በኢትዮጵያ በቆዳና ሌጦ ዘርፍ ሲሰሩ ከነበሩ 31 ፋብሪካዎች ውስጥ አሁን በስራ ላይ ያሉት ሰባት ብቻ ናቸው ተባለ።
- 30 minutes ago
- 1 min read
ሐምሌ 16 2018
በኢትዮጵያ በቆዳና ሌጦ ዘርፍ ሲሰሩ ከነበሩ 31 ፋብሪካዎች ውስጥ አሁን በስራ ላይ ያሉት ሰባት ብቻ ናቸው ተባለ።
ይህን ያለው የኢትዮጵያ ጥሬ ቆዳ እና ሌጦ አቅራቢዎች ማህበር ነው ።
እነዚህ ፋብሪካዎች የወጡት በግብር እና በቫት መጨመር እንደሆነም ማህበሩ ነግሮናል።
ፋብሪካዎቹ ላይ ቫት እንዲጨመር የተደረገው የቆዳው ዘርፍ አካባቢን እየበከለ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ እንደሆነ ሰምተናል።
ይህንን የነገሩን የኢትዮጵያ ጥሬ ቆዳና ሌጦ አቅራቢዎች ማህበር የቦርድ ፀሐፊ አቶ መስፍን ለገሠ ናቸው ።
ይህ ችግር እንዲፈታ ለተለያዩ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ጥያቄ አቅርበናል ያሉት አቶ መስፍን ለጥያቄያቸውም ምላሽ እየጠበቁ መሆኑም ነግረውናል።
በሌላ በኩል በቆዳ እና ሌጦ ዘርፍ ያሉ የጥሬ እቃ ችግሮች ከሞላ ጎደል እየተፈቱ ቢሆንም አሁንም ከዘርፉ የወጡ አምራቾችን የሚመለስ አሰራር ወይንም እልባት እያገኘ እንዳልሆነ ነግረውናል ።
አቶ መስፍን አሁንም በዘርፉ አሉ ካሏቸው ችግሮች መካከል የጨው ምርት ተጠቃሽ ነው።
ከዚህ ቀደም በቆዳ እና ሌጦ ዘርፍ የነበረው የገበያ ትስስር ችግር አሁን በተወሰነ መልኩ መሻሻል እንዳሳየም አቶ መስፍን ነግረውናል።
ይሁን እንጂ በግብር እና በቫት መጨመር ምክንያት እየተጎዳ ያለው የቆዳው ዘርፍ የሚመለከተው መስሪያ ቤት እልባት እንዲሰጥበትም የኢትዮጵያ ጥሬ ቆዳና ሌጦ አቅራቢዎች ማህበር ጠይቋል።
ፍቅሩ አምባቸው
_edited.jpg)
