top of page

በኢትዮጵያ የፋይናንስ ተቋማት የሚገላበጠው አብዛኛው ገንዘብ ወይም ከ73 በመቶ በላዩ የሚዟዟረው በዲጂታል መንገድ ነው፡፡

  • 9 minutes ago
  • 1 min read

መጋቢት 8/2018


በኢትዮጵያ የፋይናንስ ተቋማት የሚገላበጠው አብዛኛው ገንዘብ ወይም ከ73 በመቶ በላዩ የሚዟዟረው በዲጂታል መንገድ ነው፡፡


በተያዘው የበጀት ዓመት በ6ት ወራት ውስጥ ብቻ 14.56 ትሪሊዮን ብር በዲጂታል መንገድ ተገላብጧል፡፡


ይህ በዲጂታል ገንዘብ ማስተላለፍ ጊዜን የሚቆጥብ፣ ምቹ መሆኑ ቢጠቀስም የአገልግሎት ክፍያውና ሌሎች ተቆራጮች መኖርና ለአጭበርባሪዎች የተጋለጠ ነው በሚልም ይወቀሳል፡


መንግስታዊ ተቋማት ለሚሰጡት አገልግሎት ክፍያቸውን ወደ ድርጅት ባንኪንግ ማዞራቸውን ተከትሎ ከማህበረሰቡ ለአገልግሎት እየተባለ የሚቆረጠው ገንዘብ እየበዛ መጥቷል፡፡


ደመወዝተኛውም ይሁን በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ለተለያዩ የክፍያ ስርዓቶች የሚያደርጉት የገንዘብ ልውውጥ ተደራራቢ ታክስ እንዲከፍሉ አያደርግም? በጉዳዩ ላይ የዘርፉን ባለሞያዎች ጠይቀናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…..


ማርታ በቀለ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page