የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች መዋዕለ ነዋያቸውን ፈሰስ ለሚያደርጉ ባለሀብቶች እምነት እንዲያደርጉ ቢያስችላቸውም በየጊዜው የሚለዋወጡ ህጎች ግን አሁንም ችግር ሆኖ ቀጥሏል ተባለ፡፡
- 4 hours ago
- 1 min read
የካቲት 12/2018
ኢትዮጵያ እያደረገቻቸው ያሉ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በሀገሪቱ መዋዕለ ነዋያቸውን ፈሰስ ለሚያደርጉ ባለሀብቶች እምነት እንዲያደርጉ ቢያስችላቸውም በየጊዜው የሚለዋወጡ ህጎች ግን አሁን ኢንቨስት ለሚያደርጉ ችግር ሆኖ ቀጥሏል ተባለ፡፡
ከውጭ የሚመጣ ሀብት በተወሰኑ ዘርፎች ላይ ብቻ ማዋሉም ሌሎች ዘርፎች በቂ ፋይናንስ እንዳያገኙ ከልክሏል ተብሏል፡፡

እንደ ትምህርት ፣ ጤና ፣ አነስተኛ እና ጥቃቅን ስራ ፈጠራ በመሳሰሉ ማህበራዊ ዘርፎች የሚሳተፉና ተዕኖ የሚያሳድሩ፣ ትርፍም የሚያገኙ ተቋማት የኢንቨስትመንት ሁኔታ ምን ይመስላል በሚል የተደረገ የምክክር መድረክ ላይ ነው ወሬው የሰማነው፡፡

ዝግጅቱን ያሰናዳው ACE investment እና Impact Advisors የተባለ የኢትዮጵያ ተቋም ከአለም አቀፉ አቀፍ GSG ተቋም ጋር በጋራ በመሆን ነው፡፡
ተቋማቱ ባለፉት 4 ወራት በኢትዮጵያ በትምህርት ፣ ጤና በመሳሰሉት ማህበራዊ ዘርፎች የተሰማሩና ትርፍ የሚያገኙ ተቋማት የኢንቨስትመንት ሁኔታ ምን እንደሚመስል ፣ አበርታችን ነገሮች የሚታዩ ችግሮች ላይ ዳሰሳ ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7












Comments