top of page


ምጣኔ ሀብት - ባንኮች ለአገልግሎት የሚጠይቁት ክፍያ
በተለያየ ጊዜ ባንኮች ለአገልግሎት የሚጠይቁት ክፍያ እየጨመረ ነው። ይህ የአገልግሎት ክፍያ በተለይ ተደጋጋሚ አገልግሎት የሚፈልጉ ደንበኞችን ቅር አሰኝቷል። የግል ባንኮች በአንድ በኩል የቢሮ እና የባንክ ስራው ላይ ተፎካካሪና ተወዳዳሪ መሆን ሲገባቸው፤ የህንፃ ግንባታና ኪራይ ላይ መግባታቸውም ጥያቄ ይፈጥራል። ለመሆኑ በዲጂታል ዘመን የወረቀት ስራና ሌላውም የቀለለላቸው ባንኮች እንዴት የአገልግሎት ክፍያቸው ከፍተኛና ቅር የሚያሰኝ ሊሆን ይችላል ተብሎ ይጠየቃል። አቶ ያዕቆብ በቀለ ፌደራሊዝም እና ኢኮኖሚክስ ተንታኝ ናቸው፡፡ ሙሉ ዘገባውንያድምጡ… ተህቦ ንጉሴ ጥቅምት 10 2018 የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37
6 days ago1 min read


ጥቅምት 14 2018 - የባንክ ደንበኞች ከሚመለከተው ግብር ሰብሳቢ ከሰጣቸው ሂሳብ ውጪ በግላቸው ሂሳብ ግብይቶች እንደሚገላበጥ ተሰማ
ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የባንክ ደንበኞች ከሚመለከተው ግብር ሰብሳቢ ከሰጣቸው ሂሳብ ውጪ በግላቸው ሂሳብ የተለያዩ ግብይቶች እንደሚገላበጥ ተሰማ። ይህን ያረጋገጠው የኢትዮዽያ ብሔራዊ ባንክ ነው። ባንኩ ባደረግሁት ምርመራ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ግለሰብ ነጋዴዎች በዚህ እንቅስቃሴ እንዳሉ አውቄያለሁ ብሏል። #የኢትዮጵያ_ብሔራዊ_ባንክ የተለያዩ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰብ ነጋዴዎች የግብር ሰብሳቢ ተቋም ካስመዘገቡት የባንክ ሒሳቦች ውጪ ወደ ግል እና ሶስተኛ ወገን የገንዘብ እንቅስቃሴዎች እየፈፀሙ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል። ይህ አሰራርም ከግብር ሰብሳቢ ባለስልጣናት ቁጥጥር እና ክትትል ለመሸሽ የሚደረግ ተግባር እንደሆነ ባንኩ አስረድቷል። በተጨማሪም በዚህ መልኩ የሚፈፀሙ የፋይናንስ ግብይቶች እና የገንዘብ እንቅስቃሴዎች የወንጀል ፍሬ ሊሆኑ እንደሚችሉ ባ
6 days ago1 min read


ጥቅምት 14 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ሩሲያ የሩሲያው ፕሬዘዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለአሜሪካም ሆነ ለሌሎች አገሮች ጫና በጭራሽ አንበገርም አሉ፡፡ የፑቲን አስተያየት የተሰማው አሜሪካ በሁለት ታላላቅ የሩሲያ የነዳጅ ኩባንያዎች ላይ ማእቀብ መጣሏን ተከትሎ እንደሆነ ዘ ስትሪይትስ ታይምስ ፅፏል፡፡ አሜሪካ በሩሲያ የነዳጅ ኩባንያዎች ላይ ማዕቀብ የጣለችው የዩክሬይኑን ጦርነት ለማስቆም በሞስኮ ላይ ጫና ለመፍጠር አልማ ነው ተብሏል፡፡ ፑቲን የአሜሪካን የማዕቀብ እርምጃ ገንቢ ያልሆነ ብለውታል፡፡ አገራቸው ለዚህ እና ለሌሎችም ጫናዎች እንደማትበገር የሩሲያው ፕሬዘዳንት ተናግረዋል፡፡ የሩሲያው ፕሬዘዳንት አሜሪካ ለዩክሬይን ቶም ሐውክ የተባለውን የረጅም ርቀት ተወንጫፊ ሚሳየል እንዳታስታጥቅ በብርቱ አስጠንቅቀዋል፡፡ ሆኖም በዚህ ዓይነት የጦር መሳሪያዎች በሩሲያ ላይ ጥቃት የሚሰነዘርባት ከሆነ ውርድ ከ
7 days ago2 min read


ጥቅምት 14 2018 - የባዮቴክኖሎጂ ውጤት የሆነው የዘረመል ምህድስና GMO
ኢትዮጵያ ግብርናን ቀድመው ከጀመሩ የዓለም ሀገራት ስሟ ቀድሞ ይነሳል፡፡ ዛሬም ግን ሀገሪቱ የትናንት የሚባል ታሪክ ካላቸው ሀገራት ተርታ እንኳን በምግብ እራሷን ችላ መሰለፍ ተስኗታል፡፡ በ21ኛው ከፍለ ዘመንም የርሃብ፣ የምግብ እጦት፣ ዜና ከምድሯ አልጠፋም፡፡ ከ1,600 በላይ ዝርያዎችን ባለፉት 70 ዓመታት ለአርሶ አደሮች ማከፋፈሉን የሚናገሩት የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ንጉሴ ደቻሳ (ፕ/ር)፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥር በጣም እየጨመረ መሆኑን አስረድተው፤ የሰብል ምርቶች ምርታማነትም በእጥፍ መጨመሩን አብራርተዋል፡፡ ለምሳሌ በአርሶ አደር ማሳ ላይ ጤፍ በሄክታር ከ10 ኩንታል ወደ 20፣ ስንዴ ከ20 ወደ 36፣ ቦሎቄ ከ14 ወደ 28 ከፍ ማለቱን አስረድተዋል፡፡ ንጉሴ ደቻሳ(ፕ/ር) ይህም ሆኖ የምርት እድገቱ ከኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት መ
7 days ago3 min read


ጥቅምት 14 2018 - ሕብረት ባንክ ከሚሰጠው ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የሰበሰበውን 35 ሚሊየን ብር ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች አበረከተ
35 ሚሊዮን ብሩ የተሰጠው ለ10 የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ነው፡፡ ድጋፍ የተርገላቸው አስሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች የተመረጡት በሸሪዓው መርህ መሰረት የሚሰሩ መሆናቸው ተመዝኖ፣ ከሚደርሱት የሕብረተሰብ ቁጥር እና የሚሰጠውን ድጋፍ ለምን ተግባር እንደሚያውሉትም ጭምር ታይቶ ነው ተብሏል። ድጋፉ ከተደረገላቸው ድርጅቶች መካከል፤ እማሙ ማሊክ ትምህርት ቤት፣ ወንድም ካሊድ ፋውንዴሽ፣ ባቡል ካኸር፣ ሜቄዶኒያ፣ ቢላሉ ሀበሺ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሙስሊም የጤና ባለሞያዎች ማህበር ይገኙበታል። ሕብረት ባንክ የሸሪዓውን መርህ በተከተለ መልኩ ከወለድ ነፃ የባንክ እገልግሎት መስጠት ከጀመረ 10 ዓመታት እንዳለፈው አስታውሷል። በአሁኑ ሰዓትም ሕብረት ባንክ 23 ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ብቻ የሚሰጡ ቅርንጫፎች ከፍቼ እየሰራሁ ነው ሲል ጠቅሷል። ባንኩ ሸሪዓው
7 days ago1 min read


ጥቅምት 13 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ሱዳን በሱዳን የRSF ፈጥኖ ደራሽ ሀይል ከአገሪቱ ኤርፖርቶች የሚነሱ እና በኤርፖቶቹ የሚያርፉ አውሮፕላኖችን በሙሉ አወድማለሁ ሲል ዛተ፡፡ ዛቻውን ያሰሙ የፈጥኖ ደራሹ ሀይሉ አዛዥ ሌተና ጄኔራል ሞሐመድ ሐምዳን ዳጋሎ እንደሆኑ ሱዳንስ ፖስት ፅፏል፡፡ ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ትናንት ወደ አገልግሎት ተመልሷል በተባለው የካርቱም ኤርፖርት ላይ ተደጋጋሚ የድሮን ጥቃት ሰንዝሯል ተብሏል፡፡ የካርቱም ኤርፖርት ትናንት ከ2 ዓመታት በኋላ የመጀመሪያውን የሀገር ውስጥ በረራ አውሮፕላን ማስተናገዱ ታውቋል፡፡ ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ከሱዳን መንግስት ጦር ጋር ሲዋጋ ከ2 ዓመታት ከመንፈቅ በላይ ሆኖታል፡፡ ጦርነቱን ማቆሚያ አንዳችም ፍንጭ አይታይም፡፡ #አሜሪካ በአሜሪካ በሁለት የሩሲያ ታላላቅ የነዳጅ ኩባንያዎች ላይ ያነጣጠረ አዲስ ማዕቀብ ጣለች፡፡ ማዕቀቡ የተጣለባቸው ሮስ
Oct 232 min read


ጥቅምት 13 2018 - የቴክኒክ ሞያ ዘርፎች ከታችኛው የትምህርት ደረጃ ጀምሮ ትኩረት እያገኘ አይደለም ተባለ፡፡
ለሀገር እድገት መሰረት የሆኑ የቴክኒክ ሞያ ዘርፎች ከታችኛው የትምህርት ደረጃ ጀምሮ ትኩረት እያገኘ አይደለም ፤ ይህም መስተካከል አለበት ተባለ፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀዳማይ ልጅነት እንክብካቤና ትምህርት ማዕከል መምህር አቶ ፍስሃ ተክሉ በልጅነት የሚሰራው ስራ ነገ በቴክኒክና ሞያ ትምህርት ቤት ውስጥ እጁ ከታች ጀምሮ የተፍታታ ተማሪ እንድናገኝ ይረዳል ብለዋል፡፡ እነዚህ ተማሪዎች ከሰዎች ጋር አብሮ የመስራትና የፈጠራ አቅማቸውም እጅግ የላቀ እንዲሆን ያደርጋልም ሲሉም ተናግረዋል፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት ዶክተር ታምሬ አንዷለም በበኩላቸው ኢትዮጵያ ውስጥ ለቴክኒክና ሞያ ትምህርት የሚሰጠው ትኩረት እጅግ አነስተኛ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ የትኩረት ማነሱ ችግር ዛሬ የመጣ ሳይሆን ቀደም ካለው ጊዜ ጀምሮ የነበረ ነው ያሉ ሲሆን ለሞያ
Oct 231 min read


ጥቅምት 13 2018 - የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሞያዎች ማህበር የኢትዮጵያ ብድር እዳ ጫና ከአጠቃላይ ሀገራዊ ምርቱ 39 በመቶ ደረጃ እንዳለው ተናገረ
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሞያዎች ማህበር የኢትዮጵያ ብድር እዳ ጫና ከአጠቃላይ ሀገራዊ ምርቱ 39 በመቶ ደረጃ እንዳለው ተናገረ፡፡ የእርዳታና ድጋፍ መቀነስም ከቀጠሉ ግጭቶችና መሰል ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ጋር ተዳምሮ ችግሩን እንዲያከፋው ቅድሚያ የሚያስፈልገውን እየለዩ መፍትሄ ማበጀት ያስችላል ብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ …. ተህቦ ንጉሴ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s 🐦X :...
Oct 231 min read


ኢትዮጵያ ብድሯን በቻይና የመገበያያ ገንዘብ ለመክፈል ጥያቄ ማቅረቧ፣ ምን ያስገኝላታል?
ኢትዮጵያ ዋና አበዳሪዋ ከሆነችው ቻይና ለወሰደችው ብድር 5.3 ቢሊዮን ዶላሩን በዩዋን ለመክፈል ጥያቄ አቅርባለች፡፡ ጥያቄው አዎታዊ ምላሽ ካገኘ የብር የመግዛት አቅም ይበልጥ እንዳይዳከም ያግዛል ተብሏል፡፡ እንዴት ? በአለም ዓቀፉ ደረጃ “ብድሯን ለመክፈል የምትቸገር ሀገር” በሚል የገባችበትን ምድብ በመቀየርስ ስሟን ያድስላት ይሆን? የዘርፉን ባለሞያ አነጋግረናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ትዕግስት ዘሪሁን የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬Wh
Oct 231 min read


ጥቅምት 13 2018 - በ3 ወራቱ ከውሃ ከመነጨው የኤሌክትሪክ ሃይል ግማሽ የሚሆነው ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የተገኘ እንደሆነ ተነገረ።
ባለፉት 3 ወራት ለኬንያ እና ጅቡቲ በሽያጭ ከቀረበ የኤሌክትሪክ ሃይል፤ ከ34 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ መገኘቱ ተነገረ። በሱዳን ያለው ግጭት በመሰረተ ልማቶች ላይ ጉዳት በማስከተሉ በጊዜ ማዕቀፉ የኤሌክትሪክ ሃይል ለሀገሪቱ በሽያጭ አልቀረበም ተብሏል። በሌላ በኩል በሶስት ወራቱ ከውሃ ከመነጨው የኤሌክትሪክ ሃይል ግማሽ የሚሆነው ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የተገኘ እንደሆነ ሠምተናል። ከሃምሌ 1 ቀን 2017 እስከ መስከረም 30/2018 ባሉት ሶስት ወራት ኢትዮጵያ 9,208 ጊጋ ዋት ሰአት የኤሌክትሪክ ሃይል አመነጭታለች ተብሏል። ከዚህ የኤሌክትሪክ ሃይል 98 በመቶ ወይም 9,027 ጊጋ ዋት ሰአቱ ከውሃ የሃይል ማመንጫ ገድቦች የተገኘ እንደሆነ ፤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ነግረውናል፡፡
Oct 231 min read


ጥቅምት 12 2018 ለሰላም፣ ለእድገት ሲባል መንግስት፣ የተፎካካሪ ፓርቲ ፖለቲከኞች እና ነፍጥ ያነሱ ታጣቂዎች ወደ መግባባት እንዲመጡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ጥሪ አቀረቡ፡፡
ፓርትርያርኩ ይህንን የሰላም ጥሪ ያቀረቡት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በተጀመረበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ነው፡፡ በሀገሪቱ ያለው አለመረጋጋት በህዝብ አጠቃላይ ስነ ልቦና፣ በሀገሪቱ አንድነትና እድገት ላይ የሚያስከትለው ጫና በቀላሉ የሚታይ አይደለም ያሉት አባ ማቲያስ ፣ የህዝቡ ስነ ልቦና ከተጎዳ የነገው እድል ጤናማ ይሆናል ተብሎ አይታሰብም ብለዋል፡፡ ችግሩ እየታየ ያለው በዋናነት በሀገራችን ፖለቲከኞች በመሆኑ ነገሩ የተወሳሰበና የተራዘመ እንዲሆን አድርጎታል ሲልም አክለዋል፡፡ በመሆኑም ይህ የርስ በርስ ግጭት ቆሞ ችግሮች በውይይትና በድርድር በመፍታት የወንድማማች እልቂት የሚያስቆም የሰላምና የዕርቅ ዕድል ቅድሚያ እንዲሰጠው ጉባኤው የበኩሉን ጥረት ማድረግ ይገባዋል ሲል አባ ማቲያስ ጠይቀዋል፡፡ የነገው ትውልድ ልማታዊ ተስፋ እውን ሊሆን የሚ
Oct 221 min read


ጥቅምት 12 2018 - አሲዳማ መሬትን ለማከም የሚረዳ የኖራ ወፍጮ በተለያዩ ክልሎች ሊያቋቁም መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ተናገረ
በአለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ እርዳታ አሲዳማ መሬትን ለማከም የሚረዳ የኖራ ወፍጮ በተለያዩ ክልሎች ሊያቋቁም መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ተናገረ፡፡ ለዚህ ተግባር የሚውል የ20 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ከአለም ባንክ መገኘቱም ተሰምቷል፡፡ ኢትዮጵያ ከምታርሰው መሬት ውስጥ 43 ከመቶ ወይም 7 ሚሊዮን ሄክታር የሚሆነው መሬቷ በአሲድ እንደተጠቃ የግብርና ሚኒስቴር ከአንድ ዓመት በፊት መናገሩ ይታወሳል፡፡ 3.1 ሚሊዮን ሄክታር የሚሆነው ደግሞ በጠንካራ አሲድ የተጠቃ አፈር ነው ተብሏል፡፡ የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ እያሱ ኤሊያስ (ፕ/ር) በአሲድ የተጠቃው መሬት ምርትን ከ70 እስከ 100 በመቶ ምርት እንደሚቀንስ ተናግረው ይህም የሀገሪቱን የግብርና ስራ ፈታኝ አድርጎታል ሲሉ አስረድተዋል፡፡ በኢሲድ የተጠቃው መሬት ከፍተኛ ዝናብ እና እርጥበት ያለበት አ
Oct 221 min read


ጥቅምት 12 2018 - "በአደጋው የሞቱና አድራሻቸው ያልታወቀ ሰዎች ስርዓተ ቀብር፣ በከተማ አስተዳደሩ ተፈፅሟል" የድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ድርጅት
"በአደጋው የሞቱና አድራሻቸው ያልታወቀ ሰዎች ስርዓተ ቀብር፣ በከተማ አስተዳደሩ ተፈፅሟል" የድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ድርጅት ሥራ አስኪያጅ። የባቡር ሾፌሩን ጨምር ለ15 ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው የድሬዳዋ ደወሌ የባቡር አደጋ እንዴት ሊከሰት ቻለ? ከባቡሩ እድሜ ጋር ተገናኝቶ እየተነሳ ያለው ጥያቄስ ለአደጋው መከሰት ምክንያት ነው ወይ? የድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ድርጅት ስራ አስኪያጅ እና ምክትል ስራ አስኪያጅን ጠይቀናል። ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… ቴዎድሮስ ወርቁ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://ti
Oct 221 min read


ጥቅምት 12 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ካሜሩን በካሜሩን ከሳምንት በፊት በተካሄደው ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ አረጋዊው የአገሪቱ መሪ ፖል ቢያ እንዳሸነፉ የቅድሚያ ውጤቱ አሳየ ተባለ፡፡ የአገሪቱ የምርጫ አከናዋኝ መስሪያ ቤት በቅድሚያ ውጤቱ ፖል ቢያ ለፕሬዘዳንታው ምርጫው ከተሰጠው ድምፅ 53 በመቶውን በማግኘት አሸንፈዋል ማለቱን አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡ የፖል ቢያ የቅርብ ተፎካካሪ ኢሳ ቺሮማ ባካሪ ያገኙት ድምፅ 35 በመቶ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ ባካሪ ከምርጫው በኋላ በተደጋጋሚ አሸንፌያለሁ ሲሉ ሰንብተዋል፡፡ ኢሣ ቺሮማ ባካሪ ውጤቱ በወጉ ይጣራልኝ ማለት መጀመራቸው ተሰምቷል፡፡ የ92 አመቱ አረጋዊ ፖል ቢያ የምርጫ ድላቸው ከፀናላቸው የ42 አመታት መሪነታቸውን በመ5 ዓመታት ይጨምርላቸዋል ተብሏል፡፡ የአገሪቱ ህገ መንግስታዊ ምክር ቤት ይፋዊ ውጤቱን ሰሞኑን እወቁት እንደሚል በመረጃው ተጠቅሷል፡፡
Oct 222 min read


ጥቅምት 12 2018 -ንፁህ የመጠጥ ውሃ የሚያገኘው ኢትዮጵያዊ ከ40 በመቶ በማይበልጥባት አትዮጰያ የውሃ ሀብት አያያዟን ዲጂታል በማድረግ በኩል ምን እየሰራች ነው?
አፍሪካ ውሃ ሀብቷን የምትረዳበት እና የምታስተዳድርበትን መንገድ ለመቀየር የሚያስችሉ የዲጂታል ፈጠራዎች፣ ቴክኖሎጂ እና መረጃ ላይ የሚመክር ሲምፖዚየም በአዲስ አበባ ከትናንት ጀምሮ እየተካሄደ ነው፡፡ በመድረኩ የመንግስት ተወካዮች፣ ሳይንቲስቶች እና የፈጠራ ባለሞያዎች ተገኝተዋል፡፡ ሲምፖዚየሙን ያዘጋጀው ዓለም አቀፉ የውሃ አስተዳደር፣ ከዲጂታል አፍሪካ እና ከሄልምስሌይ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተበባር መሆኑን ሰምተናል፡፡ ዘመናዊ የውሃ አስተደደር ላይ መምከር ከውሃ ጋር በተያያዘ ያለውን የመረጃ ክፍት ለመሙላት፣ በዚህም የምግብ ስርዓትን የተመለከቱ ውሳኔዎችና ኢንቨስትመንቶችን ለመደገፍ በማሰብ ነው ተብሏል፡፡ የ3 ቀናት ስብሰባው የሳተላይት መረጃ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና ዲጂታል መድረኮች ከውሃ ጋር በተያያዘ ሀገሮች ዕቅድ እንዲያሻሽሉ፣ የው
Oct 221 min read


ጥቅምት 11 2018 - ባህርዳር እና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች በኒኩለር ሳይንስ የሁለተኛ ዲግሪ ት/ት መስጠት መጀመራቸውን ተናገሩ
በኒኩለር ሳይንስ የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርት መስጠት መጀመራቸውን ሁለት ዩኒቨርሲቲዎች ተናገሩ፡፡ ትምህርቱን እየሰጡ ያሉት ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ናቸው፡፡ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ በተያዘው ዓመት ለመጀመርያ ጊዜ በ2ተኛ ዲግሪ ሲያስተምራቸው የነበሩ ተማሪዎች እንደሚያስመርቅ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት መንገሻ አየነ(ዶ/ር) ነግረውናል፡፡ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ደረጀ እንግዳ(ዶ/ር) በበኩላቸው ከሁለተኛ ዲግሪ ባለፈ የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት ለመስጠት ዝግጅት እያጠናቀቁ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ በቅርቡ መንግስትበ ኢትዮጵያ የኒኩለር ፕላንት ለሰላማዊ መንገድ እንደሚገነባ የተናገረ ሲሆን ሁለቱ ተቋማት ለዚህ የሚሆን ባለሞያ ለማፍራት ማቀዳቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. በረከት
Oct 211 min read


ጥቅምት 11 2018 የኢትዮዽያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን በተለያዩ ፕሮጀክቶች ላይ ትኩረት በማድረግ አለም አቀፍ ኩባንያ ለመሆን ጉዞ ጀምሬያለሁ አለ።
ኮርፖሬሽኑ በበፊቱ አዋጅ መሰረት ሶስት የተሰጡትን ግዙፍ የኢንቨስትመንት ክንውኖችን ለመፈፀም ወደ ስራ መግባቱን ተናግሯል። ኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን እፈፅማቸዋለው ካላቸው ግዙፍ ስራዎች፤ አንደኛው የምድር ባቡር መሰረተ ልማት ግንባታ፤ ሁለተኛ የተገነባውን የባቡር ልማት ማከናወን እና ሶስተኛው የመሰረተ ልማት አካል አስተዳደርና ተዛማጅ ስራዎች ናቸው። ኮርፖሬሽኑ ከዚህ በተጨማሪም በአዋጅ በተሰጠው በደረጃ አንድ ኮንትራክተር ፤ በደረጃ አንድ መልቲሞዳል አገልግሎት እንዲሁም በደረጃ አንድ የባቡር አካላት ማምረቻ እና ሌሎች ፈቃዶች ወደ ስራ ለመግባት ማሰቡን ሲናገር ሰምተናል። የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሸን ዛሬም የመንግስትና የግል ሽርክና በማስማማት ፋይናንስ ለማሰብሰብ ሲመክር ውሏል። ኮርፖሬሽኑ እነዚህን ግዙፍ ፕሮጀክቶች ለማልማት በሽርክና ማህ
Oct 212 min read


ጥቅምት 11 2018 - የጫኝ እና አውራጅ ጉዳይ
በአዲስ አበባ ከተማ አንዱ የነዋሪዎች ፈተና የጫኝ እና አውራጅ ጉዳይ ነው፡፡ አንድ ሰው ቤት ለመቀየር ፈልጎ እቃውን ሲያጓጉዝ ጫኝ እና አውራጆቹ እቃውን የምንጭነውም ይሁን የምናወርደው እራሳችን በምንተምነው ገንዘብ ነው እያሉ ነዋሪውን ሲያስመርሩት መመልከት የተለመደ ጉዳይ ከሆነ ውሎ አድሯል፡፡ ይህ ደግሞ ነዋሪዎችን ካለው የኑሮ ውድነት ጋር ተደማምሮ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሆነባቸው ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በየአካባቢው በህጋዊ መንገድ የተሰማሩ ጫኝ እና አውራጅን በዘመናዊ መልኩ የሚሰሩ ተቋማት በርከትከት እያሉ ነው፡፡ ከእነዚያም መካከል አንዱ መላ ሎጅስቲክስ ሰርቪስ ነው፡፡ መላ ሎጅስቲክስ ሰርቪስ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች አንዱ የሆነው የቤት ቅየራ አገልግሎት ወደ ስራ ከገባ የአንድ ዓመት እድሜ እንደያዘ የተነገረ ሲሆን የግለ
Oct 211 min read


ጥቅምት 11 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ፈረንሳይ የፈረንሳይ ሹሞች እጅግ ውድ የአገራችንን ቅርሶች ማስጠበቅ ተስኖናል ሲሉ በፀፀት ተናገሩ፡፡ የሹሞቹ አስተያየት የተሰማው በርዕሰ ከተማዋ ፓሪስ ከሚገኘው የሉቨር ቤተ መዘክር ውድ ጌጣ ጌጦች ከተሰረቁ በኋላ እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡ ጌጣ ጌጦቹ የአገሪቱ ቅርሶችም በመሆናቸው በዋጋ እንደማይታመኑ እየተነገረ ነው፡፡ ከተዘረፉት ቅርሶች መካከል የፈረንሳዩ ንጉሰ ነገስት ናፖሊዮን በናፖርት ለባለቤቱ አበርክቶለት የነበረ በአልማዝ የተንቆጠቆጠ ሐብልም ይገኝበታል ተብሏል፡፡ ዘራፊዎቹ ላይ በፍጥነት ካልተደረሰባቸው ቅርሶቹን በማወላለቅ በትንሽ በትንሹ ወደ ውጭ አገራት ሊያሸሿቸው ይችላሉ የሚል ስጋት አሳድሯል፡፡ የፓሪሱ ዘረፋ በመሰል ቤተ መዘክሮች የደህንነት ጥበቃው በእጅጉ እንዲጠናከር የማንቂያ ደወል ሆኗል ተብሏል፡፡ የቤተ መዘክሩ የቅርሶች ዘረፋ በአገሪቱ
Oct 212 min read


ጥቅምት 11 2018 - በኢትዮጵያ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ አርሶ አደሮችን እና አርብቶ አደሮችን በተለያየ መልኩ እየረዳ መሆኑን የአለም ምግብ ድርጅት ተናገረ።
የድርጅቱ የኢትዮጵያ ተወካይ ሙቲንታ አምባይ(ዶ/ር) ይህንን ያሉት ዛሬ በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል በተከበረው የአለም የምግብ ቀን ላይ ባደረጉት ንግግር ነው፡፡ ምርጥ ዘር እና ግብዓት በማቅረብ፣ የማጨጃ እና መውቂያ መሳሪያዎችን በመለገስ፣ በገንዘብ ድጋፍ፣ የገበያ ትስስር በመፍጠር እና በሰብል እና እንስሳት ኢንሹራንስ በሀገሪቱ ከ1.5 ሚሊየን በላይ አርሶ፣ አርብቶ እና ከፊል አርሶ አደሮችን እየደገፈ ነው ሲሉ አስረድተዋል። ካለፈው ጥር ጀምሮ ወደ 47,000 አርሶ አደሮች 35,000 ሄክታር በ5 ክልሎች እየለማ መሆኑን የተናገሩት የድርጅቱ የኢትዮጵያ ተወካይ ከዚህ ውስጥ ከ10,000 በላይ የሚሆነው በመስኖ እየለማ ነው ብለዋል። ምርታማነትን ማሳደግ፣ ገቢን በመጨመር ማህበረሰቡን ከጥገኝነት የማውጣት ስራ ከመንግስት እና ከሌሎች መንግስታዊ ካልሆኑ
Oct 211 min read


ጥቅምት 11 2018 - ክፍት የተተዉ ጉድጓዶች
በአዲስ አበባ በየጎዳናው ክዳናቸው ተሰርቆ ወይም ተሰብሮ ክፍት የተተዉ ጉድጓዶች ለተለያየ አደጋ ምክንያት መሆናቸውን ቀጥለዋል፡፡ በየዓመቱ 6,000 ክዳኖች እየተዘጋጁ ለአደጋ የሚያጋልጡ ጉድጓዶች እየተከደኑ ቢሆንም አሁንም ስርቆቱ የቀጠለ በመሆኑ ችግሩን መቅረፍ አዳጋች ሆኗል ተብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ገዛ ጌታሁን የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s 🐦X : https://x.com/sheg
Oct 211 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page








