አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ከሌሎች ተማሪዎች እኩል የማይማሯቸው ትምህርቶች በመኖራቸው ተወዳዳሪነታችንን ይቀንስብናል ብለዋል።
- 3 hours ago
- 1 min read
መጋቢት 24/2018
በኢትዮጵያ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ቀላል የማይባል ችግር እንደሚያጋጥማቸው በተደጋጋሚ ይናገራሉ፡፡
የመሰረተ ልማት አለመሟላት፣ እነሱን ተቀብሎ የሚያስተምር ትምህርት ቤት አለማግኘት፣ የቁሳቁስ አለመሟላት፣ በስራ ቅጥር ወቅት እድል አለማግኘት እና በሌሎች ፈተናዎች እንደሚያልፉ ይነገራል፡፡
አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ከሌሎች ተማሪዎች እኩል የማይማሯቸው ትምህርቶች በመኖራቸው ተወዳዳሪነታችንን ይቀንስብናል ብለዋል።
በዚህም ምክንያት አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ገበያ ሲቀላቀሉ ከሌሎች ተማሪዎች ጋር እኩል ተወዳዳሪ ለመሆን እንደሚቸገሩ አንስተዋል።
ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ እስከ ሁለተኛ ደረጃ የትምህርት ክፍል ድረስ አካል ጉዳተኞች የማይማሯቸው የትምህርት ዓይነቶች በመኖራቸው ተወዳዳሪነታቸው ላይ ችግር እየፈጠረባቸው መሆኑንም ነው ተማሪዎቹ የሚናገሩት።
እንደማሳያም ዓይነ ስውራን ተማሪዎች ሰውነት ማጎልበቻ፣ ሒሳብ፣ ፊዚክስ እና ሌሎችንም የትምህርት ዓይነቶች እንደማይማሩ የሚያነሱት ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ገበያ ሲወጡ ከሌሎች ተማሪዎች እኩል ተወዳዳሪ እና ብቁ እንዳንሆን እንቅፋት እንደሚፈጥርባቸው ተናግረዋል።
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….
ፋሲካ ሙሉወርቅ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments