ትልልቅ የሚባሉ ባንኮች ኪሳራ ሊያስከትል የሚችል የብድር አሰጣጥ አሰራርን እንደሚከተሉ ጥናት አሳየ፡፡
- 7 minutes ago
- 1 min read
ሰኔ 25/2018
ትልልቅ የሚባሉ ባንኮች ኪሳራ ሊያስከትል የሚችል የብድር አሰጣጥ አሰራርን እንደሚከተሉ ጥናት አሳየ፡፡
ትልልቅ ካፒታል ያላቸው ባንኮች ለኪሳራ ሊያጋልጡ የሚችሉ አሰራሮችን ስራ ላይ የሚያውሉበት አንደኛው ምክንያት አደጋ ቢያጋጥመን መንግስት ያግዘናል የሚል አስተሳብ ስላላቸው ነው ተብሏል፡፡
በጥናቱ 31 የመንግስትና የግል ባንኮችን እንደተካተቱበትና በባንኮቹ መሃል ውድድር ሲኖርና ሳይኖር ያለው ልዩነት በጥናቱ ተለይቷል፡፡
ይህንን ለማረጋገጥ የ31ን ባንኮች የፋይናንስ መረጃዎችን መመልከታቸውንም በቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ የአካዉንቲንግ እና ፋይናስ መምህርና ተመራማሪው እንዲሁም አጥኚው ነዋይ አያሌው ነግረውናል።
አሁን ላይ ባንኮች በከፍተኛ ውድድር ውስጥ እየገቡ መሆኑን አንስተው ይህ ደግሞ የችግሩን መጠን እንደሚቀንስ በጥናታቸው ማረጋገጣቸውን አክለዋል።
ጥናቱ መፍትሄ የሚሆኑ ምክረ ሀሳቦችንም አካተዋል፡፡
ማርታ በቀለ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv

