ዳሸን ባንክ ከአንድ ዓመት በፊት ባስጀመረው የሴቶች የአቅም ግንባታ መርሀ ግብር ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት አካሄደ።
- sheger1021fm
- 15 minutes ago
- 1 min read
ጥር 14/2018
ዳሸን ባንክ ከአንድ ዓመት በፊት ባስጀመረው የሴቶች የአቅም ግንባታ መርሀ ግብር ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት አካሄደ።
በተለያዩ የስራ ዘርፎች የተሰማሩ ሴት ሰራተኞቹን አቅም ለማጎልበትና ወደከፍተኛ የአመራር ሃላፊነቶች ለማሳደግ ያለመውና ለአንድ ዓመት ያህል ሲተገበር በቆየው አጠቃላይ የሴቶችን አቅም የማጎልበት መርሃ-ግብር (Comprehensive Women Empowerment Program) ላይ ያተኮረ ውይይት አካሂዷል።
ባንኩ ከአንድ አመት በፊት የሴቶች አቅም ግንባታ መርሃ ግብርን ማስጀመሩ ይታወሳል።

በአንድ አመት ጊዜም ከ140 በላይ የሚሆኑ ሴት የባንኩ ባልደረቦች በዚህ መርሃግብር የመሳተፍና በተለያዩ መንገዶች አቅማቸውን የማጎልበት እድል አግኝተዋል ብሏል።
በዚህ መርሃ-ግብር በአንድ ዓመት ሶስት የትስስርና ውይይት መድረኮች የተካሄዱ ሲሆን በእያንዳንዱ የውይይት መድረክ ላይ ከ200 በላይ ታዳሚዎች መሳተፋቸውን የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው አለሙ ተናግረዋል።
ሴቶች በዚህ መድረክ አማካኝነት የሚያገኟቸው የአመራር ክህሎትና አቅም ግንባታ ስልጠናዎች ለባንኩ ስኬት የሚኖረው አስተዋፅኦ ከፍተኛ ስለሆነ ይህ አይነቱ መርሀ ግብር ለወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አንስተዋል።
በአሁኑ ሰዓት ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ሴቶች በተለያዩ የአመራር እርከኖች እያገለገሉ መሆኑን ያነሱት አቶ አስፋው ዓለሙ በባንኩ ካሉት ከ11 ሺ በላይ ቋሚ ሰራተኞች ከ3300 በላይ የሚሆኑት ሴቶች ናቸው።
ፋሲካ ሙሉወርቅ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…..
YouTube : https://url-shortener.me/2DTR
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://url-shortener.me/2DTY
WhatsApp :https://url-shortener.me/2DU0
Website፡ https://www.shegerfm.com/
LinkedIn :https://url-shortener.me/2DU8
Tiktok : https://url-shortener.me/2DUB
Instagram : https://url-shortener.me/2DUD











Comments