በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት ወይም ማቆያዎች ላይ ለውጦች እየመጡ ነው ተባለ፡፡
- 9 hours ago
- 1 min read
ሐምሌ 15 2018
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት ወይም ማቆያዎች ላይ ለውጦች እየመጡ ነው ተባለ፡፡
ከጥቂት አመታት በፊት የህፃናት ማቆያዎቹ ጥቂት ነበሩ ያለው የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አሁን ላይ ከፍተኛ መሻሻሎች ታይተውበታል ብሏል፡፡
ጥናቱም በግል እና በመንግስት ማቆያዎች ላይ ያሉ ለውጦችን እና መሻሻሎችን ለማየት ሞክሯል የተባለ ሲሆን በመንግስት የሚሰሩት ማዕከላት የስራ ቦታ እና የህዝብ ማቆያዎች ናቸው ብሏል፡፡
በዚህም የህዝብ የሚባሉት ማቆያዎችን መንግስት ከምግብ ጀምሮ መሰረተ ልማቶችን እና ሌሎች ለህፃናቱ የሚያስፈልጉ ነገሮችን አሟልቶ የሚያቀርብ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ሌላኛው በመንግስት ተቋማት ለሚሰሩ ሰራተኞች ልጆች የተዘጋጀው የስራ ቦታ የህፃናት ማቆያዎች ነው፡፡
የጥናቱ ውጤት የሚያሳየውም የተጠቃሚው ፍላጎት ከቀን ወደ ቀነ እየጨመረ መምጣቱን ነው ያለው ጥናቱ እንዲህ ዓይነት ህፃናት ማቆያ ማዕከላት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፉ መምጣታቸው በትምህርት ላይ ያሉ ልጆች ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዲከታተሉ አድርጓል ብሏል።
በተጨማሪም የህዝብ የህፃናት ማቆያዎች ላይ ደግሞ ከ55 በመቶ በላዩ ሴቶች ወደ አዲስ ስራ እንደገቡ እና የኢኮኖሚ አቅማቸው እንዲያድግ አድርጓል ተብሏል።
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ...
ፋሲካ ሙሉወርቅ
_edited.jpg)




Comments