top of page

ደህንነቱ ያልተጠበ ከ13 ሺህ ኩንታል በላይ የጨው ምርት በክትትል መያዙን የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ተናገረ።

  • sheger1021fm
  • 3 hours ago
  • 1 min read

ጥር 13/2018


ደህንነቱ ያልተጠበ ከ13 ሺህ ኩንታል በላይ የጨው ምርት በክትትል መያዙን የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ተናገረ።


ባለስልጣኑ ይህንን ያለው ከብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት ጋር በትብብር በመሆን በህብረተሰቡ ላይ የጤና ጉዳት የሚያስከትሉ ምርቶችን በተመለከተ የወሰደውን ርምጃ አስመልክቶ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ ላይ ነው።


የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ነጋሸ ስሜ እነዚህ የተያዙ የጨው ምርቶች ለጤና ጎጂ መሆናቸው በላብላቶሪ ተረጋግጧል ብለዋል።


የጨው ምርቶቹ በተለይም በአስገዳጅነት ማሟላት ያለባቸውን የአዮዲን መጠን ሳያሟሉ የቀሩ ናቸው ተብሏል።


በህጉ መሰረት የጨው ምርት ለገበያ ከመቅረቡ በፊት በተመጠነ አዮዲን መበልፀጉ መረጋገጥ አለበት ተብሏል።


አሁን ተያዙ የተባሉ የጨው ምርቶች አንዳንዶቹ ከሚገባው መጠን በላይ አንዳንዶቹ ደግሞ ከመጠን ያነሰ የአዮዲን መጠን የተገኘባቸው ናቸው ብሏል ተቋሙ።


ለጤና ጎጂ ሆነው ተገኝተዋል የተባሉት የጨው አምራቾች 3 ሲሆኑ በስምም አፋር፣ አፍዴር ወለላ እና በርዋቅ እንደሚባሉ ይፋ አድርጓል።


ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ለጤና አስጊ እንደሆነ የጠረጠረው ምርት ካለ በ 8482 ይጠቁመኝ ብሏል።


ማንያዘዋል ጌታሁን

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page