top of page

በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የግል አየር መንገዶች ለአውሮፕላኖቻቸው ጥገና በዓመት እስከ 800,000 ዶላር ያወጣሉ ተባለ፡፡

  • sheger1021fm
  • 5 hours ago
  • 1 min read

ጥር 6/2018

 

በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የግል አየር መንገዶች ለአውሮፕላኖቻቸው ጥገና በዓመት እስከ 800,000 ዶላር ያወጣሉ ተባለ፡፡

 

አየር መንገዶቹን ከዚህ ወጪ፣ የውጭ ሀገር ጉዞና እንግልት ለማዳን ያግዛል የተባለ አገልግሎት እንዲሰጥ ለኢትዮጵያ አየር ሀይል የአውሮፕላን ጥገና ፈቃድ ተሰጥቶታል፡፡

 

በኢትዮጵያ ያሉ የግል አየር መንገዶች በቁጥር አስራ ሁለት መድረሳቸው ተነግሯል።

 

የነዚህ አየር መንገዶች ንብረት የሆኑ መካከለኛና አነስተኛ አውሮፕላኖች ጥገና ሲፈልጉ አገልግሎቱን የሚሰጣቸው እራሱን የቻለ የጥገና ማዕከል በሀገር ውስጥ አልነበረም ተብሏል።

 

በዚህም ምክንያት ለጥገና አገልግሎት ወደ ኬንያና ሌሎችም ሀገሮች ለመጓዝ እንደሚገደዱ ተሰምቷል።

 

ይህም ብዙ ወጪን የሚያስወጣቸው አቅማቸውንም የሚፈታተን መሆኑን ሰምተናል።

 

አሁን ግን ይህንን በሂደት ሙሉ ለሙሉ የሚያስቀር ስራ መጀመሩ፤ የመጀመሪያው እውቅናም ለአየር ኃይል መሰጠቱ ተነግሯል።

 

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣንንም ስለዚሁ እውቅና ጠይቀናል።

 

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….

 

ቴዎድሮስ ወርቁ

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…..

 

X : https://x.com/shegerfm?s=2                 

Website፡ https://www.shegerfm.com/                           

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page