በኢትዮጵያ የተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሚያስፈልጋቸውን የፋይናንስ አቅርቦት
- Mar 30
- 1 min read
መጋቢት 21/2018
በኢትዮጵያ የተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሚያስፈልጋቸውን የፋይናንስ አቅርቦት አግኝተው ምርታማ እንዲሆኑ የፋይናንስ ተቋማት በየዓመቱ ከሰባት ትሪሊዮን ብር በላይ ብድር ፈሰስ ማድረግ እንዳለባቸው መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
ይሁንና የሚቀርበው ብድር ከሚያስፈልገው ከግማሽ በታች መሆኑን ከሰሞኑ የብሔራዊ ባንክ ያወጣው ሪፖርት አሳይቷል፡፡
እንደ ማሳያ የግብርናው ዘርፍ በየዓመቱ ከሁለት ትሊዮን ብር በላይ #ብድር እያስፈለገው ያገኘው ግን 8 በመቶ ብቻ ነው፡፡

ካገኘው ብድሩ መካከልም አብዛኛው ለማዳበሪያ ማስመጫ የተሰጠ ብድር መሆኑን የብሔራዊ ባንክ ሪፖርት አሳይቷል፡፡
ለአምራች ኢንዱስትሪውና ቤት መግዛት ለሚፈልጉም የሚቀርበው ብድርም እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡
በተለይ ለቤት ገዥዎች የሚያስፈልገው ብድር ቢቀርብ እንኳን በተለይ ተቀጣሪው የመበደርና ብድሩን የመመለስ አቅም የለውም፡፡
በሌላ በኩል የቁጠባም ሆነ የብድር ተጠቃሚዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
በፋይናንስ ተቋማት ለተቀማጭነት ከተቆጠበ ገንዘብ 60 በመቶው በመንግስት የልማት ድርጅቶች ሀብት መሆኑን የብሔራዊ ባንክ ሪፖርት አሳይቷል፡፡
ለግለሰቦችም ሆነ ለሀገር እድገት የቁጠባም ሆነ የብድር አቅም ከፍ ማለት እንዳለበት እሙን ነው፤ ሪፖርቱ የሚያሳየው ደግሞ ተቃራኒው ነው፡፡
መፍትሄው ምንድነው? የፕራግማ ካፒታል መስራችና የፋይናንስና ኢንቨስትመንት ባለሙያውን አቶ መርዕድ ፍቅረዮሐንስን ጠይቀናል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….
ትዕግስት ዘሪሁን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments