ለትርፍ የተቋቋሙ የመንግስት ተቋማት ጭምር በበጎ አድራጎት ስራ ላይ ተሰማርተው ማህበራዊ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ተጠየቀ፡፡
- 1 day ago
- 1 min read
መጋቢት 22/2018
ለትርፍ የተቋቋሙ የመንግስት ተቋማት ጭምር በበጎ አድራጎት ስራ ላይ ተሰማርተው ማህበራዊ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ተጠየቀ፡፡
እንደ ባንኮች፣ አምራች እንዱስትሪዎችና ሌሎችም የመንግስትና የግል አትራፊ ተቋማት በጎ አድራጎት ላይ በመሳተፍ ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ተጠይቋል።

የተቋማቱ አትራፊነትና ስኬት ምንጭ ህዝብ እንደመሆኑ፣ አቅመ ደካሞችን በመርዳት ፣ ጎዳና ላይ የወደቁትን በማንሳት፣ ወላጅ አልባ ህፃናትን በማስተማርና በሌሎችም በጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ በመሳተፍ የማህበራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ የተጠየቀው ሙዳይ የበጎ አድራጎት ማህበር "የፍቅር ሳምንት" የተሰኘ ዓመታዊ መርሃ ግብሩን አስመልክቶ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።
#ሙዳይ_በጎ_አድራጎት_ማህበር ህፃናት፣ ሴቶችና አካል ጉዳተኞችን ከልመና፣ ከጎዳና ተዳዳሪነትና ከድህነት በማላቀቅ በራሳቸው እንዲቆሙ ማስቻልን ዓላማ አድርጎ እየተንቀሳቀሰ ያለ ሀገር በቀል ግብረ ሰናይ ድርጅት መሆኑን፣ የድርጅቱ መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሙዳይ ምትኩ ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት ከ1400 በላይ ህፃናትና ሴቶችን እየረዳ ነው ተብሏል።
ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ዓመታት የፍቅር ሳምንትን ሲያከብር ቆይቷል ያሉት ዋና ስራ አስኪያጇ ሙዳይ ምቱኩ፣ በዚህ ዓመትም ከመጋቢት 21 እስከ መጋቢት 28 የሚካሄደው ፕሮግራም መጀመሩን አንስተዋል።
ንጋት መኮንን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7




Comments