ተመካካሪዎች በተመደቡላቸው አጀንዳዎች ላይ መመካከር መጀመራቸውን የምክክር ኮሚሽን ተናገረ፡፡
- 4 hours ago
- 1 min read
ሐምሌ 13/2018
ተመካካሪዎች በ80 ንዑስ ቡድኖች በመከፈል በተመደቡላቸው አጀንዳዎች ላይ መመካከር መጀመራቸውን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተናገረ፡፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እየተካሄደ ባለው የምክክር ጉባኤ የዛሬውን የምክክር ሂደት አስመልክቶ መግለጫ በሰጠው መግለጫው፤ በንዑሳን ቡድኖች የተከፈሉት ተመካካሪዎች በተመደቡበት አጀንዳ ላይ መመካከር መጀመራቸውን ተናግሯል፡፡
የዛሬውን መግለጫ የሰጡት የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር ሙሃሙድ ድሪር በእያንዳንዱ ንዑስ ቡድን ውስጥ 50 ተመካካሪዎች ያሉ ሲሆን በአጠቃላይ 80 አነስተኛ ቡድኖች እየተመካከሩ ይገኛሉ ብለዋል፡፡

በአንድ አጀንዳ ላይ እንዲመካከር የተመደበ ዐብይ የስራ ቡድን 500 ተመካካሪዎችን ሲይዝ በስሩ እያንዳንዳቸው 50 ተመካካሪዎችን የያዙ 10 ንኡሳን ቡድኖችን እንዲይዝ ተደርጎ መዋቀሩንም ተናግረዋል፡፡
በአጠቃላይ 80 ንዑስ ቡድኖች በተመደቡላቸው አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ እንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡
ሂደቱ በስኬት እንዲከናወን ኮሚሽኑ በስራ ልምዳቸውና በትምህርት ዝግጅታቸው አንቱታን ያተረፉ 160 የሚሆኑ አመካካሪዎችን መመደቡን በመግለጫቸው አመልክተዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም 256 የሚሆኑ የቃለ ጉባኤ ጸሃፊዎች ተሰማርተው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን በብቃት እየመሩ ይገኛሉ ሲሉም የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር ሙሃሙድ ድሪር በዛሬው መግለጫቸው አስረድተዋል፡፡
ምንታምር ፀጋው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7
_edited.jpg)
