ ላይም ከምርጫ ቦርድ እና ከመጭው ፓርላማ ጋር ልነጋገርበት እቅድ ይዣለሁም ብሏል፡፡


እንዲሁም የመረጃ እጥረት እና ሕፃናት ጭምር በምርጫ እንዲሳተፉ የተደረጉበት የአፈፃፀም ችግሮችም ለወደፊቱ ትምህርት ሆነው ሊታሙ የሚገቡ ናቸው ሲል አሳስቧል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ……


ትዕግስት ዘሪሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



YouTube : https://shorturl.at/18TS1






Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page