ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ባለፉት 10 አመታት ሲሰጥ የቆየው ከወለድ ነፃ "ንብ ሃላል" የባንክ አገልግሎት ጥሩ ውጤት ያስመዘገበ ነው አለ።
- 6 hours ago
- 1 min read
ሰኔ 22/2018
ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ባለፉት 10 አመታት ሲሰጥ የቆየው ከወለድ ነፃ "ንብ ሃላል" የባንክ አገልግሎት ጥሩ ውጤት ያስመዘገበ ነው አለ።

ለዚህም የ10 አመታት ውጤት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ደንበኞቹ እና ሰራተኞቹ እውቅና ተሰጥቷቸዋል።
ይህ ማለት ግን የተሰራው ስራ በቂ ነው ማለት አይደለም ያለው ባንኩ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎትን በተመለከተ ካለው የደንበኞች ፍላጎት አንፃር ከዚህ በላይ መስራት እንዳለብን ይጠቁመናል ብሏል።
ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ይህንን ያለው ባለፉት 10 አመታት "ንብ ሃላል" ከወልድ ነፃ የባንክ አገልግሎት መስጠት የጀመረበትን 10ኛ አመት ክብረ በዓል ማጠቃለያ መርሃ - ግብር ባካሄድበት ወቅት ነው።
ባንኩ "ንብ ሃላል" ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት መስጠት የጀመረበትን 10ኛ አመግ ክብረ-በዓል ላለፉት ስድስት ወራት በተለያዩ ሁነቶች ሲያከብር መቆየቱን የተናገረ ሲሆን የማጠቃለያ ዝግጅቱን ዛሬ አካሂዷል።
በማጠቃለያ መርሀ-ግብሩ በተደረገው የንብ ሀላል የ10 አመታት ጉዞ ሂደት አገልግሎቱ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ያስመዘገባቸውን ውጤቶች፣ የደንበኞች ቁጥር እና የተቀማጭ ገንዘብ መጠን ዕድገት በተመለከተ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
በቴክኖሎጂ የተደገፉ አዳዲስ የቁጠባ ሂሳቦችንና በዲጅታል አማራጮች የተጀመሩ እንቅስቃሴዎችን በማጠናከር ወደፊት አገልግሎቱን አዘምኖ ለማቅረብ እየሰራ መሆኑን ያነሳው ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ የደንበኞችን ፍላጎት መሰረት ያደረገና የሸሪዓ መርሆችን የጠበቁ አገልግሎቶችን አጠናክሮ ለመስጠን ማቀዱን ተናግሯል።
ባንኩ የ"ንብ ሃላል" አገልግሎቱን በሁሉም መደበኛ እና ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ አገልግሎት በሚሰጡ ቅርንጫፎቹ አማካይነት ለደንበኞች ተደራሽ እንዲሆን እያደረኩ ነው ያለ ሲሆን ታህሳስ 8 ቀን 2008 ዓ.ም የጀመረውን የንብ ሀላል አገልግሎት መለያ በአዲስ መልክ አዘጋጅቻለሁ በቅርቡም ይፋ አደርጋለሁ ብሏል።
ፋሲካ ሙሉወርቅ




Comments