የአቪዬሽን ዘርፍ ባለሙያዎች በሚፈለገው ልክ ማሰልጠን እና ያሉትንም የማቆየቱ ፈተና እንዴት እየሆነ ይሆን?
- 5 hours ago
- 1 min read
መጋቢት 24/2018
በአቪዬሽን ዘርፍ የሚሰማሩ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች፣ ኦዲት ኢንስፔክተሮች እና ሌሎች ባለሞያዎችን መቅጠር፣ ያሉትንም ማቆየት የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ዘርፍ ያልተፈታ ፈተና ነው።
በክፍያ ምክንያት የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን እነዚህን የአቪዬሽን ዘርፍ የጀርባ አጥንት የሆኑትን ባለሙያዎች በሚፈለገው ልክ ለማግኘትና፣ የገቡትንም ለማቆየት እንደሚቸገር በየጊዜው ይነሳል።
ኢትዮጵያ ከዓለም ተወዳዳሪ፣ ከአፍሪካ ቀዳሚ የሆነ ግዙፍ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ እየገነባች ነው፣ የአቪዬሽኑ ዘርፍ በፍጥነት እያደገ ነው፣ የሀገር ውስጥ በረራን የሚሰጡ አዳዲስ አውሮፕላን ማረፊያዎችም በየክልሉ እየተገነቡ ነው።

ለመሆኑ ለዚህ ሁሉ ስራ የግድ የሆኑትን፣ የአቪዬሽኑን ዘርፍ ከጀርባ ሆነው የሚደግፉትን፣ የበረራ ደህንነትን የሚያረጋግጡትን ባለሙያዎች በሚፈለገው ልክ ማሰልጠን እና ያሉትንም የማቆየቱ ፈተናስ እንዴት እየሆነ ይሆን?
ለዓመታት ከክፍያ ጋር በተገናኘ የሚነሳው ጥያቄና ሠራተኛውን የሚያስኮበልለው ችግርስ የሚፈታው እንዴት ነው?
ይህንን ጥያቄ ለኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሃንስ አበራ አቅርበናል።
እሳቸውም ይህንን ችግር ለመፍታት እየተሰራ ስላለው ስራ ነግረውናል።
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..
ቴዎድሮስ ወርቁ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments