የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ ኢራንን ለመምታት መዘጋጀቱን ተሰማ፡፡
- 1 hour ago
- 1 min read
የካቲት 12/2018
የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ ኢራንን ለመምታት መዘጋጀቱን ተሰማ፡፡
ዋሽንግተንን ቴህራንን በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት ለመምታት ዝግጅት ማድረጓን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ሰዎች ነግረውናል ብሎ የዘገበው ሲ ኤን ኤን ነው፡፡
ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግን የመጨረሻውን ውሳኔ አለመስጠታቸው በመረጃ ተጠቅሷል፡፡
የአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ከፍተኛ ባለስልጣናት በትላንትናው እለት በዋይት ሐውስ ተገኝተው በኢራን ጉዳይ ላይ ውይይት ማድረጋቸውም ተነግሯል፡፡
ትራምፕም ከኢራን ጋር ስለተደረገው ድርድር ሁኔታ ከልዩ መልዕክተኛው ስቲቭ ዊትኮፍ እና ከአማቻቸው ጃሬድ ኩሽነር ማብራሪያ እንደተሰጣቸው በመረጃው ተነስቷል፡፡

አሜሪካና ኢራን ያደረጉት ትራምፕ ቀይ መስመር በሚላቸው ጉዳዮች ላይ አሁንም ከስምምነት አለመድረሱ ተዘግቧል፡፡
በተጨማሪም አሜሪካ በሶሪያ የቀሯትን ወታደሮች ልታስወጣ ተነግሯል፡፡
ዋሽንግተን ከሶሪያ ወታደሮቿን በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት ውስጥ ለማስወጣት መዘጋጀቷን የዋይት ሐውስ ምንጮቼ ነግረውናል ብሎ ቢቢሲ ፅፏል፡፡
አሜሪካ ወደዚህ እርምጃ የገባችው ሶሪያ በግዛቷ ውስጥ ሽብርተኝነትን በመዋጋት በኩል የመሪነት ሚና እንድትጫወት ለማስቻልና በዚያ የአሜሪካ ሀይል በከፍተኛ ቁጥር መኖር ከዚህ በኋላ አስፈላጊ ሆኖ ባለመገኘቱ ነው ተብሏል፡፡
የአሜሪካ ወታደሮች የአይ ኤስ ተፅዕኖንን ለመግታት የፀረ ሽብር ዘመቻ አካል ሆነው ባለፉት 11 አመታት በሶሪያ ውስጥ መቆየታቸው መረጃው አስታውሷል፡፡
በዚህ አመት መጀመሪያ አካባቢ በሶሪያ ከሚገኙ ሁለት የጦር ሰፈሮች የአሜሪካ ወታደሮች ለቀው መውጣታቸውም ተጠቅሷል፡፡
አሜሪካ ከሶሪያ ቀሪ ወታደሮቿን ለማስወጣት የወሰነችው ከኢራን ጋር የገባችው ፍጥጫ እየተካረረ ባለበት አጋጣሚ ነው፡፡
ንጋቱ ሙሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7











Comments