ከጉዞ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ያቀላል፣ የቱሪዝም ዘርፉንም ያበረታዋል ተብሎ የተነገረለት የዲጂታል መላ ስራ መጀመሩ ተነገረ።
- 20 hours ago
- 1 min read
ሰኔ 19/2018
ከጉዞ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ያቀላል፣ የቱሪዝም ዘርፉንም ያበረታዋል ተብሎ የተነገረለት የዲጂታል መላ ስራ መጀመሩ ተነገረ።
“ዛጎል” በሚል መጠሪያ የቀረበው የጉዞ መተግበሪያ ትላንት ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ተመርቆ ሥራ መጀመሩን ከተላከልን መግለጫ ላይ ተመልክተናል ።

“ዛጎል” ሱፐር አፕ በተለይም የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ ተጓዦች የአውሮፕላን ጉዞዎችን በቀላሉ በኦን ላይን ማስተናገድ የሚያስችላቸው መድረክ ነው ተብሏል።
መተግበሪያው ተጠቃሚዎች የጉዞ እቅድ ማውጣት ፣ ቦታ መያዝ (Booking) እና ተያያዥ የጉዞ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ ታስቦ የተሰራ መሆኑ ተጠቅሷል።
ዛጎል ሁሉንም የጉዞ ፍላጎቶች በአንድ መተግበሪያ መያዝ መቻሉ፣ በ7 የተለያዩ ቋንቋዎች ይሰራል፣ ለአጠቃቀምም ቀላል ነው ተብሏል።
"ዛጎል መተግበሪያ ደንበኞች ካሉበት ሆነው ያለምንም እንግልት የጉዞ ፍላጎቶቻቸውን በሰከንዶች ውስጥ እንዲያሳኩ የሚያስችል ነው" ሲሉ የድርጅቱ የደንበኞች አገልግሎት ሀላፊ ወ/ሮ ሙና ሱልጣን መናገራቸው ተጠቅሷል።
ንጋቱ ሙሉ

