top of page

በባህር፣ በየብስ እና በአየር ተጓጉዘው የሚመጡ እቃዎችን ከጉምሩክ መጋዘን በሚያወጡበት የጊዜ ገደብ ላይ ለውጥ ተደርጓል።

  • Mar 30
  • 1 min read

መጋቢት 21/2018


በአዲሱ የጉምሩክ አዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ ላይ አስመጪዎች በባህር፣ በየብስ እና በአየር ተጓጉዘው የሚመጡ እቃዎችን ከጉምሩክ መጋዘን በሚያወጡበት የጊዜ ገደብ ላይ ለውጥ ተደርጓል።


በባህር እና በየብስ ተጓጉዘው የሚመጡ እቃዎችን ከጉምሩክ መጋዘን ማውጫ ጊዜው ከ15 ቀን ወደ 45 ቀን፤በአየር ተጓጉዘው የሚመጡ እቃዎችን ማውጫ ጊዜ ገደቡ ከ10 ቀን ወደ 30 ቀን ይሻሻላል ተብሏል።


ይህንን የፈቀደው ባለፈው ሳምንት እንደገና ተሻሽሎ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የቀረበው የጉምሩክ አዋጅ ነው፡፡


በአንድ ዲክላራሲዮን ወደ አገር ውስጥ የገቡ እቃዎች በአንድነት መለቀቅ እንዳለባቸውም አሁን በስራ ላይ ያለው አዋጅ ያስገድዳል።


ይህ ግን ብዙ ጊዜ አስመጪው በገንዘብ እጥረት ምክንያት በእቃዎች ላይ ሊከፍል የሚገባውን ቀረጥ እና ታክስ በአንድነት መክፈል በማይችልበት ጊዜ ኮሚሽኑ እቃዎች ተከፋፍለው ሊለቀቁ እንዲችሉ ሊፈቅድ የሚችል አንቀጽ ታክሎበት ሊወጣ መሆኑም ተነግሯል።


ማሻሻያው ሌሎች ነጥቦችንም በስሩ የያዘ ሲሆን የማሻሻያውን መልካም ጎንና ስጋቱን በተመለከተ

የዘርፉን ባለሙያ ጠይቀናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….


ቴዎድሮስ ወርቁ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page