top of page

10 አባላት ያሏቸው ቡድኖች በሚያጠናቅሩት ሪፖርት ላይ ከነገ ጀምሮ ምክክሩ እንደሚቀጥል የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተናገረ።

  • 4 hours ago
  • 1 min read

ሐምሌ 16 2018


10 አባላት ያሏቸው ቡድኖች በሚያጠናቅሩት ሪፖርት ላይ ከነገ ጀምሮ ምክክሩ እንደሚቀጥል የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተናገረ።


የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ የምክክሩን ያለፉት 3 ቀናት ውሎ ያብራሩበትን መግለጫ ሰጥተዋል።



ከሰኞ ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ 50 ተመካካሪዎችን በያዙ ንዑሰ ቡድኖች በመከፋፈል በተመደቡበት አጀንዳዎች ላይ ሲመካከሩ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡


በእያንዳንዱ ንዑስ ቡድን 50 ተመካካሪዎችን የያዙ 80 አነስተኛ ቡድኖች ሲወያዩ ቆይተዋል ብለዋል።


ለምክክሩ አመቺነት ሲባልም ኮሚሸኑ ባስቀመጠው አሰራር መሰረት 50 ተመካካሪዎች ባሉበት ቡድን ውስጥ ተሳታፊዎች አስር አስር በመሆን የምክክር ሂደቱ መቀጠሉንም ፕሮፌሰር መስፍን ጠቅሰዋል።



የነበረው የምክክር ሂደት ተመካካሪዎች ስለተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ያላቸውን አመለካከት፣ ስጋት፣ ፍላጎት እንዲሁም ተስፋ ጠለቅ ያለ ግንዛቤን እንዲኖራቸው ያደረገ እንደነበርም አንስተዋል ።


በዚህ መነሻነት ዛሬ ሐምሌ 16 ቀን ተመካካሪዎች እንዲመካከሩ በተመደቡባቸው የአጀንዳ ሀሳቦች ላይ ኮሚሸኑ በተለያዩ መመዘኛዎች መልምሎ ያሰማራው የባለሙያዎች ሰብሰብ በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ በምክክር አጀንዳ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሳንይንሳዊ ገለፃዎችን አድርገዋል፡፡


በከሰዓቱ የምክክር ጊዜ ተመካካሪዎቹ በቀረቡቸው በገለፃዎች ላይ የጥያቄና መልስ ጊዜ ይሆናል ተብሏል ፡፡


በነገው ዕለትም ተሳታፊዎች በ50 ቡድኖቻቸው ተመልሰው የምክክር ሂደቱ የሚቀጥል መሆኑ በመግለጫው ተጠቅሷል።


ምንታምር ጸጋው

Recent Posts

See All
በኢትዮጵያ በቆዳና ሌጦ ዘርፍ ሲሰሩ ከነበሩ 31 ፋብሪካዎች ውስጥ አሁን በስራ ላይ ያሉት ሰባት ብቻ ናቸው ተባለ።

ሐምሌ 16 2018 በኢትዮጵያ በቆዳና ሌጦ ዘርፍ ሲሰሩ ከነበሩ 31 ፋብሪካዎች ውስጥ አሁን በስራ ላይ ያሉት ሰባት ብቻ ናቸው ተባለ። ይህን ያለው የኢትዮጵያ ጥሬ ቆዳ እና ሌጦ አቅራቢዎች ማህበር ነው ። እነዚህ ፋብሪካዎች የወጡት በግብር እና በቫት መጨመር እንደሆነም ማህበሩ ነግሮናል። ፋብሪካዎቹ ላይ ቫት እንዲጨመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page