top of page


ጥቅምት 11 2018 - ባህርዳር እና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች በኒኩለር ሳይንስ የሁለተኛ ዲግሪ ት/ት መስጠት መጀመራቸውን ተናገሩ
በኒኩለር ሳይንስ የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርት መስጠት መጀመራቸውን ሁለት ዩኒቨርሲቲዎች ተናገሩ፡፡ ትምህርቱን እየሰጡ ያሉት ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ናቸው፡፡ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ በተያዘው ዓመት ለመጀመርያ ጊዜ በ2ተኛ ዲግሪ ሲያስተምራቸው የነበሩ ተማሪዎች እንደሚያስመርቅ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት መንገሻ አየነ(ዶ/ር) ነግረውናል፡፡ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ደረጀ እንግዳ(ዶ/ር) በበኩላቸው ከሁለተኛ ዲግሪ ባለፈ የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት ለመስጠት ዝግጅት እያጠናቀቁ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ በቅርቡ መንግስትበ ኢትዮጵያ የኒኩለር ፕላንት ለሰላማዊ መንገድ እንደሚገነባ የተናገረ ሲሆን ሁለቱ ተቋማት ለዚህ የሚሆን ባለሞያ ለማፍራት ማቀዳቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. በረከት
Oct 211 min read


ጥቅምት 11 2018 የኢትዮዽያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን በተለያዩ ፕሮጀክቶች ላይ ትኩረት በማድረግ አለም አቀፍ ኩባንያ ለመሆን ጉዞ ጀምሬያለሁ አለ።
ኮርፖሬሽኑ በበፊቱ አዋጅ መሰረት ሶስት የተሰጡትን ግዙፍ የኢንቨስትመንት ክንውኖችን ለመፈፀም ወደ ስራ መግባቱን ተናግሯል። ኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን እፈፅማቸዋለው ካላቸው ግዙፍ ስራዎች፤ አንደኛው የምድር ባቡር መሰረተ ልማት ግንባታ፤ ሁለተኛ የተገነባውን የባቡር ልማት ማከናወን እና ሶስተኛው የመሰረተ ልማት አካል አስተዳደርና ተዛማጅ ስራዎች ናቸው። ኮርፖሬሽኑ ከዚህ በተጨማሪም በአዋጅ በተሰጠው በደረጃ አንድ ኮንትራክተር ፤ በደረጃ አንድ መልቲሞዳል አገልግሎት እንዲሁም በደረጃ አንድ የባቡር አካላት ማምረቻ እና ሌሎች ፈቃዶች ወደ ስራ ለመግባት ማሰቡን ሲናገር ሰምተናል። የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሸን ዛሬም የመንግስትና የግል ሽርክና በማስማማት ፋይናንስ ለማሰብሰብ ሲመክር ውሏል። ኮርፖሬሽኑ እነዚህን ግዙፍ ፕሮጀክቶች ለማልማት በሽርክና ማህ
Oct 212 min read


ጥቅምት 11 2018 - የጫኝ እና አውራጅ ጉዳይ
በአዲስ አበባ ከተማ አንዱ የነዋሪዎች ፈተና የጫኝ እና አውራጅ ጉዳይ ነው፡፡ አንድ ሰው ቤት ለመቀየር ፈልጎ እቃውን ሲያጓጉዝ ጫኝ እና አውራጆቹ እቃውን የምንጭነውም ይሁን የምናወርደው እራሳችን በምንተምነው ገንዘብ ነው እያሉ ነዋሪውን ሲያስመርሩት መመልከት የተለመደ ጉዳይ ከሆነ ውሎ አድሯል፡፡ ይህ ደግሞ ነዋሪዎችን ካለው የኑሮ ውድነት ጋር ተደማምሮ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሆነባቸው ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በየአካባቢው በህጋዊ መንገድ የተሰማሩ ጫኝ እና አውራጅን በዘመናዊ መልኩ የሚሰሩ ተቋማት በርከትከት እያሉ ነው፡፡ ከእነዚያም መካከል አንዱ መላ ሎጅስቲክስ ሰርቪስ ነው፡፡ መላ ሎጅስቲክስ ሰርቪስ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች አንዱ የሆነው የቤት ቅየራ አገልግሎት ወደ ስራ ከገባ የአንድ ዓመት እድሜ እንደያዘ የተነገረ ሲሆን የግለ
Oct 211 min read


ጥቅምት 11 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ፈረንሳይ የፈረንሳይ ሹሞች እጅግ ውድ የአገራችንን ቅርሶች ማስጠበቅ ተስኖናል ሲሉ በፀፀት ተናገሩ፡፡ የሹሞቹ አስተያየት የተሰማው በርዕሰ ከተማዋ ፓሪስ ከሚገኘው የሉቨር ቤተ መዘክር ውድ ጌጣ ጌጦች ከተሰረቁ በኋላ እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡ ጌጣ ጌጦቹ የአገሪቱ ቅርሶችም በመሆናቸው በዋጋ እንደማይታመኑ እየተነገረ ነው፡፡ ከተዘረፉት ቅርሶች መካከል የፈረንሳዩ ንጉሰ ነገስት ናፖሊዮን በናፖርት ለባለቤቱ አበርክቶለት የነበረ በአልማዝ የተንቆጠቆጠ ሐብልም ይገኝበታል ተብሏል፡፡ ዘራፊዎቹ ላይ በፍጥነት ካልተደረሰባቸው ቅርሶቹን በማወላለቅ በትንሽ በትንሹ ወደ ውጭ አገራት ሊያሸሿቸው ይችላሉ የሚል ስጋት አሳድሯል፡፡ የፓሪሱ ዘረፋ በመሰል ቤተ መዘክሮች የደህንነት ጥበቃው በእጅጉ እንዲጠናከር የማንቂያ ደወል ሆኗል ተብሏል፡፡ የቤተ መዘክሩ የቅርሶች ዘረፋ በአገሪቱ
Oct 212 min read


ጥቅምት 11 2018 - በኢትዮጵያ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ አርሶ አደሮችን እና አርብቶ አደሮችን በተለያየ መልኩ እየረዳ መሆኑን የአለም ምግብ ድርጅት ተናገረ።
የድርጅቱ የኢትዮጵያ ተወካይ ሙቲንታ አምባይ(ዶ/ር) ይህንን ያሉት ዛሬ በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል በተከበረው የአለም የምግብ ቀን ላይ ባደረጉት ንግግር ነው፡፡ ምርጥ ዘር እና ግብዓት በማቅረብ፣ የማጨጃ እና መውቂያ መሳሪያዎችን በመለገስ፣ በገንዘብ ድጋፍ፣ የገበያ ትስስር በመፍጠር እና በሰብል እና እንስሳት ኢንሹራንስ በሀገሪቱ ከ1.5 ሚሊየን በላይ አርሶ፣ አርብቶ እና ከፊል አርሶ አደሮችን እየደገፈ ነው ሲሉ አስረድተዋል። ካለፈው ጥር ጀምሮ ወደ 47,000 አርሶ አደሮች 35,000 ሄክታር በ5 ክልሎች እየለማ መሆኑን የተናገሩት የድርጅቱ የኢትዮጵያ ተወካይ ከዚህ ውስጥ ከ10,000 በላይ የሚሆነው በመስኖ እየለማ ነው ብለዋል። ምርታማነትን ማሳደግ፣ ገቢን በመጨመር ማህበረሰቡን ከጥገኝነት የማውጣት ስራ ከመንግስት እና ከሌሎች መንግስታዊ ካልሆኑ
Oct 211 min read


ጥቅምት 11 2018 - ክፍት የተተዉ ጉድጓዶች
በአዲስ አበባ በየጎዳናው ክዳናቸው ተሰርቆ ወይም ተሰብሮ ክፍት የተተዉ ጉድጓዶች ለተለያየ አደጋ ምክንያት መሆናቸውን ቀጥለዋል፡፡ በየዓመቱ 6,000 ክዳኖች እየተዘጋጁ ለአደጋ የሚያጋልጡ ጉድጓዶች እየተከደኑ ቢሆንም አሁንም ስርቆቱ የቀጠለ በመሆኑ ችግሩን መቅረፍ አዳጋች ሆኗል ተብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ገዛ ጌታሁን የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s 🐦X : https://x.com/sheg
Oct 211 min read


ጥቅምት 11 2018 - የማሻሻያ እርምጃ ተከትሎ የኢትዮጵያ ጥቅል ሀገራዊ ምርት በ90 ቢሊዮን ዶላር ቀንሷል
ከዓመት በፊት የተወሰደውን የውጪ ምንዛሪ አስተዳደር የማሻሻያ እርምጃ ተከትሎ የኢትዮጵያ ጥቅል ሀገራዊ ምርት (GDP) በ90 ቢሊዮን ዶላር ቀንሷል፡፡ እንዲያም ሆኖ የተሻለ የ GDP እድገት ካላቸው ሀገራት መካከል ነች የተባለችው ኢትዮጵያ በዚህ ዓመት አንዱ ትኩረቴም ጥቅል ሀገራዊ ምርቱን ይበልጥ ማሳደግ ላይ ይሆናል ብላለች፡፡ ለመሆኑ የትኞቹ ዘርፎች ላይ ትኩረት ብታደርግ ይሻላታል? የምጣኔ ሐብት ባለሞያን ጠይቀናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ ንጋቱ ረጋሣ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com
Oct 211 min read


ጥቅምት 10 2018 - ድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሀብት እና ዓለም አቀፍ ህጎች (ክፍል 1)
#ጉዳያችን - ድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሀብት እና ዓለም አቀፍ ህጎች ኢትዮጵያ ካሏት ተፋሰሶች 90 በመቶ የሚሆነው ድንበር ተሻጋሪ ነው። ለመሆኑ ድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሀብት መካከል አለመግባባት ሲፈጠር በዓለም አቀፍ ህግ እንዴት ይዳኛል? በጉዳዩ ላይ፣ የአለም አቀፍ የውሃ ህግ ባለሞያ የሆኑት ከበደ ገርባ(ዶ/ር) የሰጡንን ማብራሪያ ያድምጡ…. ቴዎድሮስ ወርቁ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s 🐦X : https:
Oct 211 min read


ጥቅምት 11 2018 - ድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሀብት እና ዓለም አቀፍ ህጎች (ክፍል 2)
#ጉዳያችን - ድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሀብት እና ዓለም አቀፍ ህጎች (ክፍል 2) ኢትዮጵያ ካሏት ተፋሰሶች 90 በመቶ የሚሆነው ድንበር ተሻጋሪ ነው። ለመሆኑ ድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሀብት መካከል አለመግባባት ሲፈጠር በዓለም አቀፍ ህግ እንዴት ይዳኛል? በጉዳዩ ላይ፣ የአለም አቀፍ የውሃ ህግ ባለሞያ የሆኑት ከበደ ገርባ(ዶ/ር) የሰጡንን ማብራሪያ ያድምጡ…. ቴዎድሮስ ወርቁ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/y
Oct 211 min read


ጥቅምት 11 2018 - በዓለም ዙሪያ በየቀኑ ከ100,000 በላይ የአየር በረራ እንደሚደረግ ይነገራል።
በኢትዮጵያም በቀን የሚነሳና የሚያርፈው እንዲሁም በኢትዮጵያ የአየር ክልል የሚተላለፈው በረራ ከ600 በላይ ደርሷል። ከዚህ ሁሉ የአየር በረራ ጀርባ ሆነው፣ የበረራውን ደህንነት፣ አዋጭነትና ቅልጥፍና የሚቆጣጠሩት #የአየር_ትራፊክ_ተቆጣጣሪዎች ናቸው። ያለነሱ ከአደጋ ነፃ የሆነ እና የሰመረ የአየር በረራን ማሰብ ከባድ እንደሚሆን ይነገራል። በዚህም ምክንያት የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ሚናን፣የአቪኤሽን ዘርፍ የልብ ምት ነው እንዲባል ያደርገዋል። በሌላ በኩል ስራው ባለው ውጥረትና ጭንቀት ምክንያት በዓለም ዙሪያ ከባድ ከሆኑ የሙያ አይነቶች አንዱ ያደርገዋል። ጥቅምት 10 በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ስራ የሚታሰብበት፣ተገቢው ክብር የሚሰጥበት ዕለት ነው። የኢትዮጵያ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ማህበርም ቀኑን አስቦት ውሏል። በዓለም ዙ
Oct 211 min read


ጥቅምት 10 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#እስራኤል እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ዳግም የአየር ድብደባዋን ፈፀመች ተባለ፡፡ የእስራኤል ጦር ዳግም የአየር ድብደባውን የቀጠለው በጋዛ ደቡባዊ ክፍል እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡ ለደቡባዊ ጋዛው የአየር ድብደባ እስራኤል በሐማስ ትንኮሳ ተፈፅሞብኛ የሚል ክስ ማቅረቧን ተሰምቷል፡፡ የእስራኤል ጦር በሐማስ ፀረ ታንክ ሚሳየል ተተኩሶብኛ ብሏል፡፡ የፍልስጤማውያኑ ታጣቂ ቡድን ሐማስ በፊናው አንዲትም ጥይት አልተኮስኩም ማለቱ ተሰምቷል፡፡ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለጋዛ ሰላም ባቀረቡት ባለ 20 ነጥቦች የሰላም እቅድ ተፋላሚዎቹ በተኩስ አቁም ሰንብተዋል፡፡ ይሁንና እስራኤል እና ሐማስ በተኩስ አቁም መጣስ መካሰሳቸው ተደጋግሟል፡፡ የእስራኤል ጦር ከትናንቱ የጋዛ የአየር ድብደባ በኋላ ወደ ተኩስ አቁሙ ተመልሻለሁ ማለቱ ተሰምቷል፡፡ #ኬንያ የኬንያ የቀድሞ
Oct 202 min read


ጥቅምት 10 2018 - የሀገር ቤት መድሃኒት አቅራቢዎች
በኢትዮጵያ ለጤና ተቋማት ተገዝቶ ከሚከፋፈለው መድሃኒት የሀገር ቤት አቅራቢዎች መጠን እጅግ ቀንሶ እንደነበር ይነገራል፡፡ በቅርቡ በተደረጉ አንዳንድ ማሻሻያዎች ይህንን በመጠኑ ቢስተካከልም አምራቾቹ አሁንም አብዛኛውን ግብዓታቸው ከውጪ ሸማች መሆናቸው የሚጣለውም ቀረጥ ከፍተኛ መሆኑ ከዚህ በላይ እንዳይሰሩ እያደረገ ነው ተባለ፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ምህረት ስዩም የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s 🐦X
Oct 201 min read


ጥቅምት 10 2018 - ህገወጥ አዘዋዋሪዎቹን ለመቆጣጠርና ገንዘቡን ለመያዝ ምን እየተሰራ ነው?
የህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር እና በሰዎች የመነገድ ወንጀል አሁንም ቀጥሏል፡፡ በዚያ ተግባር የሚገለበጠው ገንዘቡም ከፍተኛ ነው፡፡ ህገወጥ አዘዋዋሪዎቹን ለመቆጣጠርና ገንዘቡን ለመያዝ ምን እየተሰራ ነው? ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. የኔነህ ሲሳይ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s 🐦X : https://x.com/shegerfm?s=2
Oct 201 min read


የአፍሪካ አህጉር ነጻ የንግድ ስምምነት ምን ምን እድሎች ይኖሩት ይሆን
ጥቅምት 10 2018 ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉር የንግድ ቀጠና ስምምነት ማድረግ ተከትሎ ለሶስት የአፍሪካ ሀገራት የተለያዩ ምርቶች ልካለች፡፡ በዚህም የመጀመሪያውን ጭነት ወደ ኬንያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ሶማሊያ ስጋ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ቡና የጥራጥሬና የቅባት እህሎችን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ እና በየብስ ትራንስፖርት አማካኝነት ልካለች፡፡ ኢትዮጵያ በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ከአሜሪካ ነፃ የንግድ ስምምነት አጎአ ታግዳ ቆይታለች፡፡ ለመሆኑ ከአጎአ የንግድ እድል ለታገደችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉር ነጻ የንግድ ስምምነቱ ምን ምን እድሎች ይኖሩት ይሆን ስንል የኢኮኖሚ ባለሞያና አማካሪ የሆኑትን አቶ ዳዊት ተሻለ ጠይቀናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ማርታ በቀለ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇
Oct 201 min read


ጥቅምት 10 2018 - ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
የቀድሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት ፕሬዝደንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባጋጠማቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ህይወታቸው ማለፉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተናግሯል።
Oct 201 min read


ጥቅምት 8 2018 "ልዩ ባስ" የሚል መጠርያ ያለው ለሀገር አቋራጭ መንገደኞች ዲጂታል የክፍያ ቴክኖሎጂ ይፋ ተደረገ
አዲስ ፔይ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂ እና እንግዳ ትራቭል ቴክኖሎጂ በጋራ "ልዩ ባስ" የሚል መጠርያ ያለው ለሀገር አቋራጭ መንገደኞች ዲጂታል የክፍያ ቴክኖሎጂ ዛሬ ማስጀመራቸውን ተናገሩ። ይህ ቴክኖሎጂ ደንበኞች ወይም ተጓዦች ባሉበት ቦታ ሆነው ወደየሚፈልጉበት አካባቢ ለመጓዝ "የልዩ ባስ" የሞባይል መተግበሪያ በመጠቀም ቲኬታቸውን በኦንላይን መቁረጥ ይችላሉ ተብሏል። የእንግዳ ትራቭል ቴክኖሎጂ መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ባንተአብ አብይ እንደተናገሩት ቴክኖሎጂውን ስራ ላይ ለማዋል አራት ዓመት እንደፈጀ እና አገልግሎቱን ከደንበኞች በተጨማሪ የግል ባስ ባለንብረቶች ስራቸውን ለማቀላጣፍ መጠቀም የሚችሉበት ነው ብለዋል። ይህንን አገልግሎት ደንበኞች ቅንጡ ስልካቸውን በመጠቀም ወደቲኬት መቁረጫ ቦታ ሳይሄዱ ባሉበት ሆነው መቁረጥ እንደሚችሉም ሰምተናል።
Oct 181 min read


ጥቅምት 8 2018 - በዚህ ተለዋዋጭ የዓለም ስርዓት አፍሪካ እንዴት ተጠቃሚ ትሁን?
በአፍሪካ ሰላምና ደህነት ዙሪያ የሚመክረው የጣና ፎረም የዘንድሮው መድረክ ተለዋዋጭ በሆነው የዓለም ስርዓት አፍሪካ እንዴት ተጠቃሚ ትሁን በሚለው ሀሳብ ዙሪያ ይመክራል ተብሏል። ለተወሰነ ጊዜያት ተቋርጦ የቆየው የጣና ፎረም 11ኛው መድረክ ከመጪው ጥቅምት 14 እስከ 16 እንደሚደረግ አዘጋጆቹ ተናግረዋል፡፡ በዚህ ፎረም ከመላው ዓለም የተወጣጡ የአፍሪካን ቀንድ ሁኔታን የሚከታተሉ ልዩ መልክተኞች፣ የተመድ፣ የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች ቀጠናውን በተመለከተ እንዲወያዩ መጋበዛቸውንም ሰምተናል፡፡ በዚህ በየጊዜው እየተለዋወጠ ባለው የአለም ስርዓት አፍሪካ እንዴት ብትራመድ ተጠቃሚ ያደርጋታል በሚል፣ የአህጉሪቱ መሪዎች፣ ሚኒስትሮች እና የሚመለከታቸው አካላት እንደሚመክሩም ተነግሯል፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ዘሪሁን
Oct 182 min read


ጥቅምት 8 2018 የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት ተቋም ለአንድ ዙር የመድኃኒት ግዥ ለመፈፀም 200 ቀናት እንደሚፈጅበት ተናገረ።
በዚህም ምክንያት መድኃኒት ተገዝቶ ወደ ጤና ተቋማት እስኪደርስ እስከ 4 ወር ሊፈጅ ይችላል ተብሏል። የሠላም ዕጦት ችግር ባለባቸው የኦሮሚያ፣ የአማራና የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል አካባቢዎች ደግሞ ችግሩ ከዚህም እንደሚከፋ ተነግሯል። ተቋሙ የመድኃኒት አገልግሎት አዋጅ እንደ አዲስ ከተሻሻለ በኋላ ለ #መድኃኒት ግዢ የሚወስድብኝ ጊዜ በፊት ከነበረው በግማሽ ቀንሷል ቢልም የክልል የጤና ተቋማት ግን አሁንም በመድኃኒት አቅርቦት መዘግየት እየተፈተንን ነው ብለዋል። ይህ የተባለው በ7ኛው ብሔራዊ የመድኃኒት አቅርቦት ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ነው። በጉባኤው ላይ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ወደ ኃላፊነት የመጡ ሰሞን በህዝብ እንደራሴዎች በኩል የሚቀርብላቸው ጥያቄ ሁሉ የመድኃኒት አቅርቦት እንደነበር ተናግረዋል። በዚህም ማህበረሰቡ በመድኃኒት አ
Oct 181 min read


ጥቅምት 7 2018 - ኢትዮጵያ በተለያዩ ተቋማት ለሚዘረጉ መሠረተ ልማቶች እስከ አሁን ማስተር ፕላን እንደሌላት ተነግሯል
አሁን ማስተር ፕላኑን የማዘጋጀቱ ስራ እንደተጀመረም ሠምተናል። ከመሰረተ ልማት ዘርጋታ ጋር በተገናኘ እያጋጣሙ ያሉ ችግሮች አንዱ መነሻ ዘርፉን የተመለከተ ማስተር ፕላን አለመኖር እንደሆነ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ተናግሯል። የትኛው መሰረተ ልማት በየት በኩል ይለፍ፣ የትኛውስ ምን ቦታ አገልግሎት ይስጥ? የሚለው በዚህ ፕላን የተደገፈ አይደለም ሲሉ፤ የሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ ኢትዮጵያ በዴቻ ተናግረዋል። አሁን ይህን ማስተር ፕላን ለማዘጋጀት ስራዎች ተጀምረዋል ያሉን አቶ ኢትዮጵያ መሰረተ ልማቶቹን የሚዘረጉ ተቋማት በስራው መሳተፋቸውንም ነግረውናል። ተቋማቱ ማስተር ፕላኑን በማዘጋጀቱ ሂደት ከመሳተፍ ባሻገር ሃብት እና ባለሞያ ማዋጣታቸውንም ጠቅሰዋል። በስራው እየተሳተፉ ያሉ ሞያተኞች ማስተር ፕላኑን
Oct 171 min read


ጥቅምት 7 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ሕንድ የሕንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሕንድ የሩሲያን የነዳጅ ዘይት መግዛት እንደምታቆም ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራሞዲ ማረጋገጫ ሰጥተውኛ ስለማለታቸው የምናውቀው ነገር የለም አለ፡፡ ትራምፕ ከትናንት በስቲያ ሕንድ የሩሲያን ነዳጅ መግዛት እንደምታቆም ማረጋገጫ አግኝቻቸው ሲሉ መናገራቸውን ቢቢሲ አስታውሷል፡፡ የህንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ቃል አቀባይ በትራምፕ እና በናሬንድራ ሞዲ መካከል ይህን መሰል ንግግር ስለመደረጉ አላውቅም ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ በጉዳዩ ላይ ከዚህ ቀደም ንግግረግ ቢደረግም ነዳጁ ግዢውን ስለማቆም የተደረሰ መደምደሚያ የለም ብለዋል፡፡ የህንድ መንግስት በዚህ ጉዳይ ባወጣው መግለጫ እኛ የምናስቀድመው የአገሪቱን ፍላጎት እና የኢነርጂ ዋስትና ነው ማለቱ ተጠቅሷል፡፡ ሕንድ ከቻይና በመቀ
Oct 172 min read


ጥቅምት 7 2018 - በአዲስ አበባ አንድም የቢንጎ ማጫወቻም ሆነ የአረቄ መሸጫ ቤት መኖር የለበትም ተባለ፡፡
ከዚህ በፊትም እነዚህ ቤቶች ከከተማው አንዲጠፋ መመሪያ ተሰጥቶ ነበር፤ ግን አሁንም ድረስ ቤቶቹ መኖራቸውና በስራ ላይ መሆናቸው ታውቋል ተብሏል፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥም የአዲስ አበባ ከተማ ከ #ቢንጎ ማጫወቻ እና የ #አረቄ መሸጫ ቤት ነፃ እንዲሆን ይደረጋል መባሉን ሰምተናል፡፡ ይህንን ያለው የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ነው፡፡ ቤቶቹ እንዳይኖሩ ይደረጋል ያለው ተቋሙ ምክንያቴም ቤቶቹ የወንጀል ምክንያት በመሆናቸው ነው ብሏል፡፡ የቢሮው ሀላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ የቢንጎ ማጫወቻ እና በየመንደሩ ያሉ አረቄ ቤቶች የከተማው ወንጀል መፈልፈያ ቦታዎች ናቸው ብለዋል፡፡ ይህንን ማስፈፀም ያልቻሉ ሀላፊዎችም በቦታቸው አይቀጥሉም ብለዋል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ገዛ ጌታሁን የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website
Oct 171 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page








