top of page

ከቴምር ፕሮፐርቲ መኖሪያ ቤት የሚገዙ ደንበኞች ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ልዩ የሼባ ማይልስ ስጦታ የሚያገኙበት ዕድል መዘጋጀቱ ተነገረ።

  • Apr 2
  • 1 min read

መጋቢት 24/2018


ከቴምር ፕሮፐርቲ መኖሪያ ቤት የሚገዙ ደንበኞች ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ልዩ የሼባ ማይልስ ስጦታ የሚያገኙበት ዕድል መዘጋጀቱ ተነገረ።


የኢትዮጵያ አየር መንገድ የደንበኞች ሎያሊቲ ክፍል ማናጀር አቶ ሰለሞን መኮንን እና የቴምር ፕሮፐርቲ የኢቨንት እና ፕሮሞሽን ዳይሬክተር አቶ ዑስማን መሀመድ ስምምነቱን በሰጡት መግለጫ ይፋ አድርገዋል።


በዚህ ስምምነት መሰረት የቴምር ሪል ስቴት ደንበኞች የሚገዙትን የቤት ወይም የሱቅ አይነት መሰረት ያደረገና የከፈሉትን መጠን ያማከለ የዓለም አቀፍ በረራ የማይልስ ዕድል ያገኛሉ ተብሏል።



የቴምር ደንበኞች በዚህ ስምምነት መነሻነት የሼባማይልስ ደረጃቸው እንደ ክፍያቸው ሁኔታ እያደገ የሚሄድ ሲሆን፤ ከብሉ ወደ ሲልቨር፣ ከሲልቨር ወደ ጎልድ ወይም ከብሉ ወደ ጎልድ የማሳደግ ዕድልንም ይሰጣል መባሉን ሰምተናል።


ደንበኞች በሚገዙት ቤት አልያም ሱቅ መሰረት ከ50 ከመቶ በታች ክፍያ ሲፈጽሙ በእያንዳንዱ 1 ዶላር ክፍያ 2.5 ማይልስ የሚያገኙበት ዕድል እንደሚኖራቸው ከቴምር ፕሮፐርቲ የተላከልን መግለጫ ላይ ተመልክተናል።


እንዲሁም 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ክፍያ የሚፈጽሙ ደንበኞች በእያንዳንዱ 1 ዶላር ክፍያ 3.5 ማይልስ ሽልማት የሚያገኙበትን ዕድል ተመቻችቷል ተብሏል።


ይህ የአጋርነት ስምምነት በተለያዩ የአለም ክፍሎች ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ቤት ገዥዎች የሚጠቅም መሆኑ ተነግሮለታል።


የቴምር ሪል ስቴት በቤት ግንባታ ዘርፍ ከተሰማራ አስር አመታት ማስቆጠሩን አስታወሷል።

Recent Posts

See All
የመንግስት ግዥ አገልግሎት በዘንድሮው በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት በሽያጭ ከተወገዱ ተሽከርካሪዎች እና ሌሎች ንብረቶች የተገኘ ወደ 323 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ለመንግስት ገቢ አድርጌያለሁ አለ፡፡

ግንቦት 17/2018 የመንግስት ግዥ አገልግሎት በዘንድሮው በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት በሽያጭ ከተወገዱ ተሽከርካሪዎች እና ሌሎች ንብረቶች የተገኘ ወደ 323 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ለመንግስት ገቢ አድርጌያለሁ አለ፡፡ አገልግሎቱ ይህን ያህል ገንዘብ ዘጠኝ ወራት ውስጥ ለመንግስት ገቢ ሲያደርግ በታሪኩ የአሁኑ የጀመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page