top of page


በሀገራዊ ምክክሩ አጀንዳ ሆኖ ብሔራዊ መግባባት ይፈጠርበት ዘንድ ከቀረቡ አጀንዳዎች መከካከል የኢትዮጵያን የዘመን አቆጣጠር ይመለከታል፡፡
ታህሳስ 23/2018 በሀገራዊ ምክክሩ አጀንዳ ሆኖ ብሔራዊ መግባባት ይፈጠርበት ዘንድ ከቀረቡ አጀንዳዎች መከካከል የኢትዮጵያን የዘመን አቆጣጠር ይመለከታል፡፡ በጉዳዩ ላይ ከዚህ ቀደም ጥናትና ምርምር ያደረጉ ምሁር እንደሚሉት የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ካሌንደር ከ3,000 ዓመት በፊት ሲጀመር የክርስትናም ሆነ የእስልምና እምነት ወደ ኢትዮጵያ አልገባም ነበር፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ያሬድ እንዳሻው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 Facebook፡ https://web.facebook.
Jan 11 min read


እስራኤል ለሶማሊላንድ እውቅና መስጠቷ በአፍሪካ ቀንድ የዲፕሎማሲ
ታህሳስ 23/2018 እስራኤል ለሶማሊላንድ እውቅና መስጠቷ በአፍሪካ ቀንድ የዲፕሎማሲ ስዕሉን እንደሚቀይረው ይታመናል፡፡ ምዕራባውያን የተለያዩ የአረብ ሀገራትና ግብፅም እጃቸውን የሚያስገቡበት የአፍሪካ ቀንድ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ ጥቅሟን ለማስጠበቅ ማድረግ ያለባት ምንድን ነው? ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ቴዎድሮስ ወርቁ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1 WhatsApp : https://whatsapp.com/cha
Jan 11 min read


በጥጥ ምርት ላይ የተጣለው ተጨማሪ እሴት ታክስ በሀገር ቤት የሚመረተው ጥጥ ዋጋው እንዲንር አድርጎታል ተባለ፡፡
ታህሳስ 22/2018 በጥጥ ምርት ላይ የተጣለው ተጨማሪ እሴት ታክስ በሀገር ቤት የሚመረተው ጥጥ ዋጋው እንዲንር አድርጎታል ተባለ፡፡ በዚህም ምንክያት ምርቱን ገበያውን ለመምራት እየተቸገረ መሆኑን የኢትዮጵያ ጥጥ ማህበር ነግሮናል፡፡ ሀገር ውስጥ የሚመረተውን የጥጥ ምርት ከውጭ ከሚገባው በዋጋ በኪሎ የ30 ብር በኩንታል ደግሞ የ3,000 ብር ጭማሪ ማሳየቱን ተነግሯል፡፡ በዚህ ምክንያት የሀገር ውስጥ ምርት ገበያው ላይ እንዲወደድና አምራቾችም የሃገር ውስጥ ምርቱን በመወደዱ ምክንያት ቀዳሚ ምርጫቸው እያደረጉት አይደለም ሲል የኢትዮጵያ ጥጥ ማህበር ነግሮናል፡፡ የኢትዮጵያ ጥጥ ማህበር ዋና ዳይሬክተር ፀጋዬ አበበ እንዳሉት ለሀገር ውስጥ የሚያስፈልግ የጥጥ ምርት በበጀት አመቱ በበቂ ሁኔታ ቢመረትም ገዥ ግን እየተገኘ አይደለም፡፡ ባለፈው
Dec 31, 20251 min read


የአካባቢ ጉዳትን የሚቀነሱ ፈጠራ ላይ የተሰማሩ ወጣቶች ፈጠራዎቻቸውን እንዲያሳድጉ የሚያስችል ስራ እየተሰራ መሆኑንን ሪች ፎር ቼንጅ ተናገረ፡፡
ታህሳስ 22/2018 የአካባቢ ጉዳትን የሚቀነሱ ፈጠራ ላይ የተሰማሩ ወጣቶች ፈጠራዎቻቸውን እንዲያሳድጉ የሚያስችል ስራ እየተሰራ መሆኑንን ሪች ፎር ቼንጅ ተናገረ፡፡ 34 ስራ ፈጣሪዎችም ፈጠራቸውን ለኢንዱስትሪዎችና ለባለሀብቶች እንዲያስተዋውቁ እድል ተመቻችቶላቸዋል ተብሏል፡፡ ከመኖሪያ ቤትና ከተለያዩ ተቋማት እንዲሁም ከፋብሪካዎች የሚወጡና አካባቢን የሚበክሉ ቁሶችን እና ፈሳሾችን በድጋሚ ጥቅም ላይ እያዋልነው ሲሉ ስራ ፈጣሪዎች ነግረውናል፡፡ አገልግሎታቸውን ጨርሰዋል ጥቅም መስጠት አቁሟል ከተባሉት መካከል እና በድጋሚ ጥቅም ላይ ከሚውሉት መካከል ፕላስቲኮች፣ ሳንቡሳ እና ቺብስ ከተጠበሰ በኋላ የሚቀረው የምግብ ዘይት እና የመኪናና የተለያዩ ሞባይል እና ላፕቶፖች ባትሪዎች ይገኙበታል፡፡ ከፕላስቲኮቹ ለመንገድ ንጣፍ የሚሆኑ ቴራሶች ከዘ
Dec 31, 20251 min read


አንድ ጊዜ ብቻ አገልግሎት ሰጥተው የሚጣሉ ስስ ፌስታሎችን መጠቀም ከአንድ ወር በኋላ ይከላከላል፡፡
ታህሳስ 22/2018 አንድ ጊዜ ብቻ አገልግሎት ሰጥተው የሚጣሉ ስስ ፌስታሎችን መጠቀም ከአንድ ወር በኋላ ይከላከላል፡፡ አምራቾች በበኩላቸው አሁንም በቂ የሽግግር ጊዜ አላገኝም፣ ስስ ፌስታሎቹንም ቢሆን ልክ እንደ የውሃ መጠጫ ኮዳዎች አገልግሎት ከሰጡ በኋላ ተሰብስበው መልሶ ጥቅም እንዲሰጡ ማድረግ ይቻላል ይላሉ፡፡ በጉዳዩ ላይ የአካባቢው ጥበቃ ባለስልጣንን ጠይቀናል፡፡ ድጋሚ ጥቅም ላይ መዋል ቢችሉም ለመሰብሰብ አስቸጋሪ ናቸው በቀላሉ በተለያየ ምክንያትም በየቦታው ተበታትነው አካባቢ ላይ ከፍተኛ የሆነ ችግር ያስከትላል ተብሏል፡፡ ከዚህ ቀደም በዚህ ፕላስቲክ ምርት ላይ የተሰማሩ አምራቾች የሚያስከትለውን ጉዳት በመረዳት ከአንድ ጊዜ በላይ አገልግሎት መስጠት ወደሚችሉ የስራ ዘርፎች ፊታቸውን ቢያዞሩ የተሻለ ነው ሲል የአካባቢ ጥበቃ ባለስ
Dec 31, 20251 min read


''ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታገኝ የተዋዋለቻችው ሰምምነቶች ሳይተገበሩ፤ በሚዲያ ብቻ እየተወራ የሚኖረው እሰከመቼ ነው?'' የም/ቤት አባል
ታህሳስ 21/2018 ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታገኝ ከሶማሊያ፣ ከሶማሊላንድ ጋር የተዋዋለቻችው ሰምምነቶች ሳይተገበሩ፤ አገሪቱም የባህርበር ሳታገኝ በሚዲያ ብቻ እየተወራ የሚኖረው እሰከመቼ ነው? የሚል ጥያቄ ከምክር ቤት አባል ቀረበ፡፡ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ በበኩላቸው የባህር በር ጥያቄ የረጅም ጊዜ እይታ ያስፈልገዋል ፣ የማሳመን ስራ እየተሰራ ነው ሲሉ መልሰዋል፡፡ የምክርቤት አባሉ አበባው ደስአለው(ዶ/ር) የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ አጅንዳ ብቻ ሆኖ የሚቆየው እስከመቼ ነው ብለው የጠየቁት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) ዛሬ በፓርላማ ተገኝተው በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከምክርቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ በሰጡበት ወቅት ነው፡፡ የምክርቤት አባሉ በፈረንጆቹ 2024 ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ እና በሶማሊላንዱ የወቅ
Dec 30, 20252 min read


ግብርናው ዘርፍ የብድር አቅርቦት ከማያገኙ ዘርፎች መካከል ቀዳሚው ነው ተባለ፡፡
ታህሳስ 21/2018 ግብርናው ዘርፍ የብድር አቅርቦት ከማያገኙ ዘርፎች መካከል ቀዳሚው ነው ተባለ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ግብርናው የብድር አቅርቦት ከፋይናንስ ተቋማት እንዳያገኝ ከሚያደርጉት ምክንያቶች ዋነኛው በዝናብ ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ነው ይላሉ ያነጋገርናቸው የግብርና ኦኮኖሚ ባለሙያ፡፡ በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የግብርና ኢኮኖሚስት ምርምር ዳይሬክተር እና ተመራማሪ ታደለ ማሞ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚቀርበው ብድር ውስጥ ግብርናው የሚያገኘው 10 በመቶ ብቻ ነው፡፡ ከ10 በመቶ ብድሩ መካከል አብዛኛው ብድር በግብርና ምርት ማቀነባበር ስራ ለተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች የሚቀርብ ነው ተብሏል፡፡ ገበሬው አሁንም ብድር እያገኘ አይደለም ብለዋል፡፡ ግብርናው ለሺህ አመታት በስፋት የሚያውቀው ቴክኖሎጂ በሬና ሞፈር ነው ፣ ገበሬውም
Dec 30, 20251 min read


ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲው የዋጋ ግሽበቱ ነጠላ ድጅት እስኪደርስ ድረስ ይቀጥላል ተባለ፡፡
ታህሳስ 21/2018 ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲው የዋጋ ግሽበቱ ነጠላ ድጅት እስኪደርስ ድረስ ይቀጥላል ተባለ፡፡ ይህም የባንኮች የብድር አሰጣጥ ላይ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ተጥሎ የቆየው ገደብ እንደሚቀጥል ያሳያል፡፡ ባንኮች ለአስቀማጮች ይሰጡት የነበረው የ7 በመቶ ወለድ በብሔራዊ ባንክ የተወሰነ እንደነበር ይታወሳል፡፡ አሁን ባንኮች እና ቆጣቢዎች እንዲደራደሩበት ወይም ለገበያው እንዲተው የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ወስኗል፡፡ በብሔራዊ ባንክ ስር የተቋቋመ የገንዘብ ፖሊስ ኮሚቴ ዛሬ አምስተኛ ዙር ስብሰባውን አካሂዶ መግለጫ አውጥቷል፡፡ ለዛሬ ስብሰባውም የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው የተለያዩ 4 ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ የብሄራዊ ባንክ የ15 በመቶ የፖሊሲ ተመን ባለበት እንዲቀጥል የሚለው የመጀመሪያው ውሳኔ ነው፡፡ በሌላ በኩል ኮሚቴው በባንኮች ያለው የጥሬ ገንዘብ ክ
Dec 30, 20252 min read


ልዩ መለያ የሌላቸው ነባር ደረሰኞች ከፊታችን ጥር በኋላ ከአገልግሎት ውጪ እንደሚሆኑ የገቢዎች ሚ/ር ተናገረ፡፡
ታህሳስ 21/2018 ልዩ መለያ ወይም ‘’ባር ኮድ’’ የሌላቸው ነባር ደረሰኞች ከፊታችን ጥር ወር በኋላ ሙሉ ለሙሉ ከአገልግሎት ውጪ እንደሚሆኑ የገቢዎች ሚኒስቴር ተናገረ፡፡ ከካሽ ሬጅስተር የሚወጡ ደረሰኞችንም ወደ ኤሌክትሮኒክ መላ ለመቀየር ስራ ተጀምሯል ብሏል። ከደረሰኝ መስጠት እና መቀበል ጋር የተገናኙ ሰፋ ያሉ ችግሮች እንደሚታዩ የገቢዎች ሚኒስቴር ተናግሯል። ሃሰተኛ ደረሰኝ ለመንግስት ማቅረብ ፤በታክስ ከፋዮች ስም ሃሰተኛ ደረሰኝ ማዘጋጀትና ያልተከፈለ የመንግስት ዕዳ አለብህ በማለት ፤ ሰዎች ላይ ያልተገባ ጫና መፍጠር ከችግሮቹ መካከል እንደሆኑ በሚኒስቴሩ የታክስ ማጭበርበር ምርመራ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሢሣይ ገዙ ጠቅሰዋል። ችግሮቹን ለማስቀረት ደረሰኞች ልዩ መለያ ወይም ባር ኮድ እንዲኖራቸው ተደርገው እየታተሙ ነው ብ
Dec 30, 20251 min read


ጉዳያችን - የመቀንጨር ችግር እና መዘዙ
ታህሳስ 20/2018 ጉዳያችን - የመቀንጨር ችግር እና መዘዙ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የዞሎጂ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ሀብቴ ጀቤሳ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ ትልቁ ችግር ስለሆነውና በተመጣጠነ ምግብ እጥረት ምክንያት ስለሚመጣ የመቀንጨር ችግርና መዘዙ በተመለከተ የሰጡንን ማብራሪያ ያድምጡ…. ቴዎድሮስ ወርቁ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1 WhatsApp : https://whatsapp.com/channel/00
Dec 29, 20251 min read


ወደ ህክምና ተቋማት የአጥንት ህክምና ፈልገው ከሚመጡ ተገልጋዮች አብዛኛዎቹ በትራፊክ አደጋ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው ናቸው ተባለ፡፡
ታህሳስ 20/2018 ወደ ህክምና ተቋማት የአጥንት ህክምና ፈልገው ከሚመጡ ተገልጋዮች አብዛኛዎቹ በትራፊክ አደጋ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው ናቸው ተባለ፡፡ የትራፊክ አደጋ አሁንም ከሌሎች ጉዳቶች ይልቅ ለአጥንትና መገጣጠሚያ ችግሮች ቀዳሚ መንስኤ መሆኑ ተነግሯል፡፡ በሌላ በኩል ጉዳቱ ከባድ ቢሆንም የህክምና ወጪው ከፍተኛ መሆንና ህክምናው በሁሉም የመንግስት የጤና ተቋማት አለመገኘቱም ተጨማሪ ጫና መፍጠሩንም የኢትዮጵያ የአጥንት ቀዶ ህክምና ማህበር ተናግሯል፡፡ የማህበሩ ፕሬዝዳንትና የአጥንት ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስቱ ዶ/ር ኤፍሬም ገብረ ሐና እንደሚናገሩት ከአጥንት ጉዳት ጋር በተያያዘ አብዛኛውን ቁጥር የሚይዘው የትራፊክ አደጋ ነው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ እስካሁን የጉዳት መረጃ መመዝገቢያ ቋት የሌላት በመሆኑም በትራፊክ አደጋ ምክንያት የ
Dec 29, 20251 min read


ኢትዮ ቴሌኮም ለደንበኞቹ የአገልግሎት ታሪፍ ማሻሻሉ ተሰማ።
ታህሳስ 20/2018 ኢትዮ ቴሌኮም ለደንበኞቹ የአገልግሎት ታሪፍ ማሻሻሉ ተሰማ። ከባንያው በተለያዩ አገልግሎቶች ላይ ያደረገው አማካይ የ ዋጋ ማሻሻያ የ23% በመቶ እንደሆነ ሰምተናል። ኢትዮ ቴሌኮም ይህን የታሪፍ አገልግሎት ማሻሻያ ያደረኩት፤ ተለዋዋጭ የ ማክሮ ኢኮኖሚ ፤ የካፒታል እና የስራ ማስኬጃ ወጭዎች ከፍ በማለቱ ነው ብሏል። ከዚህም ባለፈ ኩባንያው፤ የአገልግሎት ጥራትን ለማስጠበቅ የታሪፍ ማሻሻያ አድርጌያለሁ ብሏል። በዚህም መሰረት የ ዋጋ ማሻሻያ ከተደረገባቸው አማካይ 23 በመቶ ውስጥ የቴሌብር ልዩ ስጦታ ጥቅል የ10% ቅናሽ ወደ 20% ከፍ ብሏል። ኩባንያው ካሉት አብዛኛው ጥቅሎች ላይ 38 የተለያዩ ጥቅሎች ላይ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አላደረኩም ብሏል። ከዚህ ውስጥም የ1 ብር፣ የ2 ብር፣ የ5 ብር እና የ1 ሰዓት ጥቅሎች ባሉበት እን
Dec 29, 20251 min read


ቭላድሚር ፑቲን ዩክሬይን የሰላሙን መንገድ ብትመርጥ ይሻላታል ሲሉ በድጋሚ አስጠነቀቁ፡፡
ታህሳስ 20/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #ሩሲያ የሩሲያው ፕሬዘዳንት ቭላድሚር ፑቲን ዩክሬይን የሰላሙን መንገድ ብትመርጥ ይሻላታል ሲሉ በድጋሚ አስጠነቀቁ፡፡ የሩሲያው ታስ የወሬ ድርጅት የፑቲንን የከትናንት በስቲያ ማስጠንቀቂያ እወቁት ማለቱን የፃፈው ሬውተርስ ነው፡፡ የሩሲያ ጦር ሰሞኑን በዩክሬይን ላይ ሁለንተናዊ ጥቃቱን ማክፈቱ ይነገራል፡፡ ፑቲን የድጋሚ ማስጠንቀቂያቸው የተሰማው የሩሲያ ጦር በቅርቡ በዳኔስክ እና በዛፓሮዢያ ግዛቶች በያዛቸው ከተሞች እና አካባቢዎች ጉብኝት ያደረጉ የጦር አለቆችን ባነጋገሩበት አጋጣሚ ነው ተብሏል፡፡ የሩሲያው ፕሬዘዳንት ዩክሬይን ሰላሙን ካልመረጠች ለጦርነቱ ያስቀመጥነውን ግብ በጦር ሀይል ማሳካታችን አይቀርም ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ ጦርነቱ ያለ ሁነኛ መፍትሄ ወደ 4ኛ ዓመቱ እየታቀረበ ነው፡
Dec 29, 20252 min read


የባዮ ቴክሎኖጂ ምርምር የተደረገባቸው የሰብል ምርቶች ላይ የሚደረገው ክትትል ምን መሳይ ነው?
ታህሳስ 20/2018 በባዮ ቴክሎኖጂ ምርምር የተደረገባቸው የሰብል ዝርያዎች ገበሬው ጋር እየደረሱ ነው፡፡ የዘረመል ምህንድስናን ጨምሮ ሌሎች የባዮ ቴክሎኖጂ ምርምር የተደረገባቸው የሰብል ምርቶች ላይ የሚደረገው ክትትል ምን መሳይ ነው? ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. በረከት አካሉ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1 WhatsApp : https://whatsapp.com/channel/0029VaAOnG9J3juypE0M4G1O X
Dec 29, 20251 min read


ምርትና አገልግሎት ያላቸውን፣ ሸማቹንና አሻሻጭን የሚያገናኝ የሞባይል መተግበሪያ በይፉ ስራ መጀመሩ ተነገረ።
ታህሳስ 18/2018 ምርትና አገልግሎት ያላቸውን፣ ሸማቹንና አሻሻጭን የሚያገናኝ የሞባይል መተግበሪያ በይፉ ስራ መጀመሩ ተነገረ። መተግበሪያው "ዳንቴል" ይባላል። በዳንቴል ሶፍትዌር የተዘጋጀው "ዳንቴል" የሞባይል መተግበሪያ አምራቾች ምርታቸውን፣ አገልገሎት አቅራቢዎች ያላቸውን አገልግሎት ሙሉ መረጃ የሚያስቀምጡበት፣ መረጃውን ደግሞ በየራሳቸው የማህበራዊ ትስስር ገፆች የሚያጋሩና ሽያጭ እንዲከናወን የሚያደረጉ ደግሞ የኮሚሽን ክፍያ እንዲያገኙ የሚያስችል ስርዓት ይዞ የመጣ ነው። ይህም ለሸማቹ ገበያ ወጥቼ የት ምን አገኛለሁ የሚለውን የሚያቀልል፣ ለአምራቹም ሰፊ የገበያ እድል የሚፈጥር፣ በተለይ በሽያጭ ስራ ገቢ ለማግኘት ለሚፈልጉ ስልካቸውን ተጠቅመው ገቢ እንዲያገኙ የሚያስች እንደሆነ የድርጅቱ ሀላፊዎች በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል። መተግበ
Dec 27, 20251 min read


እስራኤል ለሶማሌላንድ ይፋዊ የነፃ አገርነት እውቅና መስጠቷ ሶማሊያን በእጅጉ አስቆጣት፡፡
ታህሳስ 18/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #እስራኤል እስራኤል ለሶማሌላንድ ይፋዊ የነፃ አገርነት እውቅና መስጠቷ ሶማሊያን በእጅጉ አስቆጣት፡፡ ሞቃዲሾ የእስራኤልን እርምጃ አጥብቃ ማውገዟን ዘ ኒው አረብ ፅፏል፡፡ ከሶማሊያ በተጓዳኝ ግብፅ ፣ ቱርክ እና ጂቡቲም እስራኤል ለሶማሌላንድ የነፃ አገርነት እውቅና መስጠቷን ኮንነውታል ተብሏል፡፡ አገሮቹ የሶማሊያ ሉአላዊነት እና የግዛት አንድነት እንዲከበር ድጋፋቸውን እንደሚቀጥሉ እወቁልን ብለዋል፡፡ ሶማሌላንድ ራሷን ከተቀረችው ሶማሊያ ከነጠለች 34 ዓመታት ሆኗታል፡፡ አለም አቀፋዊ እውቅና ባይኖራትም ከሶማሊያ በተሻለ የተረጋጋች እንደሆነች ይነገርላታል፡፡ በነፃ አገርነት ይፋዊ እውቅና ስታገኝ የእስራኤል የመጀመሪያው ሆኗል፡፡ ሶማሊያ እና አጋሮቿ ሌሎችም የእስራኤልን ፈለግ እንዳይከተሉ መስጋታቸው ተጠቅሷል፡፡
Dec 27, 20252 min read


በዚህ ዓመት ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ በትግራይ ማካሄድ ካልተቻለ በክልሉ ያለው ቀውስ ሊባባስ እንደሚችል የፖለቲካ ፓርቲዎች ተናገሩ፡፡
ታህሳስ 17/2018 በዚህ ዓመት ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ በትግራይ ማካሄድ ካልተቻለ በክልሉ ያለው ቀውስ ሊባባስ እንደሚችል የፖለቲካ ፓርቲዎች ተናገሩ፡፡ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች እንዳሉት በትግራይ ክልል ያለውን የመብት ጥሰት እና መሰል ችግሮችን ለመፍታት በህዝብ የተመረጠ መንግስት ያስፈልጋል፡፡ ለምርጫ አስቻይ ሁኔታ አለ ወይስ የለም የሚለውን በተመለከተ ጊዜያዊ አስተዳደር በቅርቡ መግለጫ እሰጣለሁ ብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ያሬድ እንዳሻው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio
Dec 26, 20251 min read
የህፃናትን መብት ለማስጠበቅ
ታህሳስ 17/2018 የህፃናትን መብት ለማስጠበቅና ለመብት ጥሰት በተጋለጡ ጊዜም የሚያስፈልጋቸውን እገዛ እንዲያደርግ መንግስት በፈረማቸው አለም አቀፍ ስምምነቶች የሚገደድ ቢሆንም በበቂ ሁኔታ ሃላፊነቱን እየተወጣ አይደለም ተብሏል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከግጭቶችም ጋር ተያይዞ በብዛት ህፃናት ለተለያየ የመብት ጥሰቶች እየደረሰባቸው መሆኑ ይነገራል፡፡ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩል ህፃናት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከል እና ፍትህ እንዲያገኙ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ነግሮናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ፋሲካ ሙሉወርቅ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhc
Dec 26, 20251 min read


የኢትዮዽያ የሎጅስቲክስ ስርዓት እና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና
ታህሳስ 17/2018 የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የሀገራትን የምርት ልውውጥ ለማሳደግ ኢኮኖሚያቸውን ይደግፋል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ ኢትዮዽያም በዚሁ መስመር ወደ ቀጠናው የንግድ እና ጭነት ስራ ጀምራለች። ሆኖም የሎጀቲክስ ስራውም ጎን ለጎን ሊሰራበት እንደሚገባ ይመከራል። ኢትዮጵያ ከ 90 በመቶ በላይ ጭነቶችን በመኪና ታጓጉዛለች፡፡ በቀጠናው ሀገራት ጋር የሚኖራትን የንግድ ግንኙነት በባቡር እና በሌሎች መንገዶች ብታቀላጥፍ ደግሞ ሎጀስቲክሱ ይበልጥ ውጤት ያመጣል። ገቢ ወጭ እቃዎችን ከአንድ ላኪ ሐገር ወደ ኢትዮዽያ በባሕር፣ በአየር፣ በመሬት ወይም በባቡር ማቀላጠፍ የሎጀስቲክስ ዋና ዋና ስራዎችን ያቀላል። በተለይ በኢትዮጵያ ከገቢና ወጭ ጭነት ጋር በተገናኘ ፤ የመሀል ሐገር ኢኮኖሚው የተሻለ ውጤት እንዲቆጠርበት ፤የጭነት መኪኖች የመ
Dec 26, 20251 min read


የ1997 እና የ2005 ዓ.ም የጋራ መኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን የሚቆጥቡ የማህበረሰብ ክፍሎች
ታህሳስ 16/2018 የጋራ መኖሪያ ቤት ለማግኘት ተመዝግበው የሚጠባበቁ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አሉ፡፡ እጣ ፈንታችን ምንድነው? ሲሉም ይጠይቃሉ፡፡ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በበኩሉ በተለያየ መልኩ እየተተገበሩ ባሉ ፕሮግራሞች ቤት የማግኘት እድል አላቸው ብሏል፡፡ እነዚህ የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን የሚቆጥቡ የማህበረሰብ ክፍሎች የ1997 እና የ2005 ዓ.ም መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በዚህ ጉዳይ ከዚህ ቀደም የሚመለከታቸው የሚባሉ የስራ ሀላፊዎችን መጠየቃቸውና መፍትሄ ማግኘት እንዳልቻሉም ያስረዳሉ፡፡ ነዋሪዎቹ ቁጠባቸውን እንዳላቋረጡ እና አሁን የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር እያስገነባ ከሚገኘው ቤት የማግኘት እድል ይኖረናል ወይ ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ የቤቶች ልማትና አስ
Dec 25, 20251 min read


ዳሽን ባንክ በ2017 በጀት ዓመት 6.7 ቢሊየን ብር አጠቃላይ ትርፍ አግኝቻለሁ አለ።
ታህሳስ 16/2018 ዳሽን ባንክ በ2017 በጀት ዓመት 6.7 ቢሊየን ብር አጠቃላይ ትርፍ አግኝቻለሁ አለ። አጠቃላይ ሃብቴም ከ254 ቢሊየን ብር ተሻግሯል ብሏል። የባንኩ ባለ አክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ በሚሊኒየም አዳራሽ ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት ሲነገር እንደሰማነው የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ ከ202 ቢሊየን ብር በላይ የደረሰ ሲሆን ካፒታሉም 14 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ሆኗል። በበጀቱ ዓመቱ 1 ነጥብ 12 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የውጭ ምንዛሪ ማግኘቱን የጠቀሰው ዳሽን ባንክ አጠቃላይ የብድር ክምችት መጠኑ በሂሳብ ዓመቱ 134 ቢሊየን ብር መድረሱን አክሏል። አመቱ በአለም አቀፍ ደረጃ ተለዋዋጭ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የታየበት እንደነበር የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር አቶ ዱላ መኮንን ተናግረዋል። ዳሽን ባንክ ግን በኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን
Dec 25, 20251 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

