የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ለማሳደግ የተሰራው ስራ ውጤት እያመጣ ነው ሲል የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተናገረ።
- Mar 27
- 1 min read
መጋቢት 18/2018
የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ለማሳደግ የተሰራው ስራ ውጤት እያመጣ ነው ሲል የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተናገረ።
ሚኒስቴሩ እንዳለው የፋብሪካዎቹ አማካይ የማምረት አቅም አሁን ላይ 66.3 በመቶ ደርሷል።
ከ8ዓመት በፊት አማካይ የማምረት አቅማቸው 46 በመቶ እንደነበር የሚኒስቴሩ የመንግስት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ አበባ ታመነ ተናግረዋል።

ከመሠረተ ልማት እና ጥሬ ዕቃ አቅርቦት እንዲሁም ከመንግስታዊ አገልግሎቶች ጋር የተያያዙ ችግሮች እንዲፈቱላቸው የተደረገው ጥረት የፋብሪካዎቹ የማምረት አቅም እንዲሻሻል ረድቷል ብለዋል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ጋር በመተባበር የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎችን የስራ ሃደት ከትናንት ጀምሮ የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ባለሞያዎች ተዘዋውረው እንዲመለከቱ እያደረገ ይገኛል።
በመገናኛ ብዙሃኑ ባለሞያዎች ከተጎበኙ ፋብሪካዎች አንዱ ቡራዩ የሚገኘው ቦይዝ ፉድ ኮምፕሌክስ ነው።
የፋብሪካው ባለቤት እና ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ታደሠ ችግሮች እንዲፈቱ በመንግሥት በተደረገ ድጋፍ በጥሩ የማምረት ሂደት ላይ እንገኛለን ብለዋል።
ከብድርና የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ጋር የተገናኙ ችግሮች ግን አሁንም መፍትሔ እንደሚሹ ተናግረዋል።
ንጋቱ ረጋሳ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments