የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎች አሁን ላይ ከ45 በመቶ በላይ የሚሆነውን የሀገር ውስጥ ምርት ፍላጎት እየሸፈኑ ነው ተባለ።
- Mar 28
- 1 min read
መጋቢት 19/2018
የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎች አሁን ላይ ከ45 በመቶ በላይ የሚሆነውን የሀገር ውስጥ ምርት ፍላጎት እየሸፈኑ ነው ተባለ።
እንደ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎች ከውጪ ይገቡ የነበሩትን ምርቶች እዚሁ በማምረት በከፊልም ቢሆን ፍላጎቱን እየሸፈኑ ነው።
በዚህም ፋብሪካዎቹ ምርቶችን ወደ ተለያዩ ሀገራት በመላክ የውጭ ምንዛሪ ከማስገኘት ባሻገር የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ማሟላት ላይም ጥሩ ስራ እየሰሩ እንደሚገኙ መረዳት ይቻላል ሲሉ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ድኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ ተናግረዋል።

ከአገልግሎት አሰጣጥ ፣ ከመሠረተ ልማት እና ብድር አቅርቦት ጋር የተገናኙ የፋብሪካዎቹ ችግሮች እንዲፈቱ የተደረገው ጥረት ውጤቶቹ እንዲገኙ አግዘዋል ብለዋል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ጋር በመተባበር በአዲስ አበባና አካባቢዋ ያሉ ፋብሪካዎችን የስራ እንቅስቃሴ የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ባለሞያዎች እንዲመለከቱ አድርገዋል።
ፋብሪካዎቹ በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ፣ በቆዳ ፣ በምግብ ማቀነባበር ፣ በኤሌክትሮኒክስ ስራ እና በመሣሠሉት የተሠማሩ ናቸው።
ያሉባቸው ችግሮች እንዲፈቱላቸው በመንግስት ዕገዛ እንደተደረገላቸው ጠቅሰው አሁንም ያለባቸውም መፍትሔ እንዲያገኙ ለመንግሥት ጥያቄ አቅርበዋል።
ንጋቱ ረጋሳ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments