top of page

የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በተልዕኮ ተለይተው በተወሰኑ የትምህርት መስኮች ላይ ትኩረት አድርገው እንዲያሰተምሩ መደረጉ

  • 1 day ago
  • 1 min read

ሐምሌ 9/2018


የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በተልዕኮ ተለይተው በተወሰኑ የትምህርት መስኮች ላይ ትኩረት አድርገው እንዲያሰተምሩ መደረጉ ለውጥ ማምጣቱን ጥናት አሳይቷል፡፡

 

በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራት መጓደልን ለማስተካከል በዘርፉ የተለያዩ የለውጥ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ ይነገራል፡፡


በተለይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተልዕኮ እና በትኩረት ተለይተው እንዲሰሩ ማድረግ ለትምህርት ጥራትና ለሀገር ኢኮኖሚ ወሳኝ ነው ተብሎ ታምኖበት ወደ ስራ መገባቱ ይታወሳል፡፡


በዚህ መሰረት ሶስት ዋና ዋና ተልዕኮ ተለይቶ መተግበራቸው የሚታወስ ሲሆን የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች አፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርስቲዎች እንዲሁም አጠቃላይ ዩኒቨርስቲዎች በሚል መለየታቸው ተነግሯል፡፡


እነዚህ ተልዕኮዎች አሁን ላይ ለውጥ እያመጡ ነው ሲሉ በጉዳዩ ላይ ጥናት ያደረጉት በአንቦ ዩኒቨርሲቲ መምህር እና አሁን ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሶስተኛ ዲግሪያቸውን በመስራት ላይ የሚገኙ ጀማል ሹክሩ ነግረውናል፡፡


ይሁንና ተማሪዎችን በታሰበው ልክ ብቁ ለማድረግ ከፍተኛ በጀት የሚጠይቅ በመሆኑ የታሰበው ውጤት ላይ ለመድረስ ገና እንደሚቀረው አሰረድተዋል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….

ማርታ በቀለ

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page