top of page

ህገወጥ ደላሎች፤ ሰዎች በህገወጥ መንገድ ጉዞ ለመጀመር ሲያስቡ ወይም ህገወጥ ስደትን እዲያስቡ ከሚያደርጓቸው ከቀዳሚ ምክንያቶች መካከል ይጠቀሳል።

  • 6 minutes ago
  • 1 min read

ሰኔ 26/2018


በየአካባቢው ያሉ ህገወጥ ደላሎች፤ ሰዎች በህገወጥ መንገድ ጉዞ ለመጀመር ሲያስቡ ወይም ህገወጥ ስደትን እዲያስቡ ከሚያደርጓቸው ከቀዳሚ ምክንያቶች መካከል ይጠቀሳል።


እነዚህ ደላሎች ኢትዮጵያውያኑ በህገ- ወጥ መንገድ ከሀገራቸው እንዲወጡ የተለያዩ ማማለያዎች በመጠቀም በሺዎች የሚቆጠሩትን አስወጥተዋል፡፡


ነገር ግን በዚሁ መንገድ ከሚወጡት ሰዎች መካከል የአውሬ እራት የሚሆኑ እና ካሰቡበት ሳይደርሱ መንገድ ላይ የሚቀሩትም ብዙ ናቸው፡፡


ይህንን ስራ የሚሰሩት ደላሎችም ቢሆኑ ለህግ ሲቀርቡ እንደማይስተዋል የተነገረ ሲሆን ማህበረሰቡ ቢያውቃቸውም ደፈር ብሎ ለህግ አካላት አሳልፎ የመስጠት ልምድ እንደሌለውም በጉዳዩ ላይ የሚሰሩ ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡


ህገወጥ ደላሎች ህግ ፊት ለማቅረብ ማህበረሰቡ እንዲጠቁም ለማድረግ ቢሞክርም ያ ሲሆን እንደማይስተዋል ያስረዳሉ፡፡


ህገወጥ ደላሎቹ በተለይ በገጠሪቱ የሀገሪቱ አካባቢ በሚገባ እየታወቁ ነዋሪው የማይጠቁምበት ምክንያት ምንድን ነው ስንል የጠየቅናቸው የማህበራዊ ጥናት መምህር እና ተመራማሪው ሎምቤቦ ታገሰ(ዶ/ር) ነዋሪው ቢጠቁም እንኳን ተመጣጣኝ ቅጣት ስለማይጣልባቸው ፍራቻ ላይ ይወድቃሉ ብለዋል።


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….


ፋሲካ ሙሉወርቅ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…









Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page