የግብርና ፖሊሲው የአርብ አደሮችን አኗኗር እምብዛም ከግምት ያስገባ እንዳልሆነ የዘርፉ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡
- 4 days ago
- 1 min read
ሰኔ 19/ 2018
የግብርና ፖሊሲው የአርብ አደሮችን አኗኗር እምብዛም ከግምት ያስገባ እንዳልሆነ የዘርፉ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡

በዚህም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋምና ሌሎች አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ለማለፍ ይቸገራሉ ተብሏል፡፡
እነሱን የተመለከቱ ህጎችም ቢኖሩ ስለሚጣሱ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰድ ተጠይቋል፡፡
ይህንን አስመልክቶ ላንድ ፎር ላይፍ-ኢትዮጵያ ከአገራዊ የመሬት ጥምረት-ከኢትዮጵያ ጋር በመሆን በአርብቶ አደር መሬት ይዞታ መብት በግጦሽ መሬት አስተዳደር እና በአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም ዙሪያ ላይ ያተኮረ ውይይት አድርጓል።
ይህ የፖሊሲ ውይይት የመሬት ይዞታ አስተዳደርን ለማጠናከር የወጣው አዋጅ ላይ ትኩረት በመስጠት እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለመፍጠር ዕድል ይፈጥራል መባሉንም ሰምተናል።
እንደሰማነው በኢጋድ ቀጠና ውስጥ ከ50 ሚሊዮን በላይ አርብቶ አደሮች የሚገኙ ሲሆን ይህም የአፍሪካን አጠቃላይ የአርብቶ አደር ሕዝብ 21 በመቶ ይሸፍናል ተብሏል::

ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….
ማርታ በቀለ




Comments