top of page


ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ስምምነት ምክንያት የውጪ ባለሃብቶች ለኢንቨስትመንት እየመረጧት ነው ተባለ
ህዳር 5 2018 ኢትዮጵያ ከወር ግድም በፊት በይፋ በተቀላቀለችው የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ስምምነት ምክንያት የውጪ ባለሃብቶች ለኢንቨስትመንት እየመረጧት ነው ተባለ። በስምምነቱ መሰረት ወደ ተለያዩ ሀገራት የሚላኩ ምርቶች ጥራታቸውን የጠበቁ ስለመሆናቸው ጥብቅ የማረጋገጥ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ነግሮናል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠናን ባለፈው መስከረም ወር መጨረሻ በይፋ መቀላቀሏ ይታወሳል። ወደ አራት የአፍሪካ ሀገራት ምርቶችን በአየር እና በየብስ ትራንስፖርት በመላክ ነው የንግድ ቀጠናውን የተቀላቀለችው። በአየር ትራንስፖርት የተላኩት ስጋ እንዲሁም የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶች ሲሆኑ ፤በየብስ ትራንስፖርት ደግሞ የተላኩት ቡና፣ የጥራጥሬ ምርቶችና የቅባት እህሎች ናቸው። ኬንያ
4 days ago2 min read


የኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚገኙ ሠራተኞች መብታቸው ለማረጋገጥ የሚደረገው ክትትል እንደሚጠናከር የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ተናገረ
ህዳር 5 2018 በተለያዩ የኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች የሚገኙ ሠራተኞች መብታቸው ተከብሮ እየሰሩ ስለመሆናቸው ለማረጋገጥ የሚደረገው ክትትል እንደሚጠናከር የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ተናገረ። ከሠሞኑ በሃዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በአንድ ኢትዮጵያዊ ሠራተኛ ላይ ድብደባ የፈጸመ አንድ የውጪ ዜጋ እና የቅርብ ሃላፊው የስራ ውላቸው ተቋርጦ ከሀገር እንዲወጡ መደረጉን ኮርፖሬሽኑ ጨምሮ ተናግሯል። በኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መብታቸው ተከብሮ እየሰሩ ስለመሆናቸው ለማረጋገጥ ፤ የሚደረገው ክትትል በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ተናግሯል። ኮርፖሬሽኑ ከሠሞኑ በሃዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በአንድ ኢትዮጵያዊ ሠራተኛ ላይ የተፈጸመውን ጥቃት መ
4 days ago1 min read


የሚበዙት ባንኮች ከመደበኛ ስራቸው ውጪ በሆኑ ሌሎች ተግባራት መሰማራታቸው
ህዳር 4 2018 የባንኮች በአቅምም፣ በአገልግሎት ጥራትም ልቀው የመገኘት ሀሳብ በየጊዜው ይነሳል። ባንኮች ወደፊት ለሚመጣው ፉክክር ዝግጁ መሆን አለባቸው ይባላል። በሌላ በኩል የሚበዙት ባንኮች ከመደበኛ ስራቸው ውጪ በሆኑ ሌሎች ተግባራት ሲሰማሩ ይታያል። በኢ-ኮሜርስ፣ በትምህርት ዘርፍ፣ በሎጅስቲክስና በሌላው መፎካከራቸው በዝቶ እየታየ ነው። የክፍያ ሥርዓትን ማገዝ የሚጠበቅባቸው ባንኮች፣ ሶፍትዌር አበልፅገው በተለያየ ንግድና አገልግሎት ውስጥ ሲሳተፉ ይታያል። ይህም የተቋቋሙበት ዓላማ ይህ ነው ወይ? የሚል ጥያቄን ያስነሳል። ባንኮች ከድንችና ሽንኩርት ሽያጭ እስከ ሎጅስቲክ ዘርፍ ገብተው ሲሰሩ ይታያል፡፡ የባንክ ስራውን ከማሳደግና ማቀላጠፍ ወደዚህ ዓይነት ስራ ውስጥ መግባታቸው ምን ይዞ ይመጣል? ባለሙያ ጠይቀናል። ሙሉ
5 days ago1 min read


በኢትዮጵያ የተፈቀደላቸው የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች 89 መሆናቸውን ብሔራዊ ባንክ ተናገረ፡፡
ህዳር 3 2018 በኢትዮጵያ የገንዘብ ማስተላለፍ አገልግሎት እንዲሰጡ የተፈቀደላቸው የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች 89 መሆናቸውን ብሔራዊ ባንክ ተናገረ፡፡ ቀደም ሲል የገንዘብ ማስተላለፍ አገልግሎት እንዳይሰጥ ታግዶ የነበረውና ዋና መስሪያ ቤቱ በአሜሪካ ቨርጂኒያ ግዛት በፎልስ ቸርች የሚገኘው ራማዳ ፔይ(ካህ) በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ አጠቃላይ ግምገማ ከተካሄደ በኋላ በሕጋዊ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች ስም ዝርዝር ውስጥ ዳግም እንዲካተት መደረጉን ባንኩ በመግለጫው ጠቅሷል። ራማዳ ፔይ በሕጋዊ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች ስም ዝርዝር ውስጥ ዳግም እንዲካተት የተደረገው አስፈላጊው የቁጥጥርና የክትትል ሂደት ከተጠናቀቀ በኋላ መሆኑን ተነግሯል። በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ አገልግሎት እንዳይሰጡ ታግደው የሚገኙ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች በሙሉ የሀገሪቱ
6 days ago1 min read


የኢኮኖሚ ድርጅቶችን እንዲቆጥሩ 40,000 ወጣቶች ተሰማርተዋል ተባለ፡፡
ህዳር 2 2018 በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የኢኮኖሚ ድርጅቶችን እንዲቆጥሩ 40,000 ወጣቶች ተሰማርተዋል ተባለ፡፡ ይህንን ያለው የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ነው፡፡ አገልግሎቱ ድርጅቶቹን እንዲቆጥሩልኝ ያሰማራኋቸው ወጣቶች ሁሉም የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ናቸው ብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት ከጥቅምት 1 ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 2018 ዓ.ም ድረስ በኢትዮጵያ የሚገኙ ሁሉም አይነት የኢኮኖሚ ድርጅቶች መረጃ የመቁጠር ስራ እየከወነ እንደሆነ ተናግሯል፡፡ በዚህ ቆጠራ በኢትዮጵያ የሚገኙ የኢኮኖሚ ድርጅቶ ብዛት፣ በምን ዘርፍ እንደተሰማሩ፣ ያላቸው የሰው ሀይል፣ የሚገኙበት ቦታ፣ የሚጠቀሙት የግብዓት ዓይነት መጠንና ምንጭ፣ የምርት ሽያጮቻቸውና ምን ያህል ኤክስፖርት እንደሚያደርጉ እንዲሁም በስራቸው የሚገጥሟቸው ችግሮች ይመዘገባል
Nov 112 min read


አዋሽ ባንክ የመስመር ዲጂታል የብድር አገልግሎት ይፋ ማድረጉን ተናገረ።
ጥቅምት 28 2018 አዋሽ ባንክ የመስመር ዲጂታል የብድር አገልግሎት ይፋ ማድረጉን ተናገረ። ባንኩ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በዲጂታል መተግበሪያ በኩል የብድር አገልግሎት ማቅረብ የሚያስችል '"መስመር ዲጂታል የብድር አገልግሎት" በአዋሽ ብር ፕሮ መተግበሪያ በኩል አቅርቧል ተብሏል። ባንኩ ይህንን መተግበሪያ ይፋ ያደረገው ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን እና ከፈርስት ኮንሰልት ጋር በመተባበር እንደሆነ ተናግሯል። አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በሙሉ አቅማቸው እንዳይወጡ እና ስራዎችን እንዳይከውኑ ከሚያደርጓቸው ችግሮች መካከል የብድር አገልግሎት አለማግኘት አንዱ መሆኑን የአዋሽ ባንክ ሲኒየር ችፍ ማርኬቲንግ ኦፊሰር የሆኑት አቶ ዮሀንስ መርጋ አንስተዋል። ለዚህ ችግር መፍትሄ ለመስጠት ደግሞ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የብድር አገልግ
Nov 71 min read


ገበያው ልቅ ነፃነት ሳይሆን የመንግስትን ጥብቅ ቁጥጥር ያሻል ተብሏል
ጥቅምት 27 2018 የአንዳንድ ምርቶች ዋጋ ባልታወቀ ምክንያት ሁለትና ሶስት እጥፍ ሲያድግ ሌላ ጊዜ ደግሞ በዛው ልክ ሲወርድ ይታያል፡፡ የደላሎች ጣልቃ ግብነት እና የመንግስት የቁጥጥር ማነስ እንዲህ ላለው ያልተረጋጋ ዋጋ ምክንያቶች መካከል እንደሆኑ ባለሙያዎች ይነገራሉ፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገራትም ገበያው ልቅ ነፃነት ሳይሆን የመንግስትን ጥብቅ ቁጥጥር ያሻል ተብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… ንጋቱ ረጋሣ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬Wh
Nov 61 min read


ለአበባ፤ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት በቂ መሬት እንዲቀርብ ከመንግስት ጋር ውይይት ተጀምሯል ተባለ
ጥቅምት 25 2018 ለአበባ፤ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት በቂ መሬት እንዲቀርብ ከመንግስት ጋር ውይይት ተጀምሯል ተባለ። በዘርፉ መሰማራት የሚፈልጉ ብዙ የሀገር ውስጥ እና የውጪ ባለሃብቶች እንዳሉም ተነግሯል። የአበባ ፤ አትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ አሁን ላይ በዓመት በአማካይ ከ500 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ ለኢትዮጵያ እንደሚያስገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። ከሁለት መቶ ሺህ ለሚበልጡ ሰዎች የስራ ዕድል መፍጠሩንም የኢትዮጵያ አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ አምራቾች እና ላኪዎች ማህበር ተናግሯል። በ2.45 ሚሊዮን ሔክታር መሬት ላይ እየተካሄደ ያለ ልማት መሆኑም ተጠቅሷል። በዘርፉ የተሰማሩ ባለሃብቶች ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን እየተጠቀሙ መሆናቸውን የሚናገሩት የማህበሩ ዋና ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ ዘውዴ ፤ አለም አቀፍ ደረጃዎችን አሟልቶ ለመገኘትም ጥረት እያደ
Nov 41 min read


ጥቅምት 21 2018 - በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ጦርነቶች ቆመው እውነተኛ እርቅ እና ሰላም እንዲወርድ የንግዱ ማህበረሰብ ጠየቀ፡፡
ነጋዴዎቹ ይህን የጠየቁት ትናንት "የንግድ ሚና ለሰላም ግንባታ'' በሚል ሀሳብ አዲስ አበባ የንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ባሰናዳው የፓናል ወይይት ላይ ነው። የውይይቱ ተሳታፊ አደም ካሚል (ረ/ፕ) ኢትዮጵያ የምትታወቅበት የረዥም ጊዜ ታሪኳ ፍትህ እና ሰላም እንደሆነ አስረድተዋል። ያ ባይሆን ኖሮ ነብዩ ሞሀመድ ለችግር የተጋለጡ ወገኖቻቸውን ወደ ኢትዮጵያ አይልኩም ነበር ይህም የምንኮራበት ታሪክ ነው ሲሉ አስታውሰዋል። ትናንት የፍትህ እና የሰላም ሀገር ከሆነች ዛሬ ምን ተፈጥሮ ነው? ችግሩ ምንድነው? የሚለውን ምሁራን እና የሃይማኖት አባቶች ትኩረት አድርገው በጥናት ሊለዩት ይገባል ብለዋል። ሌላ የውይይቱ ተሳታፊ መሳሪያ አንስተው እየታገሉ ያሉት የእኛው እህት ወንድሞቻችን ናቸው በስልጣን ላይ ያሉትም እንደዛው የእኛው ናቸው እያፋጁን
Oct 313 min read


ጥቅምት 20 2018 የዳሸን ሱፐር አፕ ደንበኞች ቁጥር ከ1 ሚሊዮን በላይ መድረሱን ባንኩ ተናገረ።
የዳሸን ሱፐር አፕ አንድ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠር ደንበኛና በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዕለታዊ የገንዘብ ዝውውር እየተፈፀመበት ይገኛል ሲለሰ ባንኩ ከላከልን መግለጫ ላይ ተመልክተናል፡፡ ይህንን በዛሬው ዕለት በዳሸን ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላትና የሥራ ክፍሎች የእውቅና አሰጣጥና የፓናል ውይይት መርሃግብር መዘጋጀቱም ተጠቅሷል፡፡ የዳሸን ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ዓለሙ፣ ዳሸን ሱፐር አፕ ይፋ በተደረገ አንድ ዓመት ውስጥ አንድ ሚሊዮን ተጠቃሚዎች ይኖሩታል የሚለውን ዕቅድ በዘጠኝ ወራት ብቻ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል። የዳሸን ሱፐር አፕን ላበለፀገው የኤግላይን ሲስተም ቴክኖሎጂ ለባንኩና ለአገር ለሚያደርገው አስተዋፅኦ አቶ አስፉው ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ዳሸን ባንክ ‘’ሱፐር አፕ’’ ባንኩ
Oct 301 min read


ጥቅምት 19 2018 - ኢንፊኒክስ ኢትዮጵያ ከተግባረ ዕድ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡
ኢንፊኒክስ ኢትዮጵያ የአዲስ አበባ ተግባረ ዕድ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተማሪዎቸን የተግባር ላይ ልምምድ ለመስጠት አንዲሁም መምህራኑን ለማሰልጠን የመግባቢያ ስምምነት ከኮሌጁ ጋር ተፈራረመ፡፡ ስምምነቱን የኮሌጁ ዲን ተስፋዬ አድማሱ(ዶ/ር ) እና ትራንሽን ማኑፋክቸሪንግ በመወከል Guo ZhongLei ተፈራርመውታል፡፡ በስምምነቱ መሰረት ኢንፊኒክስ ክለብ በተግባረ ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ይቋቁማል፣ ይህም ለተማሪዎች ለተግባራዊ የኢንዱስትሪ ልምድ፣ ለክህሎት ግንባታ እና ለፈጠራ ፍለጋ እድሎችን ይሰጣል ተብሎለታል። በዚህ ትብብር ተማሪዎች በግል እና ሙያዊ እድገት ላይ ያተኮሩ ስለጠናዎቸን እና የማማከር ፕሮግራሞች ውስጥ ይሳተፉሉ፣ በኢንፊኒክስ እና ትራንሽን ባለሙያዎች የፈጠራ ተነሳሽ ትምህርት ይሳተፉሉ። ከዚህ በተጨማሪም የኮሌጁ ተማሪዎች በትራንሽን እና ኢንፊ
Oct 291 min read


ለአፍሪካ አህጉራዊ የጉምሩክ ምስረታ ኢትዮጵያ ምን ይጠበቅባታል?
ጥቅምት 18 2018 በአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጠና ውስጥ በረዥም ጊዜ ይተገበራሉ ከተባሉት መካከል አንዱ አህጉራዊ የጉምሩክ ህብረት ምስረታ ይገኝበታል፡፡ ንግዱን ለማቀላጠፍ የመጀመሪያው የጉምሩክ እንቅስቃሴና ነፃነት አንዱ እንደሆነ በተደጋጋሚ ይነገራል፡፡ ዘርፉ ብዙ ችግሮች እንዳሉበት ባለሞያዎችና ነጋዴዎች ቅሬታቸውን ያሰማሉ፡፡ ታዲያ ከዚህ በመነሳት ለአፍሪካ አህጉራዊ የጉምሩክ ምስረታ በዘርፉ ኢትዮጵያ ምን ይጠበቅባታል ስንል የኢኮኖሚ ባለሞያን ጠይቀናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ማርታ በቀለ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/S
Oct 281 min read


ጥቅምት 14 2018 - የባንክ ደንበኞች ከሚመለከተው ግብር ሰብሳቢ ከሰጣቸው ሂሳብ ውጪ በግላቸው ሂሳብ ግብይቶች እንደሚገላበጥ ተሰማ
ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የባንክ ደንበኞች ከሚመለከተው ግብር ሰብሳቢ ከሰጣቸው ሂሳብ ውጪ በግላቸው ሂሳብ የተለያዩ ግብይቶች እንደሚገላበጥ ተሰማ። ይህን ያረጋገጠው የኢትዮዽያ ብሔራዊ ባንክ ነው። ባንኩ ባደረግሁት ምርመራ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ግለሰብ ነጋዴዎች በዚህ እንቅስቃሴ እንዳሉ አውቄያለሁ ብሏል። #የኢትዮጵያ_ብሔራዊ_ባንክ የተለያዩ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰብ ነጋዴዎች የግብር ሰብሳቢ ተቋም ካስመዘገቡት የባንክ ሒሳቦች ውጪ ወደ ግል እና ሶስተኛ ወገን የገንዘብ እንቅስቃሴዎች እየፈፀሙ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል። ይህ አሰራርም ከግብር ሰብሳቢ ባለስልጣናት ቁጥጥር እና ክትትል ለመሸሽ የሚደረግ ተግባር እንደሆነ ባንኩ አስረድቷል። በተጨማሪም በዚህ መልኩ የሚፈፀሙ የፋይናንስ ግብይቶች እና የገንዘብ እንቅስቃሴዎች የወንጀል ፍሬ ሊሆኑ እንደሚችሉ ባ
Oct 241 min read


ጥቅምት 14 2018 - ሕብረት ባንክ ከሚሰጠው ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የሰበሰበውን 35 ሚሊየን ብር ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች አበረከተ
35 ሚሊዮን ብሩ የተሰጠው ለ10 የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ነው፡፡ ድጋፍ የተርገላቸው አስሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች የተመረጡት በሸሪዓው መርህ መሰረት የሚሰሩ መሆናቸው ተመዝኖ፣ ከሚደርሱት የሕብረተሰብ ቁጥር እና የሚሰጠውን ድጋፍ ለምን ተግባር እንደሚያውሉትም ጭምር ታይቶ ነው ተብሏል። ድጋፉ ከተደረገላቸው ድርጅቶች መካከል፤ እማሙ ማሊክ ትምህርት ቤት፣ ወንድም ካሊድ ፋውንዴሽ፣ ባቡል ካኸር፣ ሜቄዶኒያ፣ ቢላሉ ሀበሺ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሙስሊም የጤና ባለሞያዎች ማህበር ይገኙበታል። ሕብረት ባንክ የሸሪዓውን መርህ በተከተለ መልኩ ከወለድ ነፃ የባንክ እገልግሎት መስጠት ከጀመረ 10 ዓመታት እንዳለፈው አስታውሷል። በአሁኑ ሰዓትም ሕብረት ባንክ 23 ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ብቻ የሚሰጡ ቅርንጫፎች ከፍቼ እየሰራሁ ነው ሲል ጠቅሷል። ባንኩ ሸሪዓው
Oct 241 min read


ጥቅምት 8 2018 "ልዩ ባስ" የሚል መጠርያ ያለው ለሀገር አቋራጭ መንገደኞች ዲጂታል የክፍያ ቴክኖሎጂ ይፋ ተደረገ
አዲስ ፔይ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂ እና እንግዳ ትራቭል ቴክኖሎጂ በጋራ "ልዩ ባስ" የሚል መጠርያ ያለው ለሀገር አቋራጭ መንገደኞች ዲጂታል የክፍያ ቴክኖሎጂ ዛሬ ማስጀመራቸውን ተናገሩ። ይህ ቴክኖሎጂ ደንበኞች ወይም ተጓዦች ባሉበት ቦታ ሆነው ወደየሚፈልጉበት አካባቢ ለመጓዝ "የልዩ ባስ" የሞባይል መተግበሪያ በመጠቀም ቲኬታቸውን በኦንላይን መቁረጥ ይችላሉ ተብሏል። የእንግዳ ትራቭል ቴክኖሎጂ መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ባንተአብ አብይ እንደተናገሩት ቴክኖሎጂውን ስራ ላይ ለማዋል አራት ዓመት እንደፈጀ እና አገልግሎቱን ከደንበኞች በተጨማሪ የግል ባስ ባለንብረቶች ስራቸውን ለማቀላጣፍ መጠቀም የሚችሉበት ነው ብለዋል። ይህንን አገልግሎት ደንበኞች ቅንጡ ስልካቸውን በመጠቀም ወደቲኬት መቁረጫ ቦታ ሳይሄዱ ባሉበት ሆነው መቁረጥ እንደሚችሉም ሰምተናል።
Oct 181 min read


ጥቅምት 5 2018የመስከረም ወር የዋጋ ግሽበት 13.2 በመቶ ሆኖ ተመዘገበ፡፡
ያለፈው ወር ሀገር አቀፍ የዋጋ ግሽበት መጠን 13.2 በመቶ ሆኖ መመዝገቡን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ተናግሯል። ከአጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ውስጥ የምግብ ነክ ዕቃዎች (Food Items) የዋጋ ግሽበት 12.1 በመቶ ድርሻ ሲይዝ፣ ምግብ ነክ ያልሆኑ ዕቃዎች (Non-food Items) የዋጋ ግሽበት ደግሞ 14.8 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል። ይህ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ነሐሴ ወር ጋር ሲነፃፀር መጠነኛ ቅናሽ አሳይቷል፡፡ በነሐሴ ወር አጠቃላይ የግሽበት ምጣኔው 13.6 በመቶ ነበር፡፡ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Faceb
Oct 151 min read


ጥቅምት 1 2018 ዘመን ባንክ በተጠናቀቀው 2017 በጀት ዓመት ያገኘው ትርፍ ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነፃፀር ከእጥፍ በላይ መሆኑን ተናገረ።
የአንድ አክሲዮን ትርፍ ወደ 68.3 በመቶ ማደጉንም አስረድቷል። ዘመን ባንክ በ2017 በጀት ዓመት 14.4 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን በዛሬው እለት ዓመታዊ የባለአክሲዮኖች ጉባኤ ላይ ባወጣው ሪፖርት ተናግሯል።...
Oct 111 min read


መስከረም 29 2018 - ኢትዮጵያ ዛሬ የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነትን በይፋ ትቀላቀላለች።
ዛሬ ከሰዓት በኋላ የተለያዩ ምርቶች በየብስ እና በአየር በይፋዊ ስነ ስርዓት ወደ ተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት እንደሚሸኙ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ነግሮናል የንግድና...
Oct 91 min read


መስከረም 28 2018 - ግጭት ለኢንቨስትመንቱ እንቅፋት እንዲሆኑ የአሜሪካ መንግስት መናገሩ ይታወሳል
ኢትዮጵያ ሰፊ የሰው ሃይል፣ ግዙፍ አየር መንገድ እና ሌሎች ለ #ኢንቨስትመንት ምቹ የሚያደርጉ ሁኔታዎች ያሉባት ሀገር ብትሆንም ተለዋዋጭ ህግ፣ ግጭት እና የመሳሰሉት ግን ለኢንቨስትመንቱ እንቅፋት እንደሆኑ የአሜሪካ...
Oct 81 min read


መስከረም 27 2018 - ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ እና ጎህ ቤቶች ባንክ በጋራ ሆነው በአይነቱ አዲስ ነው ያሉትን የቤት ግንባታ ፕሮጀክት ዛሬ ይፋ አድርገዋል።
ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ እና ጎህ ቤቶች ባንክ በጋራ ሆነው በአይነቱ አዲስ ነው ያሉትን የቤት ግንባታ ፕሮጀክት ዛሬ ይፋ አድርገዋል። አሰራሩም በቅድሚያ አንድ ቤት ፈላጊ ወደ ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ በመሄድ የሚፈልውን ...
Oct 71 min read


መስከረም 27 2018 - ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ስምምነትን ማጠናቀቋን ተከትሎ በሸቀጦች ንግድ ዘርፍ መስከረም 29/2018 በይፋ ትጀምራለች ተባለ
ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ስምምነትን ማጠናቀቋን ተከትሎ በሸቀጦች ንግድ ዘርፍ መስከረም 29/2018 በይፋ ትጀምራለች ተባለ፡፡ ይህንን ያሉት የንግድ ትስስርና ወጪ ንግድ ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታዋ...
Oct 71 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page








