ሀገራዊ ምክክሩ የትግራይ ነገ የተረጋጋ እንዲሆን የክልሉ ህዝብ የድርሻውን የሚወጣበት መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተናገረ።
- 10 hours ago
- 1 min read
መጋቢት 23/2018
ሀገራዊ ምክክሩ የትግራይ ነገ የተረጋጋ እንዲሆን የክልሉ ህዝብ የድርሻውን የሚወጣበት መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተናገረ።
ለበርካታ ጊዜያት ሊከናወን ቀጠሮ ሲያዝ ሲራዘም የነበረው የትግራይ ክልል አጀንዳ የማሰባሰብ ምክክር ዛሬ በአዲስ አበባ ተጀምሯል።
ከዛሬ መጋቢት 23 እስከ አርብ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ በሚካሄደው የመጀመሪያውን ዙር የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረክ ከክልሉ የመጡና በአዲስ አበባ ያሉ የትግራይ ተወላጆች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራት፣ የሃይማኖት ተወካዮች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻዎች እየተሳተፉ ነው።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ትግራይ የሌለችበት ምክክር ግቡን የማይመታ በመሆኑ ከብዙ ጥረቶች በኋላ በአዲስ አበባ እንድንመካከር ሆኗል ብለዋል።
ተሳታፊዎች በነፃነት ሃሳባቸውን እንዲገልፁ የጠየቁት ዋና ኮሚሽነሩ ምክክሩ የነገዋ ትግራይ የተረጋጋች እንድትሆን የድርሻችሁን የምትወጡበት ነው ሲሉም አስረድተዋል።
በመድረኩ ሃሳባቸውን የሰጡ አብዛኞቹ ተሳታፊዎች የትግራይ ህዝብ በገዢዎች ምክንያት ስቃይ ውስጥ ነው፤ ወረድ ብላችሁ እንድታነጋግሯቸው እንፈልጋለን፤ ችግራችን ብዙ ነው ተናግረን አንዘልቀውም የፌድራል መንግስቱ በደላችንን ቢመለከት የሚሉ ሃሳቦችን አንስተዋል።
የምክክር ኮሚሽኑ በበኩሉ ከዚህ በኋላ በክልሉ አስቻይ ሁኔታ ካለ ለምክክሩ ዝግጁ ነኝ ብሏል።
በተጀምረው የምክክር ቀናት አጀንዳዎች ከተሰበሰቡ በኋላ ከተወያዮች መካከል በዋናው ሃገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚሳተፉ የትግራይ ተወካዮች ይለያሉ ሲባል ሰምተናል።
ፋሲካ ሙሉውርቅ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7

