top of page

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሶስት የመንግስት መስሪያ ቤቶች ለሚሰጡት አገልግሎት ክፍያዎችን ለመወሰን የወጣ ደንብ በስራ ላይ እንዲውል ወሰነ፡፡

  • 23 hours ago
  • 1 min read

ሰኔ 19/ 2018


የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሶስት የመንግስት መስሪያ ቤቶች ለሚሰጡት አገልግሎት ክፍያዎችን ለመወሰን የወጣ ደንብ በስራ ላይ እንዲውል ወሰነ፡፡


የሚኒስትሮች ምክር ቤት ይህን የወሰነው ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ ነው፡፡


ሶስቱ ተቋማት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ቤተ መፅሐፍትና ቤተ መዛግብት እና የትምህርት ፈተናዎች አገልግሎት ናቸው፡፡



የሚኒስትሮች ምክር ቤት በስብሰባው ሶስቱ ተቋማት ለሚሰጧቸው አገልግሎቶች በውስጥ ገቢ የሚሸፈኑ ወጪዎችን ከአገልግሎት ተጠቃሚዎች በመሰብሰብ እንዲጠቀሙ የወጣውን ደንብ በነጋሪት ጋዜጣ ከታተመ ቀን ጀምሮ ስራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡


በተጨማሪም አንድ የብድር ስምምነት እና ኒው ዴቨሎፕመንት ማቋቋሚያ ባንክ ስምምነት ማፅደቂያ ረቂቅ አዋጅን ወደ ሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት መርቷል፡፡


ያሬድ እንዳሻው

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page