top of page

ኢትዮጵያን ከሌሎች ሀገሮች ልዩ ከሚያደርጓት ስርዓቶች አንዱ የቡና አፈላል ስርዓቷ ነው፡፡

  • 17 minutes ago
  • 1 min read

የካቲት 17/2018

ኢትዮጵያን ከሌሎች ሀገሮች ልዩ ከሚያደርጓት ስርዓቶች አንዱ የቡና አፈላል ስርዓቷ ነው፡፡


ቡና በኢትዮጵያ ከተሞችም ሆነ ገጠራማ አካባቢዎች ላይ የተለየ የአቀራረብ ስርዓት አለው፡፡


ይህ የቡና አፈላል ሥርዓትና ሂደት ኢትዮጵያ አለማቀፍ ቅርስ አድርጋ ለማስመዝገብ ስራ መጀመሯም እየተነገረ ነው፡፡



ኢትዮጵያ የቡና አፈላል ሥርዓት (የቡና ሥነ-ሥርዓት) በዓለም አቀፉ የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (UNESCO) በማይዳሰሱ የባህል ቅርሶች መዝገብ ላይ እንዲሰፍር ለማድረግ ስራ ከጀመረች ሰንብታለች፡፡


ኢትዮጵያ የቡና (Arabica Coffee) መገኛ ምድር ብቻ ሳትሆን፣ ቡናን ከመጠጥነት ባለፈ የማኅበራዊ መስተጋብር፣ የሰላም፣ እና የባህል መገለጫዋ እንደሆነ ይነገራል፡፡


በተጨማሪም የቡና አፈላል ሥነ-ሥርዓት በኢትዮጵያውያን ዘንድ የዕለት ተዕለት ሕይወት አካል ነው ያሉት በአዲስ አበባ UNESCO ላይዘን ቢሮ የባህል ፕሮግራም ሀላፊ አቶ ጌቱ አሰፋ ይህ ሥርዓት በዩኒስኮ መመዝገቡ የሰው ልጅን የጋራ ባህል እሴት ለማሳደግ ይረዳናል ብለዋል፡፡


ይህ ሥርዓት በዓለም አቀፍ ደረጃ መመዝገቡ የቱሪዝም፣ የገበያ እድል እና ሌሎች መልካም አጋጣሚዎችን ይዞልን ይመጣል የተባለ ሲሆን እስከ መጭው አመት ድረስ የሚያስፈልጉ መረጃዎች ተሰባስበው ይቀርባሉ መባሉን ሰምተናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….


ፋሲካ ሙሉወርቅ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page