የነዳጅ የሚያጓጉዙ ቦቴ ባለንብረቶች በየሁለት አመቱ የትራንስፖርት ታሪፍ እንዲሻሻልላቸው ህግ ቢኖርም ስራ ላይ እየዋለ ባለመሆኑ የባንክ እዳ መክፈል አልቻልንም አሉ፡፡
- 10 hours ago
- 1 min read
ሐምሌ 15 2018
የነዳጅ የሚያጓጉዙ ቦቴ ባለንብረቶች በየሁለት አመቱ የትራንስፖርት ታሪፍ እንዲሻሻልላቸው ህግ ቢኖርም ስራ ላይ እየዋለ ባለመሆኑ የባንክ እዳ መክፈል አልቻልንም አሉ፡፡
የመኪና መለዋወጫ ውድነትና ሌላም ጫና ቢኖርብንም በሚገባን ልክ ክፍያ እያገኘን ባለመሆኑ ከስራው ለመውጣት እየተገደድን ነው ይላሉ፡፡
የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ማህበር የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን በተገኘበት በጉዳዩ ላይ ውይይት አድርጓል፡፡
በዘርፉ ላይ ጥናት አድርጋቸው አምጡ ብንባልም ከአንዴም ሁለቴ ጥናት አድርገን ለሚመለከተው አካል ብንሰጥም ምንም የተለወጠም የተሻሻለው ነገር የለም ሲሉ ያስረዳሉ፡፡
የባንክ እዳ የኢንሹራንስ የመኪና መለዋወጫና የአሽከርካሪ ክፍያ እና ሌላም ሌላም ተደማምሮ ኪሳራ ውስጥ ገብተናል መንግስት ሊመለከተን ይገባል ሲሉ ባለንብረቶቹ ቅሬታቸውን ተናግረዋል፡፡
በኢትዮጵያ ከ5 ሺ በላይ የነዳጅ የሚያጓጉዙ ቦቴዎች እንዳሉና ከእነዚህ ውስጥ 75 በመቶ የሚሆነው የባንክ እዳ ያለባቸው በመሆኑ ሰምተናል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ....
ማርታ በቀለ
_edited.jpg)



Comments