ለኢመደበኛ ፍለሰቱ ትልቁ ምክንያት ተደረጎ የተነሳውም ድህነት ነው፡፡
- sheger1021fm
- 3 minutes ago
- 1 min read
ጥር 12/2018
በአንዳንድ አካባቢዎች የሀይማኖት መሪዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች ሳይቀር ወጣቶችን ወደ ስደት መርቀው መሸኘታቸው ኢመደበኛ ፍልሰትን ከሚያስፋፉ ምክንያቶች አንዱ ሆኖ ቀጥሏል ሲል የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ፡፡
እነዚህ አካላት ይህንን የሚያደርጉትም በኢመደበኛ ስደት ወጣቶች የሚደርስባቸው አደጋ እና ስቃይ ካለለመገንዘብ ነው ብሏል፡፡
በየአካባቢው ‘’የእከሌ ልጅ እኮ ያለፈለት እና ለቤተሰቦቹም ኤፍኤስአር(FSR) መኪና የገዛው ስደት ሄዶ ነው’’ በሚሉ እና መሰል ማበረታቻዎች ወጣቶች ለኢመደበኛ ፍልሰት እየተዳረጉ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡
ይህ የተነገረው የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የአካል ጉዳተኞች፣ የአረጋውያን፣ የማህበራዊ ጥበቃ መብቶች፣ ኢመደበኛ ፍልሰትን እና ቤተሰብን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ለሚዲያ ባለሞያዎች በአዳማ ከተማ ባዘጋጀው የግንዛቤ መስጫ መድረክ ላይ ነው።
በተለይ አሁን አሁን ህጋዊ የሚመስለው ኢመደበኛ ፍልሰት በረቀቁ የማታለያ ዘዴዎች በመታጀቡ፣ ከፍተኛ ደመወዝ የሚያገኙ ባለሞያዎች ጭምር ስራቸውን ትተው ያላቸውን ሁሉ ከፍለው እንደሚታለሉ ተነግሯል፡፡
በኢመደበኛ መልኩ በመፍለስ ላይ እያሉ በአንድ ጊዜ ሰላሳ አርባ ሞተው የሚገኙበት ወቅት መኖሩንም ተጠቅሷል፡፡
ለኢመደበኛ ፍለሰቱ ትልቁ ምክንያት ተደረጎ የተነሳውም ድህነት ነው፡፡
ከድህነት በተጨማሪም የተሻለ ገቢ ያላቸው ሰዎች የሚፈልሱትም በተሳሳተ መረጃ የተነሳ ነው እንደሆነ ተነግሯል፡፡
ለመሆኑ በየጊዜው እየተደጋገመ አስከፊነቱ የሚወራለት ኢመደበኛ ፍለሰትን ለመቀነስ ምን እየሰራ እንደሆ የተጠየቀው የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እስከ ወረዳ እና ቀበሌዎች ድረስ ባሉ መዋቅሮች ግንዛቤ እየሰጠ እንደሆነ አስረድቷል፡፡
ባለፉት 3 ዓመታት በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከግማሽ ሚሊዮን በበላይ ኢትዮጵያዊንን ወደ ሀገር እንደተመለሱ ተነግሯል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….
ማንያዘዋል ጌታሁን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…..
YouTube : https://url-shortener.me/2DTR
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://url-shortener.me/2DTY
WhatsApp :https://url-shortener.me/2DU0
Website፡ https://www.shegerfm.com/
LinkedIn :https://url-shortener.me/2DU8
Tiktok : https://url-shortener.me/2DUB
Instagram : https://url-shortener.me/2DUD











Comments