top of page

በ2018 ወደ ውጪ ከተላከ ቡና 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን የግብርና ሚ/ር ተናገረ፡፡

  • 5 hours ago
  • 1 min read

ሰኔ 25/2018


በ2018 በጀት ዓመት ወደ ውጪ ከተላከ ቡና 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር ተናገረ፡፡


በጀት ዓመቱ ከቡና ወጪ ንግድ 3 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ለማግኘት የተያዘው ዕቅድ ማሳካቱን ሚኒስቴር መ/ቤቱ አስረድቷል፡፡


በባለፈው በጀት ዓመት ከቡና ወጪ ንግድ 2.65 ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን ሚኒስቴር መ/ቤቱ አስታውሷል፡፡


መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት የቡናውን ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስራዎች እየተሰሩ ነው ያለው የግብርና ሚኒስቴር በዚህም ለውጥ መጥቷል ሲል አስረድቷል፡፡


ኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ላይ 5.8 ሚሊዮን ገበሬ በቡና አምራችነት ተሰማርቶ የሚገኝ ሲሆን ገበሬው ከሰራው ስራ ወደ ኪሱ የተጣራ ገቢ የሚያገኘው 40 ከመቶውን ብቻ መባሉ ይታወሳል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…..


በረከት አካሉ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page