top of page

ኢትዮጵያ በመካከለኛ የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ዝርጋታ አቅሟን ለማሳደግ ከፈረንሳይ ተቋም ጋር ውል አሰረች፡፡

  • sheger1021fm
  • 12 minutes ago
  • 1 min read

ጥቅምት 25 2018

 

ኢትዮጵያ በመካከለኛ የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ዝርጋታ አቅሟን ለማሳደግ ከፈረንሳይ ተቋም ጋር ውል አሰረች፡፡

 

የመካከለኛ የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ተጠቃሚዎች የሆኑት ኢንዱስትሪዎች መሆኑ የተነገረ ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሚያስተዳድራቸው እና ከሚመራቸው መስመሮች አንዱ መሆኑ ተነግሯል፡፡


ree

 

ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የመካከለኛ መስመር ዝርጋታ አቅምን ለማሳደግ የተፈራረመችው ከፈረንሣዩ 'ኤሊክቲሪሲቲ ደ ፍራንስ' (EDF) ጋር መሆኑን  ሰምተናል፡፡

 

በሌላ በኩል አገልግሎቱ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ግብዓቶች ከሚያመርት የኬንያ ኩባንያ ጋር ውይይት ማረጉን ተናግሯል፡፡

 

ተቋሙ ከኩባንያው ጋር የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ግብዓቶችን በኢትዮጵያ ማምረት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መወያየቱን የሰማን ሲሆን ለኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ዝርጋታ የሚያገለግሉ ኬብሎችን፣ ኮንዳክተሮች፣ ምሰሶዎች፣ ስማርት ሜትሮችና ተያያዥ ግብዓቶች እንደሚያርት ተነግሮለታል፡፡   

               

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…

 

ፋሲካ ሙሉወርቅ

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇

 

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page